Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) – ኢሰመኮ
Kanalga Telegram’da o‘tish
EHRC is an independent NHRI tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.
Ko'proq ko'rsatish1 508
Obunachilar
+124 soatlar
+97 kunlar
+4430 kunlar
Postlar arxiv
በሴቶች መብቶች ዙሪያ መደበኛ ካልሆኑ የሴቶች አደረጃጀቶች ጋር የተካሄደ የግንዛቤ ማሳደጊያ ውይይት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሴቶች መብቶች ላይ ለሚሠሩ መደበኛ ያልሆኑ የሴቶች መብቶች አደረጃጀቶች የግንዛቤ ማሳደጊያ ውይይት በሰኔ 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አካሂዷል። ውይይቱ መደበኛ ያልሆኑ የሴቶች መብቶች አደረጃጀቶችን ዐቅም በማሳደግ ሥራቸውን ከሰብአዊ መብቶች መርሕ ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲያከናውኑ ለማስቻል ያለመ ነው፡፡
በመድረኩ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር በዞንና በወረዳ ያቋቋማቸው የበጎ ፈቃደኛ ኮሚቴ አመራሮች፤ ከአፋር፣ ከአማራ፣ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ከማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከኦሮሚያ፣ ከሲዳማ፣ ከሶማሊ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ እና ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የተወጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ጾታን መሠረት ያደረገ ጥቃትና የሰብአዊ መብቶች ምንነት፤ ለጥሰት ተጋላጭ በሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚቀርቡ አቤቱታዎች አቀባበል፤ የምርመራ ሥነ ሥርዓት መሠረታዊ መርሖች፣ እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የደረሰባቸውን ሴቶች እና ሕፃናት ቃለ-መጠይቅ የማድረግ ስልቶች እና የሥነ-ልቦና ጉዳትን ታሳቢ ባደረገ ምላሽ አሰጣጥ፤ እንዲሁም የአደረጃጀቶቹን አሠራር ለማጠናከርና ለመደገፍ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የመነሻ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
ተሳታፊዎች በየአካባቢያቸው የሚከሰቱ ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን እና በሥራ እንቅስቃሴያቸው የሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶችን አጋርተዋል። የአካባቢ ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብነት፣ መረጃዎችን በአግባቡ አለማደራጀትና የአሠራር ሥርዓት ክፍተቶች፣ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመቀበል ዐቅም ውስንነት፣ እንዲሁም በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ምላሽ አሰጣጥ ዙሪያ ውስንነቶች እንደሚታዩ ገልጸዋል።
የኢሰመኮ የሴቶች እና የሕፃናት መብቶች ኮሚሽነር አሸነፈች አበበ፤ ለመብቶች ጥሰት ተጋላጭ ለሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጥራት ያለው፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ የሕግ ድጋፍ ለማድረግ ብሔራዊ የነጻ የሕግ ድጋፍ ስትራቴጂን ለማስፈጸም የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን አጸድቆ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ መደበኛ ያልሆኑ የሴቶች አደረጃጀቶች የሚሰጧቸው የሕግ ድጋፎች በተለይም ለሴቶች እና ለሕፃናት መብቶች መከበር ወሳኝ መሆናቸውን አብራርተዋል። አክለውም እነዚህ አገልግሎቶች ይበልጥ ሊጠናከሩና ሰብአዊ መብቶች ተኮር ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=38402
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የሳምንቱ #HRConcept: የማሠቃየት ተግባር ተጎጂዎች መብት
...
የማሠቃየት እና ሌሎች የጭካኔ፣ ኢ-ሰብአዊ የሆነና ክብርን የሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት ለማስቀረት የተደረገ ስምምነት፣ አንቀጽ 14
- እያንዳንዱ አባል ሀገር በሕግ ሥርዓቱ ውስጥ የማሠቃየት ተግባር ሰለባ የሆነ ሰው መፍትሔ እንደሚያገኝ እንዲሁም በተቻለ መጠን የተሟላ ማገገሚያን ጨምሮ ተፈጻሚነት ያለው ፍትሐዊና በቂ ካሳ የማግኘት መብት እንዳለው ማረጋገጥ አለበት።
- ተጎጂው በደረሰበት የማሠቃየት ተግባር ምክንያት የሞተ እንደሆነ በእርሱ ኃላፊነት እና ድጋፍ ይተዳደሩ የነበሩ ሰዎች ካሳ ሊያገኙ ይገባል።
🔗 https://ehrc.org/?p=38394
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
ኦሮሚያ፦ በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ዙሪያ የተዘጋጀ የውትወታ መድረክ
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል፣ በጅማ እና ምሥራቅ ሐረርጌ ዞኖች እንዲሁም በጅማ ከተማ አስተዳደር በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ አተገባበር ላይ ባከናወናቸው የክትትል ሥራዎች፣ ግኝቶችና ምክረ ሐሳቦች ዙሪያ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም. የውትወታ መድረክ በጅማ ከተማ አካሂዷል። መድረኩ ኢሰመኮ ባከናወናቸው ክትትሎች የተለዩ መልካም ተሞክሮዎችን፣ ተግዳሮቶችን እና የተፈናቃዮች መብቶች የሚከበሩበትን ሁኔታ ለመገምገም እና ልምድ ልውውጥን ለማጎልበት ያለመ ነው።
በመድረኩ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን፤ ከኦሮሚያ ፕሬዚደንት ጽሕፈት ቤት፣ ከኦሮሚያ ቡሳ ጎኖፋ፣ ከክልሉ የዞንና የወረዳ ቡሳ ጎኖፋ ተወካዮች፤ ከመንግሥታዊ ተቋማት፣ ከሰብአዊ ድጋፍና ልማት አጋር ድርጅቶች፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እንዲሁም የጅማ እና የምስራቅ ሐረርጌ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ተወካዮች ተሳትፈዋል።
