ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Kanalga Telegram’da o‘tish
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Ko'proq ko'rsatish2 936
Obunachilar
-124 soatlar
+3307 kun
+38330 kun
Postlar arxiv
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ልዩ ቦታው በአርማንያ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይሎች በተፈፀመ የጦር ወንጀል አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የተባሉ አርሶ አደር በግፍ መገደላቸውን ተሰማ!
ሰኔ 29/2018ዓ.ም
የጦር ወንጀለኛው የብልፅግናው አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ስርዓት ወለድ ታሪክ ይቅር የማይላቸውን ግፎች በህዝባችን ላይ በየቀኑ እየፈፀመ ሲሆን ሰኔ 25 ቀን 2018ዓ.ም ከምሽቱ 4:00 ላይ ከመኖሪያ ቤታቸው በአገዛዙ ሀይሎች የተወሰደው የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የ48 ዓመቱ ጎልማሳ አርሶ አደር አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ እጅግ አሰቃቂ በሆነ አገዳደል በአገዛዙ ሀይሎች ህይዎቱ ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ።
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ስር የምትገኘው የአርማኒያ ቀበሌ ታዳጊ ከተማ ለበርካታ ወራት በአማራ ፋኖ ቁጥጥር ስር የቆየች ሲሆን በቅርቡ ወደ ቀጠናው የገባው የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለጦር በንፁሀን ወገኖች ላይ በየቀኑ እየፈፀመ ያለው የጦር ወንጀል ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን የሁለት ልጆች አባት የሆነው አርሶ አደር አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ በመኖሪያ ቤቱ በምሽት በተወሰደ ማግስት ሁለት ዓይኖቹን በማውለቅ የቀኝ እጁን በገጀራ በመቁረጥ ለአንድ ቀን ካሳደሩት በኋላ በሁለተኛው ቀን ሙሉ ሰውነቱን በገጀራና በጩቤ በመቆራረጥ እጅግ ዘግናኝ በሆነ አገዳደል ህይዎቱን ማጥፋታቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል።
በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለውን የአቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ አስክሬን ለመውሰድ ዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2018ዓ.ም ወደ መከላከያ ካምፕ ያቀኑት በአማራነቱ ሰማዕት የሆነው የቅርብ ዘመዶችና ህፃናት ልጆቹ በአገዛዙ ሀይሎች ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው አስክሬን ተከልክለው በተኩስ እንዲበተኑ መደረጋቸውን በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል።
አገዛዙ በአርማኒያ ቀበሌ እየፈፀመ ያለው የጦር ወንጀል ሞልቶ የፈሰሰ ሲሆን ዕድሚያቸው ያልደረሰ ልጃገረዶች የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ሲፈፀምባቸው በርካታ ወጣቶች በአስገዳጅ ሁኔታ የሚሊሻ ስልጠና ወስደው እንዲጠረነፉ መደረጋቸውን ቤተሰቦቻቸው በከፍተኛ መሬትና ሀዘን ውስጥ ሆነው ተናግረዋል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+1
በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተፈፀመ ሲሆን የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን " አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴን" በጨለማ አራት ሰዓት(4:00) ከቤቱ አውጥተው ወደ ካምፕ በመውሰድ ለአንድ ቀን አሳድረው በማግስቱ "አይኑን" በማውለቅ እጁን በመቆራረጥ የገደሉት ሲሆን፤ ከገደሉም በኋላ እሬሳውን ለቤተሠቡ እዳይሠጥ የከለከለ የአለማችን አረመኔ ሆኗል። አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፡ ልጆቹን ያለ እናት በስስት ሲያሳድግ የኖረ፣ ሚስቱ ሞታበት በሀዘን የተጎዳ ትጉሕ ገበሬ ነበረ። ይሕንን አረመኔዊ ድርጊት የተመለከቱት ዘመድ ጎረቤቶቹ ከሀዘን በላይ ሆኖባቸው ቤታቸውን ዘግተው በጫካ ይገኛሉ።
ሌላኛው ደግሞ በቀን 28/10/2018 ዓ.ም በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር እዲሁ አንድ ንፁህ ገበሬ በአገዛዙ ተረሽኗል። አቶ መንገሽ ታዬ የተባሉ የ55 ዓመት ገበሬ ለህክምና ከአጋምሳ አምባ ቀበሌ ወደ መኮይ ከተማ ያቀኑ ሲሆን፡ ከሚታከሙበት ጤና ጣቢያ በማውጣት አስረው ከገረፉ በኋላ በግፍ በአገዛዙ ተረሽነዋል።
በመንዝ አውራጃ ፤ ጥርጥራ ቀበሌ የደፈጣ ጥቃት፤ የአገዛዙ 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር በፋኖ መብረቃዊ እርምጃ ጉዳት አስተናገደ!!
