Seblework Old Books Delivery ™📚
Kanalga Telegram’da o‘tish
« ሰብለ _ወርቅ የቆዩ ፥ መጽሐፍት መደበር » 📚 የልቦለድ 📚የፍልስፍና 📚 የታሪክ 📚 የስነ ልቦና 📚 መንፈሳዊ መጽሐፍ እንሸጣለን - እንገዛለን ፡፡ መጽሐፍትን በተለያዩ ዓለማት Delivery በታማኝነት እና በተቀላጠፈ ሁኔታ እናደርሳለን ፡፡ #ስልክ ቁጥር ፡- 0946523397 ይደውሉልን! @sebleold inbox 📥
Ko'proq ko'rsatish1 768
Obunachilar
+124 soatlar
+267 kunlar
+9230 kunlar
Postlar arxiv
የኔዋ ንጋት ኮኮብ ግን ከጎኔ ትጠፋለች ፡፡ወደ እኩለ ሌሊት ክንዴን ተንተርሳ እጉያዬ ላይ እንቅልፍ ሽልብ አድርጓታል ፡እኔ ግን መንፈሴ አልረጋጋ አለ ፡እንቅልፉም ራቀኝ ፡፡በልስላሴ እና በቀስታ ጸጉርዋን ፊትዋን እየዳሰስኩ ፡የኢስክ ኩለን ቀላይ በተመስጦ ፡በአድናቆት ዓይኖቸን ተክዬ አይ ጀመር ፡እንዳይነጋ የለም ፡መሬት ነጋ ፡፡
©የነበረው እንዳልነበረ 📚
+6
ሕይወትን በሆነ መንገድ ኖሬያታለሁ፥ እናም በሌላ ወይም ከዚህ ተቃራኒ በሆነ አኗኗር ልኖራት ይቻለኝ ነበር፡ ብዙ ነገር ሰርቻለሁ ሌሎች ብዙ ነገሮች ደግሞ አልሰራሁም ፡፡ይህንን ሠርቻለሁ .....ያኛውን ግ ን አልሰራሁም እና ምን ይጠበስ ..?
Albert Camus The stranger 🖤
+8
📖 ''ሕይወቴ''
ጸሐፊ - ደጃዝማች ወልደ ሰማዕት ገብረወልድ
ዘውግ - ግለታሪክ (Autobiography)
@sebleold inbox 📖📚
ኢየሱስ "የእግዚአብሔር ልጅ ነው" እጆቹ ሲዘረጉ ም ለመብረር የተዘጋጀ ንስር ይመስል ነበር ፡፡ የመጨረሻው ብርሃንም ከአይኖቹ ላይ ሲጠፉ ፡ እንኳን ፈገግታ ከከንፈሮቹ ላይ እንዳልሸሹ ፡በዓይኖቹ አይቻለሁ ፡፡ ፈገግታ ውንም ዛሬም ድረስ ሳስበው ክረምት አልቆ በጋ ሊጀመር ፡ሲል ያየዘውን ብሩህ ተስፋ የሰነቀ ዓይነት መስሎ ይታየኝ ነበር ፡፡ እንዴት ልግለፅላችሁ!?
ከአንደበቱ በሚወጡት ቃላት ውስጥ በረከት አለ ፡ድምጹም በብርዳማ ለሊት ሊሞቁት እንደሚደረብ መጎናጸፊያ ነው ፡፡
ኢየሱስ የሰው ልጅ 📚
©ካህሊል ጅብራን ❤️
"ከዚህ በኋላ ክርስቶስን በገንዘብ የሸጠው ሰው ላይ አልፈርድም።በደካሞችና በሰካራሞች ልብ ውስጥ ምን እንዳለ የሚያውቀው ፈጣሪ ነው።"ከአንድ ሰዓት በኋላ ወደ ሆቴሉ ስመለስ ጨቅላ ህጻን ያቀፈች ወጣት አየሁ። ሕፃኑ ስድስት ሳምንት ቢሆነው ነው። በዚያ ቅፅፈት ነበር ህፃኑ ለመጀመርያ ጊዜ ፈገግ ሲል እናቱ ያየችው። እናትየዋ በጥልቅ ስሜት ደጋግማ ስታማትብ አየኋትና ጠየቅኋት። "ፈጣሪ ከሰማይ ሆኖ ከልቡ የሚፀልይን አንድ ሃጢያተኛ የሚሰማውን ደስታ የሚያክል ሌላ ደስታ ቢኖር የህፃን ልጇን ፈገግታ ለመጀመርያ ጊዜ የምታይ እናት ልብ ውስጥ ያለ ደስታ ነው"አለቺኝ። የወጣቷ ሴት ንግግር ጥልቅ ነበር። በውስጥ መላውን የክርስትና አስተምህሮ ብቻ ሳይሆን በፈጣሪ እና በሰው ልጅ መካከል ያለውን የአባትና ልጅ የፍቅር ትስስር የሚገልፅ ነበር። በንግግሯ የክርስቶስን መሠረታዊ ሃሳብ መግለጿ ልቤን ነካው። ሊዮቭ ኒኮላዮቪች ሚሽኪን(ልዑሉ) ©Fydor ዶስቶቭስኪ 🖤📚
ሲራክ እስክንድርን፡ ትኩር ብሎ ሲመለከተው ከቆየ በኋላ «ለመሆኑ ስለምንድነው የምትፅፈው?» ብሎ ጠየቀው ፡፡
«ምን ማለትህ ነው?»
«ድርሰት እወዳለሁ»
ጥሩ ግን ድርሰት፡ ፍቅር ብቻውን በቂ አይደለም፡፡
«ድርሰት ተልዕኮም አላት ፡፡»
«ያንተ ድርሰት ተልዕኮ ምንድነው?»
«በድርሰትህ ምን ለመግለፅ ነው የምትፈልገው ?»
«ሀቅ ፡ውበት ፡በድርሰት ሌላ ምን የሚገለፅ ነገር አለ?»
«የማን ሀቅ፡ የማን ውበት?»
....
( በዓሉ ግርማ ፡ ደራሲው)
*
‹‹በገብርዬ የታማኝነት ስሜት በሕልም እንኳን መሸፈት ራሱ እንደ ክህደት የሚቆጠር ነበር፡፡ ይህንን ክህደት አንደ ደህና ነገር ለሰው ማውራት ደግሞ ከትዝብት ያለፈ ዓመፅ መስሎ ተሰማው፡፡ ሰው በሚጠላው ላይ ይሸፍታል፡፡ "የተበደለ ሰውም ቢያምፅ አይፈረድበትም፡፡" በሚወዱትና በሚታመኑት ላይ እንዴት ሲደረግ ይታሰባል? ገብርዬ ተራቅቆ ባይፈላሰፍም ማንም ሰው አንድ ጠቅላላ ሥርዓት መከተል እንደሚገባ ይሰማዋል፡፡ በጦር ሜዳ ደረቱን አስጥቶ ልቡን ሰጥቶ የሚዋጋውን ያህል አገር በመበጥበጥ፤ መንደር ለማመስ ለመዝረፍ ወይም ለመፈራትና ለመታወቅ የሚደረግ ሽፍትነትን በጣም ይጠላል፤ ይጠየፋል፤ ቴዎድሮስን ያመነበት ዋናው ምክንያትም ይኸው ነበር፡፡››
የታንጉት - ምስጢር ❤️
© ከብርሃኑ ዘርይሁን