በውይይቱ በጅማ ከተማ ለበርካታ ዓመታት ሲኖሩ ለነበሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ፣ ቤት እና የመተዳደሪያ ድጋፎችን በመስጠት ተፈናቃዮች ወደ መደበኛ ኑሮ እንዲሸጋገሩ ማድረግን ጨምሮ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት በመንግሥት ተቋማት፣ በአካባቢው ማኅበረሰቦች እና በአጋር ድርጅቶች ቅንጅታዊ ጥረት የተከናወኑ ሥራዎች በመልካም ተሞክሮነት ተነስተዋል። በሌላ በኩል በዞኑ ከመልሶ ማቋቋም፣ ከመሠረታዊ አገልግሎቶች ተደራሽነት፣ ከመሠረተ ልማት እና ከማኅበራዊ ውህደት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመፍታት ሂደቱ በተሟላ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ማድረግ እንደሚገባ አጽንዖት ተሰጥቶታል።
በተጨማሪም በጅማ ከተማ አስተዳደር እና በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ላሉ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እና የተፈናቃዮችን መብቶች ለማስከበር ባለድርሻ አካላት በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ሰብአዊ ክብርን ባማከለ ሁኔታ በቅንጅት ለመሥራት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
በኢሰመኮ የትምህርት እና ስልጠና ዘርፍ ኮሚሽነር በዳሳ ለሜሳ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ በካምፓላ ስምምነት እና በሌሎች አግባብነት ባላቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መርሖች እና መስፈርቶች መሠረት መጠበቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። አክለውም ኢሰመኮ የተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በመከታተል፣ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች አፈጻጸምን በመገምገም፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ እንዲረጋገጥ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=38357
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
በሀገር ውስጥ በሴቶች እና በሕፃናት የመነገድ ድርጊትን አስመልክቶ የተካሄደ የምክክር መድረክ
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሀገር ውስጥ በሴቶች እና በሕፃናት የመነገድ ድርጊትን ለመግታት በሚወሰዱ ምላሾች ላይ ባከናወነው ክትትል የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች አተገባበርን አስመልክቶ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል። በመድረኩ ከፌዴራልና ከክልል ተቋማት የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከባሕር ዳር፣ ከሐዋሳ እና ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከምሥራቅ ሸዋ ዞን የተወጣጡ የፍትሕ ተቋማት፣ አስፈጻሚ አካላት፣ የሥራ ኃላፊዎች እና ተወካዮች ተገኝተዋል።
በውይይቱ በሴቶች እና በሕፃናት የመነገድ ድርጊትን ለመግታት የተካሄዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ጥናትና ምርምር፣ የሥራ እቅዶችና መመሪያዎች አተገባበር፣ የአቤቱታና የጥቆማ ሥርዓት፣ የወንጀል ምርመራ፣ የክስ አቀራረብና ተጠያቂነት እንዲሁም የተጎጂዎች የደኅንነት ጥበቃና መልሶ ማቋቋም የቅንጅት ሥራዎችን በተመለከተ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች አተገባበር እና ሌሎች በክትትሉ የተለዩ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መከናወናቸው፣ መደበኛ ባልሆኑ የሥራ ዘርፎች ላይ ክትትል የሚደረግ መሆኑ፣ የጥቆማ ሥርዓትን መዘርጋት መቻሉ እንዲሁም ከዐቅም ማሳደጊያ እና መልሶ ማቋቋም አንጻር የተወሰዱ እርምጃዎች በውይይቱ በአዎንታዊነት ተነስተዋል። በሌላ በኩል ከተደራጀ መረጃ አያያዝ፣ ከወንጀል ምርመራ እና ክስ አመሠራረት፣ እንዲሁም ከጥናት እና ምርምር ተግባራት አንጻር አሁንም ክፍተቶች መኖራቸው በአሳሳቢነት ተመላክቷል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች መልካም ጅምሮችን ማስቀጠልና በአሳሳቢነት የቀጠሉ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ በማኅበረሰብ አመለካከት ለውጥ ላይ በስፋት መሥራት፣ የሕግ ክፍተቶችን ማስተካከል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማሳደግና የባለድርሻ አካላትን ቅንጅት ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተጨማሪም ለፍትሕ አካላት ስልጠና መስጠት እንዲሁም በረቂቅ ደረጃ የሚገኘው የተጎጂዎች ፈንድና የፍልሰት ፖሊሲ ጸድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢሰመኮ የሴቶች እና የሕፃናት መብቶች ኮሚሽነር አሸነፈች አበበ በሀገር ውሰጥ በሴቶች እና ሕፃናት የመነገድ ድርጊትን ለመግታት የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የወጡ ሕጎችና የተቋቋሙ የማስተባባሪያ ማእከላት አበረታች ጅምሮች መሆናቸውን ገልጸው፤ ከችግሩ ስፋት አንጻር ሕጎችን በቁርጠኝነት መተግበር፣ ክፍተቶችን መሙላትና የባለድርሻ አካላትን የተቀናጀ አሠራር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል። አክለውም የተጀመሩ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=38348
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የሳምንቱ #HRConcept: የአካባቢ ደኅንነት መብት እና ልማት
...