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ የደፈጣ ውጊያ መርህ መሰረት፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር (በአባተ ፩ኛ ሻለቃ) በመንዝ ላሎ ክላስተር ጥራጥር ቀበሌ ወታደራዊ የበላይነትን በማድረግ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል።
ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ድረስ በተካሄደው የሰዓታት ጠንካራ ውጊያ፣ ከመንዝ ላሎ ወገሬ ከተማ ተነስቶ ወደ ጥርጥራ ቀበሌ ለመንቀሳቀስ የሞከረው የብልፅግናው 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር "ሀያደጋ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ በታቀደ ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት እቅዱ ከሽፏል።
የኮሪ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ባስተላለፈው ግንባር መረጃ መሰረት፣ የፋኖ ስልታዊ ጥቃት የወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸሙን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ነበር። በዚህም የአገዛዙ የጥምር ጦር አባላት የነበሩ አንድ የ፶ አለቃ ማዕረግ ያለው የሚሊሻ አመራርን ጨምሮ ከ10 በላይ ወታደሮች የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ቆስለው በአምቡላንስና በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሆስፒታል እደላከ ተረጋግጧል።
በሜዳው ፍልሚያ ከፍተኛ የሰው ኃይልና የሞራል ስብራት የገጠመው የአገዛዙ ሰራዊት፣ ሽንፈቱን ለመቀልበስ ከመንዝ ቀያ ዘመሮ ከተማ የኃይል ማዛባት (ማጠናከሪያ ኃይል) ለማንቀሳቀስ ቢሞክርም በምኒልክ ልጆች ፅኑ መከላከል ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። ሰራዊቱ ወታደራዊ ግዳጁን ማሳካት ሲያቅተው፣ የክፍለ ጦሩ አስተዳደር ኃላፊ የፋኖ ልዑል እሱባለውን ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በር በመስበርና ንብረት በመዝረፍ የተለመደውን የውንብድና ተግባሩን ፈፅሟል።
ይህ በመንዝ ላሎ ቀጠና የተመዘገበው ድል፣ በትጥቅ ትግሉ ሂደት የፋኖን የደፈጣ ውጊያ ብቃት፣ የመረጃ የበላይነት እና የተደራጀ አቅም በተግባር ያሳየ ሲሆን፣ የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለ ጦር መራር ሽንፈት አከናንቦ ወደ መጣበት እንዲፈርጠጥ አድርጎታል።
"ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ፡ ሳሲት ክላስተር የዓመታዊ ሥራ አፈፃጸምን ገምግሞ የዕውቅና መድረክ ሲያካሂድ፡ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የብልፅግናው ሠራዊት ንፁሀንን በግፍ ረሸነ!!
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በቀን 29/10/2018 ዓ.ም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ ተጉለት ቀጠና ሳሲት ክላስተር ዓመታዊ የሥራ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ ። በዚሁ መድረክ ላይ የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች፣ የክላስተርና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት ድርጅታዊ ተልዕኮዎች፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች በስፋት ተገምግመዋል ።
📌 ዋና ዋና የውይይት ነጥቦች
~ ቀጥተኛ የድጋፍና አርአያነት: የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ ያደረጉት ድጋፍ የሚበረታታ ጅምር በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል ።
~ የተቋማት ነፃነት: ክላስተርና ቀበሌዎች ያለምንም ጣልቃ ገብነት የተሰጣቸውን ተቋማዊ ሥልጣን በነፃነትና በኃላፊነት እንዲተገብሩ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩ ተገልጿል ።
~ የተጣለባቸውን ሕዝባዊና ድርጅታዊ ኃላፊነት በተሻለ ሁኔታ ለተወጡ ቀበሌዎችና አመራሮች የምስጋናና የዕውቅና ሽልማት ተበርክቷል ። ይህ ሽልማት ጠንካራዎችን ለማበረታታትና ደካማ አፈፃጸም ያሳዩትን ደግሞ ለቀጣይ ሥራ ለማነቃቃት ያለመ ነው ።
✊ ለቀጣይ ትግል የቀረበ ጥሪ:-
~ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች "ተጉለት በታሪክ የነበረውን ብሔራዊ ሚና በአማራ የሕልውና ትግል በድጋሚ በተግባር አሳይቶናል" በማለት ለአመራሩና ለማኅበረሰቡ ምስጋና አቅርበዋል ።