የአፍሪካ የሰዎች እና የሕዝቦች መብቶች ቻርተር፣ አንቀጽ 24
ሁሉም ሕዝብ ለእድገቱ አመቺ የሆነ አጠቃላይ ተስማሚነት ያለው አካባቢ የማግኘት መብት አለው።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 44
ሁሉም ሰዎች ንጹሕና ጤናማ በሆነ አካባቢ የመኖር መብት አላቸው።
መንግሥት በሚያካሂዳቸው ፕሮግራሞች ምክንያት የተፈናቀሉ ወይም ኑሯቸው የተነካባቸው ሰዎች ሁሉ በመንግሥት በቂ እርዳታ ወደሌላ አካባቢ መዘዋወርን ጨምሮ ተመጣጣኝ የሆነ የገንዘብ ወይም ሌላ አማራጭ ማካካሻ የማግኘት መብት አላቸው።
🔗 https://ehrc.org?p=38278
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
respective institutions and committed to making the necessary adjustments to ensure accessibility of roads and buildings for persons with disabilities. Institutions further pledged to collaborate with relevant organizations of persons with disabilities and to strengthen implementation of accessibility standards. Authorities responsible for construction permits, regulation, and supervision further committed to strengthening enforcement and oversight mechanisms.
Roads and buildings must be designed, constructed, and supervised in strict compliance with national and international legal standards before they begin public service. Health facilities, banks, schools, and other public and private institutions are required to ensure full accessibility and provide inclusive services for persons with disabilities, while meaningfully incorporating their input in accessibility-related decisions.
EHRC strongly emphasizes the need for all respondent institutions to fully comply with the recommendations issued. It also calls on building construction permit and supervision authorities to effectively monitor and ensure the implementation of these recommendations by the institutions concerned.
EHRC’s Civil, Political and Socio-Economic Rights Commissioner, Dr. Abdi Jibril, stated that millions of persons with disabilities in Ethiopia continue to face the harsh reality of inaccessible buildings and roads, which are essential for their daily life. As a result, they are unable to fully enjoy their rights to health, education, work, equal access to public services, autonomy, and dignity on a daily basis. He emphasized that infrastructure is built at great cost and must be accessible to all without discrimination. Dr. Abdi further emphasized the importance of recognizing institutions that construct accessible buildings and thanked victims for bringing their lived experiences to light, as well as the respondent institutions for their commitments to take corrective action and bring about meaningful change.
🔗 https://ehrc.org/?p=38273
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
You can file a human rights violation complaint by calling our toll-free line at 7307.
Accessibility of Roads and Buildings for Persons with Disabilities Remains a Pressing Human Rights Concern
...
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) conducted a public hearing in Hawassa City on April 28 and 29, 2026, as part of its ongoing systemic human rights investigation into the accessibility of roads and buildings for persons with disabilities. The hearing focused on barriers affecting accessibility of roads, buildings, and public services for persons with disabilities. This follows an earlier public hearing held in Addis Ababa on December 26 and 27, 2024, which focused on accessibility of buildings as an initial component of the broader systemic investigation.
During the hearing, EHRC heard over 70 different complaints from 24 victims of alleged human rights violations, including 16 men and 8 women. Among the victims, 7 were blind, 15 had physical disabilities, and 2 were deaf. Nineteen victims presented their cases in person, one was heard confidentially, and four were represented by others.
The public hearing revealed that accessibility of roads and buildings remains a pressing human rights concern for persons with disabilities in Ethiopia. Lack of accessibility significantly limits the ability of persons with disabilities to exercise fundamental rights, including the rights to health, education, work, equality in accessing public services, freedom of movement, and the right to participate in cultural life. It also exposes persons with disabilities to significant threats affecting their physical, psychological, economic and social well-being.
EHRC’s systemic investigation was initiated in response to the structural, recurring and prevalent nature of these challenges across different parts of the country. Systemic human rights investigations help examine consistent patterns and trends of violations, rather than isolated incidents, as well as the underlying structural causes that enable recurring violations, with the aim of identifying widespread issues and recommending long-term reforms. Public hearings form part of this process by enabling victims to present their cases directly before responsible institutions and relevant governmental and non-governmental stakeholders.
Victims who testified during the hearing described inaccessible roads and buildings as major barriers to their daily lives, preventing them from fully exercising their human rights. They highlighted challenges in accessing health services, education, employment, and public services, as well as serious safety risks caused by inaccessible infrastructure. Particular concerns were raised regarding open manholes and drainage holes left unattended without proper signage following infrastructural works undertaken by Ethio Telecom, the Ethiopian Electric Utility, and other entities.