~ በመጨረሻም፣ በቀጣይ የሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎችንና ግዳጆችን በአግባቡ ለመወጣት እንዲሁም የተደቀነውን የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ አመራሩና ሕዝቡ በተለመደው የጋራ አንድነትና ትውልዳዊ ኃላፊነት እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል ።
በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተፈፀመ ሲሆን የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን " አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴን" በጨለማ አራት ሰዓት(4:00) ከቤቱ አውጥተው ወደ ካምፕ በመውሰድ ለአንድ ቀን አሳድረው በማግስቱ "አይኑን" በማውለቅ እጁን በመቆራረጥ የገደሉት ሲሆን፤ ከገደሉም በኋላ እሬሳውን ለቤተሠቡ እዳይሠጥ የከለከለ የአለማችን አረመኔ ሆኗል። አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፡ ልጆቹን ያለ እናት በስስት ሲያሳድግ የኖረ፣ ሚስቱ ሞታበት በሀዘን የተጎዳ ትጉሕ ገበሬ ነበረ። ይሕንን አረመኔዊ ድርጊት የተመለከቱት ዘመድ ጎረቤቶቹ ከሀዘን በላይ ሆኖባቸው ቤታቸውን ዘግተው በጫካ ይገኛሉ።
ሌላኛው ደግሞ በቀን 28/10/2018 ዓ.ም በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር እዲሁ አንድ ንፁህ ገበሬ በአገዛዙ ተረሽኗል። አቶ መንገሽ ታዬ የተባሉ የ55 ዓመት ገበሬ ለህክምና ከአጋምሳ አምባ ቀበሌ ወደ መኮይ ከተማ ያቀኑ ሲሆን፡ ከሚታከሙበት ጤና ጣቢያ በማውጣት አስረው ከገረፉ በኋላ በግፍ በአገዛዙ ተረሽነዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ከእንግዲህ አንገት አይደፋም፣ ዙፋኑ ተዘጋጅቷል፤ የብርሃን ሰይፉን የመዘዘው የአማራ ልጅ ፋኖ በአሸናፊነትና በግርማዊነቱ ወደ ፊት እየገሰገሰ የመኖራችን ዋስትና ሆኗል። ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ
በእናርጅ እናውጋ ወረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
====================
.....ሰኔ 29/2018 ዓ/ም
201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦር የእናርጅ እናዉጋ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስትማሀበረሰቡን እያወያየ ችግሮችን እየፈታይገኛል በዛሬዉለትም የመጠያ እነዳራ ቀበሌ ማህበረሰብን ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን፦
በዉይይቱ የቀረቡ አጀንዳዎች
➺.የመልካም አስተዳደር ችግሮች
➺.የዉል መሬቶችን አጠቃቀም
➺.የፍትህ አሰጣጣችንን በተመለከተ በስፋት ውይይት የተካሄደ ሲሆን
➺የቀበሌ መዋቅር አመራሩን ህዝቡ በመገምገም የተለያዩ የአሰራር ክፍተት አለባቸው የተባሉትን በመለየት እና መገምገም የቀበሌዉን አመራር በአዲስ የማዋቀር ስራ በመስራት አሁን ላይ ትግላችን የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ገለፃ በማድረግ ውይይታችን ተጠናቋል።
>> ከህዝባችን ጋር እየተመካከርን ድላችን እናስቀጥላለን።<<
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ሰበር ዜና!!!
የጀብደኛው ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ጌጤ ግርማ መብረቅ ክፍለጦር በደፈጣ ድል ተቀዳጀ።
እድሜ ልኩን ሲላላክና ሲያጎበድድ ለአገዛዙ ገረድ በመሆን የአማራን ህዝብ ሲያሳድድና እያሸማቀቀ የኖረው ጌታቸው መንግስቱ በጉቶ ጊዳ ወረዳ ሜጢ ቀበሌ ልዩ ቦታው አንገር አለልቱ ላይ በጌጤ ግርማ መብረቅ ክፍለጦር እስከወዳኛው ተሸኝቷል።
በ1999ዎቹ በጉቶ ጊዳ ወረዳ ሲኖሩ የነበሩት የቤንሻንጉል ጉምዝ ወድሞቻችንን ከቦታው በማባረርና ይዞታቸውንና ተወልደው ካደጉበት ቀያቸው በማባረር ይዞታቸውን ቀምቶ ይኖር የነበረ ግለሰብ ነው።
ለስርዓቶቺ መላላክን ስራየ ብሎ የተያያዘው ይህ ሰው ፓይሌት በማብረር የሚታወቀው ጌታቸው በሰሜኑ ጦርነትም ከትግራይ ወድም ህዝብ ላይ ድብደባ ሲያካሂድና ሰጨፈጭፍ የነበረ ግለሰብ ነው።
አሁንም ለዚህ ፋሽስት መግስት በሎኬሺኖቺ እድሁም ኦፒ በመሆን በተለይ ወለጋ ምድር ላይ ይሄን 15ቀን እየተካሄደ ያለውን የህዝባቺንን ጭፍጨፋ ሲመራ የነበረው ይህ ግለሰብ ነወ።በተለይ ማህበረሰባቺንን ነገ ታያለህ እያለ ነበር ቃሉን ተከትለው በሚናገርባቸው ቦታዎቺ ሁሉ የጦር ሄሌኮፍተር ህዝቡን ሲደበድቡ የሚውሉ ይህን ሁሉ ሲያደርግ ከቆየ ቦኋላ በአማራ የቁርጥ ቀን ልጆቺ ተሸኝቷል።
ግፍ የወለደን፡ግፈኞቺን የምቀጣ
የአንሻ ሰይድ ወድሞቺ ነን!!!
አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ
ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ29/2018ዓ.ም
ወታደር የሚለውን ስሙን ብቻ ሳይሆን ውትድርናን በተግባር የሚኖር፤ ለመርህ እና ለአሰራር የሚመች ባህሪን የተላበሰ የተሰጠውን ግዳጅ በጊዜው እና በሰዓቱ የሚፈፅም፣ ለትንሹም ለትልቁም ታዛዥ እና ብርቱ አመራራችን፤የውስጥም የውጭም ጠላት ገፍቶ የማይጥልህ ከማንም ጋር አብሮ መስራትም አብሮ መኖርም የሚያስችልህ መልካም ስብዕናን የተላበስህ የትግል ጓዴ ይህ ጦርነት ካስተዋወቀኝ ጀግና መሪዎች ውስጥ መቶ አለቃ አበበ ሰውመሆን እንኳንም ተወለድክ!! አንተን ለሚጠሉህ ለጠላቶችህ እንኳንም ተወለድክባቸው። የአፋብን ም/አዛዥ ለወታደራዊ አስተዳደር አርበኛ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው
አፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር በደፈጣ ጥቃት በጠላት ላይ ድል መቀዳጀቱን ሲገልፅ፡ የሀገር መሠረተ ልማቶች በሕዝብና አባት አርበኞች መሠራቱ ተገለፀ!!
ቀን 29/10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር በቅርቡ የሪፎርም ስራ ካከናወነ በኋላ፣ በአገዛዙ ኃይሎች ላይ የተሳካ የደፈጣ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ ።
ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ላይ ከመንዝ ቀያ ክላስተር ዘመሮ ከተማ በመነሳት ወደ ዘረት ሲንቀሳቀስ በነበረው የመከላከያ ሰራዊት ላይ የአፄ ምኒልክ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ አባላት አስደናቂ ድል አስመዝግበዋል። በዚሕ የደፈጣ ጥቃት የጠላት ኃይል ክፉኛ መጎዳቱን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ከግንባር በደረሰው መረጃ አረጋግጧል።
ጠላት የደረሰበት ጉዳት ፧ በተሰነዘረው የደፈጣ ጥቃት 6 የአገዛዙ ኃይሎች የተገደሉ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልተረጋገጠ ቁስለኞች በዘመሮ ከተማ ሆስፒታል በሕክምና ላይ እንደሚገኙ ዕዙ አረጋግጧል ።
የብልፅግናው ሰራዊት የደረሰበትን ምት መቋቋም አቅቶት ሙትና ቁስለኛ ይዞ፣ ያሰበውን ዓላማ ሳያሳካ ወደመጣበት ለመመለስ ተገድዷል ።
በቅርቡ የአመራር ሪፎርም ያደረገው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር፣ በአሁኑ ወቅት የተሻሉ ግዳጆችን በመፈፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ ክፍለ ጦሩ ራሱን ለግዳጆች በማዘጋጀት ላይ ከመሆኑም በላይ፣ በከፍተኛ የሰው ኃይል ግንባታ ላይ እንደሚገኝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በሰጠው መግለጫ አመልክቷል ።
በተያያዘ ዜና የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ሕዝቡን በማስተባበር የመሰረተ ልማት ስራ እየሰራ ይገኛል። ሰኔ 29/2018 ዓ/ም በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ቀወት ወረዳ ተሬ ክላስተር የጃበርና ጎልጎዲሳ ጎጥ ለመንገድ መሰረተ ልማት ስራ ዘመቻ በነቂስ በመውጣት ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን በሞራል ሲሰሩ ውለዋል።
እንዲሁም በተጨማሪ በተመሳሳይ በቀን 29/10/2018 ዓ/ም በዚሁ አውራጃ ማጀቴ ክላስተር የ"አየለ አባተ ብርጌድ" አባት አርበኞች ክረምትን የዋጀ መሠረተ ልማት ተሠርቷል። የማህበረሰቡን እንቅስቃሴ እዳይገታ ተብሎ የታሠበው የጃራ ወንዝ ጋቢዮን ስራ አባት አርበኞቹ በሞራልና በትብብር የወንዙን ፍሰት መቆጣጠር የሚያስችል ስራ አከናውነዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አከናወነ!!