Victims further reported that inaccessible toilets and entrances in health facilities make it extremely difficult for persons with disabilities to seek medical care, forcing them to struggle even during sickness. Women with disabilities specifically testified to the difficulties faced during pregnancy and childbirth, describing degrading situations in health care facilities where no accessible procedures or accommodations were provided.
In addition, the inaccessibility of educational institutions was cited as a major barrier, denying persons with disabilities the opportunity to empower themselves through education and fully participate in social and economic life. Inaccessible workplaces similarly continue to exclude many persons with disabilities from formal employment, often forcing them into informal employment, unemployment, or dependency. Victims also described how inaccessible public institutions compel persons with disabilities to rely on the support of others to access essential services such as banking.
A total of 23 institutions against whom complaints were lodged as well as relevant government stakeholders participated in the public hearing as respondents. Following the testimonies, respondents acknowledged many of the concerns raised against their
Consultation on Ethiopia’s Draft Combined State Report on the implementation of the International Convention on the Elimination of All Forms of Racial Discrimination (ICERD)
...
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), in collaboration with the Ministry of Justice (MoJ), organized a consultative meeting on Ethiopia’s 17th to 25th combined draft state report on the implementation of the International Convention on the Elimination of Racial Discrimination (ICERD) on June 12, 2026, in Addis Ababa. The consultation aimed to ensure the stakeholders’ active participation in the report preparation process by providing their inputs and assessment of the state party’s performance in implementing its obligations under ICERD, including both positive developments and areas of concern and challenge.
The meeting brought together members of the state report drafting team (Inter-Ministerial Team), Civil Society Organizations (CSOs), line ministries, government agencies, and international organizations to ensure the report preparation process remains inclusive, participatory, and consultative. Participants were also familiarized with the Convention’s key features and the Concluding Observation adopted in 2009 by the (CERD), following its review of Ethiopia’s previous report submitted in 2008.
During the focus group discussions (FGDs), participants shared their feedback and concern on the draft report. The Inter-Ministerial Team and MoJ carefully recorded all inputs to strengthen the final report submission.
Mr. Yusuf Jemaw, Director of International Cooperation on Legal Affairs from the Ministry of Justice (MoJ), underscored the state party’s obligation to submit periodic reports to treaty bodies in a timely manner and highlighted the importance of the reporting process in assessing a country’s compliance with its human rights obligations. He also outlined the process used to prepare the overdue 17th to 25th combined ICERD state report and acknowledged the challenges encountered during its drafting.
Dr. Abdi Jibril, EHRC’s Commissioner for Civil, Political and Socio-economic Rights, emphasized the need to periodically discharge reporting obligations in order to assess the state of implementation of international human rights treaties, noting that Ethiopia’s report to the CERD has long been overdue. He further called upon CSOs and state institutions to actively participate in the preparation of the national report, while noting that civil society organizations may still choose to submit their own independent or complementary report on the implementation of the ICERD.
🔗 https://ehrc.org/?p=38246
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
You can file a human rights violation complaint by calling our toll-free line at 7307.
Memorandum of Understanding Signed for Joint Implementation of Inclusive Transitional Justice
...
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Transitional Justice Consortium-Ethiopia on June 8, 2026, to facilitate the realization of an inclusive and human rights-based transitional justice process. The agreement was signed by Berhanu Adello, Chief Commissioner of the EHRC, and Muluken Getachew, representative of the Consortium and Executive Director of the African Center for Transitional Studies. The agreement will contribute significantly to the EHRC’s ongoing efforts to implement a victim-centered transitional justice process through collaboration with the Consortium and other stakeholders.
Established by four local civil society organizations (CSOs)-: the African Center for Transitional Studies (ACT), the Partnership for Pastoralists Development (PAPDA), the Consortium for Ethiopian Civil Society Organizations of Peace (CESCOP), and the Horn Center for Democracy (HCD)-the Transitional Justice Consortium-Ethiopia aims to facilitate the active and collaborative participation of local CSOs in Ethiopia’s transitional justice process.
During the signing ceremony, Muluken Getachew, Executive Director of the African Center for Transitional Studies and representative of the Consortium, stated that the MoU will play a significant role in ensuring the inclusivity and success of the transitional justice process. He affirmed that they would strive to execute the CSO Mapping and Categorization project, authorized for the Consortium under the agreement, with greater diligence.
EHRC Chief Commissioner, Berhanu Adello, noted that the agreement will make a positive contribution towards implementing a victim-centered, inclusive, and human rights-based transitional justice process in Ethiopia. He added that the EHRC has consistently supported efforts to strengthen capacity building and participation in transitional justice in collaboration with CSOs, noting that this partnership will further strengthen the existing, long-standing cooperation with CSOs.
🔗 https://ehrc.org/?p=38215
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsforAll
You can file a human rights violation complaint by calling our toll-free line at 7307.
Awareness-Raising Forum for Members of the Inter-Religious Council of Ethiopia (IRCE)
...
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), in collaboration with the Inter-Religious Council of Ethiopia (IRCE), held an awareness-raising forum on June 11, 2026, in Addis Ababa. The forum aimed to enhance the awareness of religious leaders regarding the EHRC’s mandate and responsibilities as well as human rights monitoring principles, data collection methods, and early-warning systems.
Representatives from the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, the Ethiopian Catholic Church, the Evangelical Churches Fellowship of Ethiopia and the Ethiopian Seventh-day Adventist Church attended the forum.
Participants discussed human rights monitoring, early warning systems, the role of religious institutions in protecting and promoting human rights and how religious institutions can coordinate with the EHRC to address threats of human rights violations and resolve related issues.
Furthermore, the forum created conditions to operationalize the Memorandum of Understanding (MoU) signed on February 26, 2026, in Jimma City, which focuses on cooperation between the EHRC and the Inter-Religious Council of Ethiopia regarding human rights protection and peacebuilding.
Haji Mesud Adem, Deputy Secretary-General of the IRCE, stated that the responsibility of protecting human rights belongs to everyone and reaffirmed the Council’s readiness to collaborate with the EHRC to improve the human rights situation in the country.
Dr. Mizanie Abate, Deputy Chief Commissioner of the EHRC, emphasized the significant role that religious institutions play in upholding human rights and stated the need for continued collaboration on human rights awareness-raising, education, and early warning systems.
https://ehrc.org/?p=38153
#Ethiopia #HumanRightsforAll
You can file a human rights violation complaint by calling our toll-free line at 7307.
ማብራሪያ፦ አልቢኒዝም ያለባቸው ሰዎች (Persons with Albinism) ሰብአዊ መብቶች ጥበቃ
...
አልቢኒዝም ምንድን ነው? አልቢኒዝም ያለባቸው ሰዎች የሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው? አልቢኒዝም ያለባቸው ሰዎች ለሚያጋጥማቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ጥበቃ የሚያደርጉ የሕግ ማዕቀፎች የትኞቹ ናቸው? አልቢኒዝም ያለባቸውን ሰዎች መብቶች በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ ሊወሰዱ የሚገባቸው እርምጃዎች ምንድን ናቸው?
https://ehrc.org/?p=38120
#Ethiopia #HumanRightsforAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፦ የጤና መብት አተገባበር ላይ የተካሄደ ውይይት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ በካፋ እና ቤንች ሸኮ ዞኖች ያለውን የጤና መብት አተገባበር አስመልክቶ ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በቦንጋ ከተማ የውይይት መድረክ አካሂዷል። በውይይቱ ከካፋ እና ቤንች ሸኮ ዞን ጤና መምሪያዎች፤ ከጊምቦ፣ ገዋታ፣ ሺሾንዴ፣ ቢጣ፣ ዴቻ፣ ጨና እና ሰሜን ቤንች ወረዳዎች፤ ከቦንጋ ከተማ እና ከሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ጤና ጽሕፈት ቤቶች እንዲሁም በአካባቢዎቹ ከሚገኙ የጤና ተቋማት የተውጣጡ ተወካዮች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ኢሰመኮ በክልሉ ካፋ እና ቤንች ሸኮ ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች የጤና መብት አተገባበር ላይ፣ በተለይም በአካባቢዎቹ የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ምላሽ አሰጣጥን አስመልክቶ ባከናወነው ስልታዊ ምርመራ የተለዩ ግኝቶች እና ምክረ ሐሳቦች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በአካባቢዎቹ የወባ በሽታ ወረርሽኝ ስርጭት ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ የታቆሩ ውሃዎችን ማፋሰስ፣ የኬሚካል ርጭት፣ የክትባት እና አጎበር ስርጭት እንዲሁም ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በመከናወናቸው በአሁኑ ወቅት በበሽታው የመያዝ ምጣኔ ሊቀንስ መቻሉን ገልጸዋል። በሌላ በኩል በሽታውን ለማከም እና ለመቆጣጠር አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶች እና የሕክምና ቁሳቁስ እጥረት መኖሩ ተግዳሮት ሆኖ መቀጠሉን አንስተዋል።
የኢሰመኮ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚ መብቶች ሥራ ክፍል ኃላፊ ሃዊ አስፋው፤ መንግሥት ወረርሽኞችን በመከላከል፣ በማከም እና በመቆጣጠር እንዲሁም ለዜጎች የሕክምና እንክብካቤ በማቅረብ ረገድ ኃላፊነት እንዳለበት በአጽንዖት ገልጸዋል። አክለውም፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በሚገኙ ለወባ በሽታ ወረርሽኝ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች በሽታውን በዘላቂነት ለመቆጣጠር፣ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አካላት ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር የጀመሩትን የተቀናጀ ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
https://ehrc.org/?p=38132
#Ethiopia #HumanRightsforAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የሕፃናት ከጉልበት ብዝበዛ የመጠበቅ መብት
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 36(1) (መ)
ማንኛውም ሕፃን ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፤ በትምህርቱ፣ በጤናውና በደኅንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎችን እንዲሠራ ያለመገደድ ወይም ከመሥራት የመጠበቅ መብት አለው።
ዓለም አቀፉ የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 32(2)(ሀ-ሐ)
ተዋዋይ ሀገራት በተለይ፡-
- ዝቅተኛ የቅጥር ዕድሜን ወይም ዕድሜዎችን ይወስናሉ፤
- የሥራ ሰዓትንና የቅጥር ሁኔታዎችን በተመለከተ ተገቢውን ደንብ ያወጣሉ፤
- ይህ አንቀጽ በሚገባ በሥራ ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ ተገቢ ቅጣቶችን ወይም ሌሎች ክልከላዎችን ያስቀምጣሉ።
https://ehrc.org/?p=38110
#Ethiopia #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የሳምንቱ #HRConcept: የሕፃናት ከጉልበት ብዝበዛ የመጠበቅ መብት
...