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
ተሃድሶ ለወታደር ዘርፈ ብዙ የስኬታማ ወታደራዊ ግንባታ ስራዎች የሚከናወኑበት የወታደራዊ ሳይንስ ክፍል አካል ሲሆን፣ ወታደራዊ ግዳጆችን በመገምገም፣ የአመርና የሰራዊቱን ወቅታዊ የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ህዝባዊነትን የተላበሰ የፋኖ ሰራዊት መገንባትን ራዕይ ያደረገ ለየትኛውም ግዳጅ ብቁ እና በከፍተኛ የሞራል ስንቅ የተሞላ አማራዊ ስነልቦና የተላበሰ ዘመናዊ የአማራ ፋኖ ሰራዊት የማደራጀት ዓላማ አንግቦ የፖለቲካዊና የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርቶች በጥምረት በአንድ መድረክ ላይ የሚሰጡበት ዘመናዊ የማታገያ ጥበብ ነው።
የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ከሰኔ 24/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አምሥት(5) ቀናት ልዩ የተሃድሶ መርሀ ግብር ለክፍለጦሩ አመራርና አባላት ሰፊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ በመስጠት የተሳካ የግንባታ መድረክ ማካሄዱን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
በዚሁ የግምገማና የግንባታ መድረክ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የድርጅትና የዕዝ አመራሮች በአካል ተገኝተው ለክፍለ ጦሩ አባላት ውጤታማ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን፣ የአፋብን ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፊትአውራሪ ባዩ አለባቸው እና የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አከበር ስመኘው እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ አመራሮች በተዘጋጀው የተሃድሶ መርሀ ግብር ላይ በአካል ተገኝተው ለራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር አባላትና አመራሮች በቂ ግንዛቤ መስጠታቸውን ኮሩ አክሎ ገልጿል።
በመድረኩም ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እንዲሁም ስለ ውስጣዊ አንድነት ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ በተለዬ አቀባበል ዓላማና ግብ ተኮር መግባባቶች የተፈጠሩበት የተሳካ መድረክ ሲከናወን ሰንብቷል።
ይህንን ድርጅታዊ የሆነ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ግንባታ ተከትሎ፣ የሰራዊቱን ሞራል ይበልጥ ከፍ ያደረገ ደማቅ የተሃድሶ መርሀ ግብር ሲከናወን፣ ይህን የተግባር ተኮር ስልጠና እስከ ግንባር ምሽጎች ድረስ በመዝለቅ የሰራዊቱ የሞራል ማማ በመሆን የሚታወቁት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር የናደው ክፍለ ጦር የባህል ቡድን አባላት የፕሮግራሙ ድምቀት ሆነው የተሳተፉበት መርሀ ግብር የተካሔደ ሲሆን፣ በዕለቱም የአማራን ማንነትና ባህል የሚገልጹ ልዩ ልዩ የባህል ጭውውቶችና ክዋኔዎች ቀርበው ለሰራዊቱ አባላት ከማነቃቃት አልፎ ለሰራዊቱ የሞራል ስንቅ በመሆን የተሳካ መድረክ ተከናውኗል።
የስልጠናው ተሳታፊ ከሆኑት የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦር ሰራዊትና አመራሮች በሰጡት አስተያየት፣ ይህ ዓይነቱ ድርጅታዊ ስራና የግንባታ መርሃ ግብር ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራ መሆኑን በመግለፅ፣ አያይዘውም ይህ መድረክ ቀጣይ ለምናደርገው የተቀናጀ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ነው፤ ትግላችንም ከተናጠል ወደ ህብረት የተሸጋገረበት በመሆኑ፣ በማንኛውም ሁኔታና ሰዓት ለህልውና ትግሉ የምንከፍለውን መስዋዕትነት በደስታና በሙሉ ልብ እንድንወጣ ያደርገናል ብለዋል።
ራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦር የተሰየመበት የጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ስም ተራ ስያሜ ብቻ እንዳልሆነ የገለጹት አመራሮቹና አባላቱ፣ የህዝብ ፍቅርንና በፅናት ለዓላማ የሚደረግ ተጋድሎን ከክፍለ ጦሩ የአሁናዊ ህልውና ትግል ጋር በማቆራኘት የስልጠና ቆይታቸውን ከታሪክ ጋር አነፃፅረው ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
የራስ አበበ አረጋይ ክፍለ ጦርም ከትንሽ የሰው ሃይልና ትጥቅ በመነሳት በከፍተኛ ፍጥነት አሁን ግዙፍ ከሚባሉ ክፍለ ጦሮች ተርታ እንድትሰለፍ ያስቻላት የአመራሮቿ እና ሰራዊቱ የአርበኛው ራስ አበበ አረጋይ የፅናት ፈለግን በመላበስ ሌት ከቀን ተግተው በመስራታቸው መሆኑንም በመድረኩ አስታውሰዋል። ታዋቂው አርበኛ ራስ አበበ አረጋይ በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት የሸዋ አርበኞችን በማስተባበርና በመምራት፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ለህዝብ ነፃነት ያደረጉት ተጋድሎ ዛሬም ለክፍለ ጦሩ አባላት ታላቅ የፅናት ምንጭ መሆኑም ተነስቷል።
በመሆኑም የክፍለ ጦሩ አባላት ትናንት በታሪክ እንደተደረገው ሁሉ፣ ዛሬም ሆነ ነገ ይህንን ታሪካዊ ስም በተግባርና በልዩ ልዩ የጦር ሜዳ ጀብዱዎች እንደሚያስጠሩት በጋራ ቃል በመግባት ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው የተሃዲሶ መርሀ ግብር በስኬት ተጠናቋል ሲል የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ገልጿል።
በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ አመራሮችና ሰራዊት ስለ ህዝብና ዓላማ፣ ስለ አማራ ታሪክና ፋኖነት እንዲሁም ስለ ድርጅትና ድርጅታዊነት ያላቸውን ግንዛቤ ይበልጥ በማሳደግ፣ ቀጣይ መርህን የተላበሱ አሰራሮችን በማስተካከል ተግተው በመስራት ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ዝግጁ መሆናቸውን በቁርጠኝነት አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ በግንባር መረጃው አረጋግጧል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የህልውና እና የአንድነት ጥሪ!
የተከበራችሁ የመላው አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አመራሮችና ታጋዮች! ለነፃነቱና ለክብሩ የሚፋለመው ፅኑ ህዝባችን! እንዲሁም ይህንን የታሪክ መጋረጃ የምትመለከቱ የትግራይና የኤርትራ ህዝቦች ሆይ!
ዛሬ እኔን የሚያውቀኝ ያውቀኛል! እኔ ከታሪክ ማዕበል የተረፍኩ፣ ከእውነት ማዕዘን የቆምኩ፣ ነገር ግን በማንነቴ ምክንያት መከራን የተጋትኩ የዚሁ ህዝብ አንዱ ነኝ።
እውነት ነው፣ እንደ አለመታደል ሆኖ በዚህች ምድር ላይ የአይሻ መሐመድን ስቃይና የሞት ፍርድ አይተናል። የታሪክ እሳት አጣዬን ሲያቃጥላት፣ የመተከልን ምድር የአክራሪዎች ገሞራ ሲያነድደው፣ ራያና ወልቃይት በግፍ ተፈናቅለው ህዝባችን ለስደት ሲዳረግ በዓይናችን ተመልክተናል።
እኔ እንደ አማራ፣ ከሌቅ እስከ ደቂቅ በተደራጁ ሆዳም የውስጥ ባንዳዎችና በተደራጁ አክራሪ ኃይሎች ሴራ ውስጤ ደምቷል! ስጋዬም ልክ እንደ ሰደድ እሳት ይበላኛል! ነገር ግን ህመማችን ወደ ተስፋ መቁረጥ ሳይሆን ወደማይበገረው ፅናት ሊቀየር ይገባል! ውድ አማራውያን ሆይ!
በታላቁ ፈጣሪ ስም ልለምናችሁ! በጀግናውና በማይበገረው በአሳምነው ዓፅም ልማጸናችሁ! ዛሬ ታሪክ አንድ እንድንሆን ያስገድደናል፤ ዛሬ ህልውናችን የሚጠይቀው ብቸኛ መፍትሄ መተባበርን ብቻ ነው! እባካችሁ አንድ እንሁን! መለያየት የጠላቶቻችን ድግስ ነው፣ አንድነት ግን የእኛ የነፃነት ጎዳና ነው!
በመጨረሻም… እንደ ዱር አውሬ ለምታሳድዱኝ የብልፅግና አሽከሮች መልዕክት አለኝ፦ ከቻላችሁ ተውኝ! ማሳደዳችሁ ከዓላማችን አያናውጠንም። እኛ የምንታገለው አማራ በክብርና በድል አሸንፎ፣ ከዚህ ግውዝ ከሆነ የብልፅግና ስርዓት ወጥቶ በሰላም፣ በፍትህና በእኩልነት የሚኖርባትን አዲስ ምድር ለመገንባት ነው!
ድል ለህዝባችን! አንድነት ለክንዳችን! አመሰግናለሁ።
የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 45ተኛ (መብረቅ) ክፍለ ጦር የሰራዊት ተሀድሶ ስልጠናውን አጠናቀቀ!!
በምዕራብ ወሎ ግንባር ወግድ ወረዳ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው 45ተኛ (መብረቅ) ክፍለ ጦር ከወግድ ባሻገር ወደ አጎራባች ወረዳዎች እና ወንዝ ተሻግሮ ጎራ ዞሮ ጭምር ወደ ደራ እንድሁም መርጦለማርያም በመጓዝ ከወገን ኃይል ጋር እየተቀናጀ የጠላትን አከርካሪ የሚሰብር ሰራዊት ያለበት ክፍለ ጦር ነው::
የክፍለ ጦሩ ሰራዊት ከእስካሁኑ በበለጠ ሁኔታ ተጠናክሮ ለጠላት እጅጉን አስፈሪ ሆኖ የማድረግ አቅሙም ይጨምር ዘንድ የተሃድሶ ፕሮግራም እና የአቅም ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ለ 10 ተከታታይ ቀናት ሰራዊቱ በጥልቅ ተሃድሶ እና በስልጠና ላይ ቆይቷል::
በዛሬው እለት የመርሀግብሩ ማጠናቀቂያ የሆነው የምርቃት ፕሮግራም ተካሂዷል:: በዚህ ፕሮግራም ላይ
የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ም/ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ሀብታሙ ደምሴ እና የ105ኛ ኮር እንድሁም የ45ተኛ ክፍለ ጦር አመራሮች የተገኙ ሲሆን ሻለቃ ሀብታሙ ደምሴ በፕሮግራሙ ላይ ባደረገው ንግግር:-
"መብረቅ በጠላት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ለመፈፀም ያሥችላት ዘንድ የሰለጠነና የበቃ ሰራዊት ገንብታለች። መብረቅ እናት ክፍለጦር እንደመሆኗ መጠን የድርጅቱን መመሪያ በጠበቀ መልኩ ማንኛውንም የሚሰጣትን ግዳጅ ለመፈፀም በዝግጁ ላይ ናት" ሲል ተደምጧል::
በሰልጠናው ወቅት የተሻለ ብቃት ላሳዩ የሰራዊት አባላት የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክተዋል። ስለ የሃድሶ እና ስልጠናው አስተያየታቸውን የሠጡ የሠራዊት አባላት በበኩላቸው በስልጠናው ያገኙት ወታደራዊና ፖለቲካዊ እውቀት ከፍተኛ መነቃቃትን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኘው የ45ተኛ (መብረቅ) ክፍለ ጦር ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ ታመነ ጎበዜም ስልጠናው አስፈላጊ እንደነበር አውስቶ ለወደፊት ለሚሰጥ ማንኛውም ግዳጅ ሰራዊቱ በሞራልም በአካልም ዝግጁ መሆኑን አስረግጦ ተናግሯል::
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ
ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም
+4
ጋንታ መሪው የፖሊስ አባሉ እና ፓራኮማንዶወች ፋኖን ተቀላቀሉ ያለ አንድ ጥይት ጩኸት የብልፅግና ተቋሙ እየፈራረሰ ነው።
===========================
....ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
ከግንደወይን ከተማ ወጥተው 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ፦
1.አበበ ጌታሁን......ጋንታ መሪ ፖሊስ
2.ተመስገን ደመቀ ......አጃቢ ፖሊስ
3.አለማየሁ ጨምር .....ፓራ ኮማንዶ
4.ደረጀው ተረፈ.........ሚሊሻ ሲሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ በከፍተኛ ሁኔታ የማስከዳት ስራው በትኩረት እየተሰራበት ሲሆን በዛሬው እለትም ከግንደወይን ከተማ ወጥተው 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆኑ በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ኑ ታሪካዊ አሻራችን አብረን እናሳርፍ ዛሬ ላይ ቢሆንም ጊዜው አልረፈደም ኑ ወደ ትክክለኛ ማንነታቹህ ተመለሱ።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ያልተነገረለት የይፋቱ ጀግና አርበኛ ዝናው በቀለ