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 36(1) (መ)
ማንኛውም ሕፃን ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፤ በትምህርቱ፣ በጤናውና በደኅንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎችን እንዲሠራ ያለመገደድ ወይም ከመሥራት የመጠበቅ መብት አለው።
ዓለም አቀፉ የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 32(2)(ሀ-ሐ)
ተዋዋይ ሀገራት በተለይ፡-
- ዝቅተኛ የቅጥር ዕድሜን ወይም ዕድሜዎችን ይወስናሉ፤
- የሥራ ሰዓትንና የቅጥር ሁኔታዎችን በተመለከተ ተገቢውን ደንብ ያወጣሉ፤
- ይህ አንቀጽ በሚገባ በሥራ ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ ተገቢ ቅጣቶችን ወይም ሌሎች ክልከላዎችን ያስቀምጣሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=38110
#Ethiopia #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የማኅበረ ሥነ-ልቦና ጉዳት ያለባቸው ሰዎች የጤና መብት ላይ የተካሄደ የምክክር መድረክ
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የማኅበረ ሥነ-ልቦና ጉዳት (psychosocial disability) ያለባቸው ሰዎች የጤና መብት ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ባደረገው የሰብአዊ መብቶች ክትትል በተለዩ ግኝቶች እና በቀረቡ ምክረ ሐሳቦች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የምክክር መድረክ አካሂዷል። ክትትሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች ሥር በሚገኙ 13 የመንግሥት ሆስፒታሎች እና የግል የሕክምና ማእከላት ላይ የተካሄደ ሲሆን፤ ዋና ዓላማውም እንደ ከባድ ድብርት፣ ባይፖላር ዲስኦርደር፣ ስኪዞፌርንያ፣ የጭንቀት ሕመም ባሉ የረዥም ጊዜ የአእምሮ ጤና ጉዳቶች ምክንያት ለተግባር ውስንነቶች (functional limitations) እና ለማኅበራዊ እንቅፋቶች (social barriers) የተጋለጡ ሰዎችን የሕክምና አገልግሎት ሁኔታዎችን ለመለየት እንዲሁም የመፍትሔ ሐሳቦችን ለማመልከት ያለመ ነው።
በምክክር መድረኩ ላይ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ፣ ከትምህርት እና ከጤና ሚኒስቴር፤ ክትትሉ ከተካሄደባቸው ክልሎች የጤና፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮዎች፣ ከአካል ጉዳተኞች ማኅበራት እና የጤና ተቋማት የተወከሉ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ ኢሰመኮ በክትትሉ በለያቸው ቁልፍ እመርታዎች፣ አሳሳቢ ጉዳዮች እና ምክረ ሐሳቦች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። ተሳታፊዎች በማኅበረ ሥነ-ልቦና ጤና አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን፣ በተቋሞቻቸው እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን እና የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች አቅርበዋል።
በክትትሉ ከተለዩ አዎንታዊ ሁኔታዎች መካከል የአእምሮ ሕክምና ቀደም ካሉት ዓመታት በተለየ በአንድ ሆስፒታል ሳይወሰን በተለያዩ ሪፈራል እና የማስተማሪያ ሆስፒታሎች ውስጥ እየተሰጠ መሆኑ፣ ታካሚዎች የአእምሮ ሕክምናን በቅርበት እንዲያገኙ መደረጉ፣ ክትትል በተደረገባቸው ተቋማት የሚገኙ የሕክምና ባለሙያዎች ታካሚዎችን በመልካም ሥነ ምግባር እና አያያዝ የሚያስተናግዱ መሆኑ እንዲሁም በመንግሥት የሕክምና ተቋማት ከሱስ ሕክምና ውጪ ያሉ የአእምሮ ሕክምናዎች እና መድኃኒቶች በጤና መድኅን ሽፋን ለተጠቃሚው እንዲሰጡ መደረጉ ተጠቃሽ ናቸው።
በሌላ በኩል ክትትሉ በተከናወነባቸው የመንግሥት የጤና ተቋማት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የመድኃኒት እጥረት መኖሩ፣ እንደ የኤሌክትሪክ ንዝረት ሕክምና (Electroconvulsive therapy) ያሉ አስፈላጊ የሕክምና ዘዴዎችና ቴክኖሎጂዎች በበቂ ያልተሟላ መሆኑ፣ በሀገሪቱ ለአእምሮ ሕክምና ተጠቃሚ ሕፃናት ተብሎ የተዘጋጀ የመድኃኒት መጠን (ዶዝ) እና የመድኃኒቶች እጥረት መኖሩ፣ በግጭት ዐውድ ውስጥ በሚገኙ ክልሎች የማኅበረ ሥነ-ልቦና ሕክምና ፈላጊ ታካሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩና አገልግሎት የሚሰጡ ባለሙያዎች ቁጥር ውስን መሆኑ እና በጤና ተቋማት የሚስተዋለው ከፍተኛ የበጀት ውስንነት አሳሳቢ ጉዳዮች መሆናቸው ተጠቅሷል።
በምክክሩ ማጠቃለያ ላይ ተሳታፊዎች በኢሰመኮ የቀረቡ ምክረ ሐሳቦችን ለመፈጸም የሚያስችል የድርጊት መርኃ ግብር አዘጋጅተዋል።
የኢሰመኮ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር መሐመድ አሕመድ፣ ሰዎች ሕይወታቸውን በአግባቡ እንዲመሩ፣ እንዲማሩ፣ እንዲሠሩ እና ለማኅበረሰባቸው የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ የአእምሮ ጤና መሠረታዊ መነሻ መሆኑን ጠቁመው፤ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ለአእምሮ ጤና ሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት፣ ተገኝነትና ጥራት ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ አሳስበዋል።
https://ehrc.org/?p=38082
#Ethiopia #humanrightsforall
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማሳደጊያ ዐውደ ጥናት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሽግግር ፍትሕ ጽንሰ ሐሳቦች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማሳደጊያ ዐውደ ጥናት ግንቦት 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አካሂዷል። በዐውደ ጥናቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ፣ የሽግግር ፍትሕ ፍኖተ ካርታ፣ የሽግግር ፍትሕ ሂደቱን ለመተግበር የተዘጋጁ ረቂቅ ሕጎች፣ በሽግግር ፍትሕ ሂደት ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ስላላቸው ሚና እንዲሁም በዚህ ረገድ ኢሰመኮ እያከናወናቸው ስላሉ ተግባራት ገለጻዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በውይይቱ ወቅት የሽግግር ፍትሕ ዋና ምሰሶዎች የሆኑት ተጠያቂነት፣ እውነትን ማፈላለግ፣ የተጎጂዎች ካሳ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች ለፍትሕ፣ ለእርቅ እና ለዘላቂ ሰላም ያላቸው አስተዋጽዖ ላይ ውይይት ተደርጓል። በተጨማሪም የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ ውጤታማ እና ተዓማኒ እንዲሆን ግልጽ የትግበራ ሥርዓቶች፣ የተቋማት ቅንጅት እና ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋማት መኖራቸው ለሽግግር ፍትሕ ውጤታማነት ወሳኝ መሆናቸው፤ ረቂቅ ሕጎቹም ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕጎችና መርሖች ጋር ተጣጥመው ሊዘጋጁ እንደሚገባ እንዲሁም ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት በሂደቱ ላይ የሚያከናውኑት የክትትል ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች ዐውደ ጥናቱ በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረጉን ገልጸው ሂደቱን በውጤታማነት ለመደገፍ የሚያስችል ጠንካራ ተቋማዊ ዐቅምን ለመገንባት መሰል ተከታታይ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠናዎች አስፈላጊ መሆናቸው ተገልጿል።
ኢሰመኮ የሠራተኞቹን ዐቅም ለማጎልበት መሰል የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠናዎችን በቀጣይነት እንደሚያካሂድ እንዲሁም የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ውጤታማ፣ ተዓማኒ እና ሰብአዊ መብቶችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን ለማድርግ አበክሮ እንደሚሠራ አስታውቋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=38024
#Ethiopia #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
ጋዜጣዊ መግለጫ፡ ኦሮሚያ፦ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የደረሰውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተመለከተ
መንግሥት ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን ሊወስድ ይገባል
. . . . .