በታሪክ ማዕበል እና በሀገር ጥሪ መካከል፣ የማይፈርስ የአቋም ጽናት እና ፍጹም መስዋዕትነትን የጠየቀ የአርበኛ ዝናው በቀለ ጀግና እውነተኛ የህይወት ጉዞ። ነገሩ እንዲህ ነው ከአንፆኪያ ገምዛ ምድር የወጣው አርበኛ፣ የአጣዬ በተደጋጋሚ በኦነግ መቃጠል እና የህዝቡ ሰቆቃ ከልቡ ሊታጠብ የማይችል ጠባሳ ጥሎበት፣ የመጻሕፍት ቦርሳውን ጥሎ የነጻነትን መሣሪያ አነገተ።
ይህ በትውልድ ታሪክ ማህደር ውስጥ በደማቅ ቀለም የሚጻፍ፣ ከደም እና ከእሳት የተወለደ የጀግንነት ገድል ነው፦
ጥቅምት 15 ቀን 2014 ዓ.ም.። ሸዋ በጭጋግ እና በጦርነት ደመና በተዋጠችበት፣ ተጠርናፊው የፋኖ ኃይል ገና በአዲስ መልክ እየተደራጀ በነበረበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ፣ ያ የአንፆኪያ ገምዛ ቆራጥ አርበኛ ወደ ትግሉ መድረክ ዘለቀ። እነዚያን ታላላቅ የቁርጥ ቀን መሪዎች ኢሳያስ ደመቀ፣ ደመላሽ ደመቀ፣ ስለሺ አበረ እና ሺመልስ ንጉሴን ተቀላቅሎ ታሪክ ወደሚሠራበት መሠረት አመራ። ያ ቀን፣ መመለስ የሌለው የነጻነት ጉዞ መጀመሪያ ነበረ።
ከአጣዬ እስከ መራቤቴ፤ ከመራቤቴ እስከ ራያ ቆቦ በነበረው ጦርነት ሀገርን ለመገንጠል እና ህዝብን ለማንበርከክ ጦርነት በከፈተበት ወቅት፣ እርሱ በሰሜን ሸዋ ምድር ላይ እንደ መብረቅ ተንቀሳቀሰ። ከአጣዬ ተነስቶ እስከ መራቤቴ ድረስ ያለውን ረጅም መንገድ በእግሩ በማቋረጥ፣ ህዝቡን የማደራጀት እና ተጠርናፊውን ኃይል ወደ አንድ ማዕከል የመሰብሰብ ታላቅ ኃላፊነት ወሰደ።
ሌላውን ኃይል ደግሞ በየሰፈሩ ከጓዶቹ ከትግል አጋሮቹ በመሆን እያደራጁ“ድረስ” በተባለበት ግንባር ፈጥኖ እንዲደርስ አደረጉ። ውጊያው እየመረረ መጣ። እርሱና ጓደኞቹ ከሸዋ መራቤቴ ተነስተው ጠላትን እያሳደዱ እስከ ወሎው ራያ ቆቦ ድረስ በመዝመት ታላላቅ ተጋድሎዎችን ፈጸሙ፤ ጠላትን አሳፈሩ። ከዚያም ወደ ኤፌሶን አጣዬ በመመለስ፣ በሸዋ ምድር ባሉት ስፍራዎች ሁሉ እየዞሩ የፋኖን ክንድ የማጠናከር ስራቸውን ቀጠሉ።
የማይበገረው የ“7 ለ 70” ታሪክ ህዝባዊ ትግሉ መልክ ቀይሮ ከመደበኛው የብልፅግና ኃይል ጋር ግብግብ ውስጥ ሲገባ፣ የእነዚህ ጀግኖች ወታደራዊ አቅም እና ጥበብ በከፍተኛ ሁኔታ አደገ። ከጠላት እየማረኩ፣ እራሳቸውን እና ህዝባቸውን እያስታጠቁ፣ ስልታዊ በሆነ መንገድ አቅማቸውን ገነቡ። ስም ታሪክን ይወልዳል! ታላቁ አፄ ሚኒልክ በታሪክ ማህደር 7 ሆነው፣ የጠላት ኃይል ደግሞ በዛብህ 70 ሆኖ የመጣበትን እና የሸዋ አርበኞች ድል የተቀዳጁበትን ያንን አንጸባራቂ የገድል ታሪክ መሠረት በማድረግ፣ ብርጌዳቸውን “7 ለ 70” ብለው ሰየሙት።
የሹመት እና የኃላፊነት እርከኖች ትግሉ ከሻለቃ ወደ ብርጌድ ከዚያ ክፍለጦር እያደገ ሲመጣ፣ የዚህ አርበኛ ዝናው በቀለ ጀግና ሚናም ከፊት መስመር መሪነት እስከ ስልታዊ የጀርባ አጥንትነት ከፍ አለ፦ በሻለቃ ምስረታ ወቅት፦ የጀግናው የደመላሽ ሻለቃ የሎጂስቲክስ ኃላፊ በመሆን ጦሩን ያለምንም እንከን መገበ፣ አስታጠቀ። በብርጌድ እድገት ወቅት፦ የብርጌዱ ምክትል ሎጂስቲክስ በመሆን ሰፊ አቅም ፈጠረ።በክፍለጦር ደረጃ፦ ታላቁ የ“7 ለ 70 ክፍለጦር” በይፋ ሲመሰረት፣ መላውን ጦር የሚመራው የሎጂስቲክስ መምሪያ ዋና ኃላፊ ሆነ። በአሁኑ ወቅት፦ የጠላትን ውድቀት፣ የፋኖን አሸናፊነት እና የትግሉን እውነተኛ ገጽታ ለታሪክ እና ለዓለም የሚያበስር የክፍለጦሩ ሪፖርተር (ቃል አቀባይ/ደራሲ) በመሆን በትግሉ ግንባር ቀደምትነቱን ይዟል። ይቀጥላል.....