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ክትትል እና ምርመራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢሰመኮ ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በአካባቢው በአካል በመገኘት ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ባሰባሰባቸው መረጃዎችና ማስረጃዎች ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ታጣቂ ቡድን በፈጸመው ጥቃት የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ለማረጋገጥ ችሏል።
ኢሰመኮ በምርመራ ሂደቱ እንዳረጋገጠው በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው በመሰማራታቸው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን እና በተሰማሩ የጸጥታ አካላት መካከል ግጭት ተፈጥሯል። ግጭቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ላይ ታጣቂ ቡድኑ ባደረሰው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ባልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም ቁጥራቸው ለጊዜው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መድረሱን፣ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፤ ቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በድለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ፣ በነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋ መፈጸሙን እንዲሁም ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አረጋግጧል።
ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡ ይታወሳል። መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች እና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት ጥቃት በተፈጸመባቸው አካባቢዎች የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ እና ሰላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ ነዋሪዎችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት የመመለስ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም በመንግሥትና በሌሎች አጋር አካላት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በቂ የሆነ የአስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኢሰመኮ ያሳስባል። በሌላ በኩል ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ይፋ የሚያደርግ መሆኑን እየገለጸ፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት እንዲፈጠር የማነሳሳት ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀርባል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ኢሰመኮ በዜጎች ላይ ለደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘኑን ገልጸው በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ አክለውም መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ያከናወናቸው ተግባራት መቀጠል ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም ጊዜ የጸጥታ ሥጋት ባለባቸው አካባቢዎች ሁሉ በቂ የጸጥታ ኃይሎች በመመደብና ተመሳሳይ ጥቃቶችን የመከላከል ሥራ በመሥራት የነዋሪዎች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነት እና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ፣ ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ እንዲሁም ሁሉም አካላት የተፈጠሩ ችግሮችን ከማውገዝ ባሻገር ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ መግለጫዎች እና ድርጊቶች እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል።
🔗https://ehrc.org/?p=37997
hashtag#Ethiopia📷 hashtag#HumanRightsForAll
በአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ አገልግሎት የማግኘት መብት ላይ የተካሄደ ውይይት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ4 ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ 13 የተሐድሶ ማእከላት እና የጤና ተቋማት ላይ የአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ አገልግሎት እና አጋዥ መሣሪያዎች የማግኘት መብትን አስመልክቶ ባካሄደው የሰብአዊ መብቶች ክትትል የተለዩ ግኝቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ውይይት አካሂዷል። ክትትሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ትግራይ ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ የተሐድሶ ማእከላት እና የሪፈራል ሆስፒታሎች ላይ የተከናወነ ነው፡፡
በውይይቱ ላይ የጤና፣ የትምህርት እና የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የሕክምና ተቋማት፣ የአካል ተሐድሶ ማእከላት፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩም የተሐድሶ አገልግሎት ምንነት እንዲሁም የተሐድሶ አገልግሎትን የተመለከቱ ዓለም አቀፍ እና ሀገራዊ የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፎች ላይ ገለጻ ተደርጓል። በተጨማሪም በኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል የተለዩ አዎንታዊና አሳሳቢ ሁኔታዎች ቀርበዋል። የተሐድሶ አገልግሎትን የተመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች መኖራቸው፣ አንዳንድ አጋዥ መሣሪያዎችና ቁሳቁሶች በሀገር ውስጥ መመረት መጀመራቸው፣ የዘርፉ ባለሙያዎች ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተከተለ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ፣ የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት በንጽጽር የተሻለ የአጋዥ መሣሪያዎች አቅርቦት ያለው መሆኑ በአዎንታዊ ሁኔታ ተጠቅሰዋል።
በአንጻሩ የተሐድሶና አጋዥ መሣሪያዎች አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አነስተኛ መሆን፤ ሩቅና ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ የገጠር አካባቢዎች ተደራሽ አለመሆን፤ በዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የሰው ኃይል እጥረት መኖር እና የተሐድሶ አገልግሎት ትምህርት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አለመሰጠት በአሳሳቢነት የተለዩ ነጥቦች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአጋዥ መሣሪያዎች፣ ቴክኖሎጂዎች እና ማሽኖች አቅርቦት እጥረት፤ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ መሣሪያዎችና ማሽኖች ያረጁና የተበላሹ መሆናቸው፤ የተሐድሶ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ምቹ አለመሆን፤ ለሁሉም የአካል ጉዳት ዓይነቶች አገልግሎት የሚሰጥ ሁሉን አቀፍ (comprhensive) የተሐድሶ አገልግሎት አለመኖር፤ ዘርፉ የሚመራበት የፖሊሲ ማዕቀፍና የድርጊት መርኅ ግብር አለመኖር እና ከፍተኛ የበጀት እጥረት መሻሻል የሚገባቸውና በአሳሳቢነት የተጠቀሱ ጉዳዮች ናቸው።
የውይይቱ ተሳታፊዎች የተሐድሶ አገልግሎት የሚፈልገው የሕዝብ ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ የተሐድሶ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት በመሣሪያና በሰው ኃይል እንዲደራጁ፣ ዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት፣ መንግሥት የተሐድሶ አገልግሎት ፖሊሲ በመቅረጽ ለዘርፉ ትኩረት እንዲሰጥ እና በቂ በጀት እንዲመድብ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት እንዲያከናውን ጠይቀዋል።
የኢሰመኮ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር መሐመድ አሕመድ የአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ እና አጋዥ መሣሪያዎች አገልግሎት የማግኘት መብት እንዲረጋገጥ ኢሰመኮ የሚያከናውናቸውን የክትትል እና የውትወታ ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ አክለውም፣ በክትትል ግኝቶቹ መነሻነት የቀረቡ ምክረ ሐሳቦች እንዲፈጸሙ፣ በዘርፉ እያጋጠመ ያለው የአጋዥ መሣሪያዎችና የሰው ኃይል አቅርቦት እጥረት እንዲቀረፍ፣ የተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ እንዲሻሻል እንዲሁም ተቋማት ተደራሽ እንዲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ እና በትብብር እንዲሠሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=37923
#Ethiopia #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
በአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ አገልግሎት የማግኘት መብት ላይ የተካሄደ ውይይት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ4 ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ 13 የተሐድሶ ማእከላት እና የጤና ተቋማት ላይ የአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ አገልግሎት እና አጋዥ መሣሪያዎች የማግኘት መብትን አስመልክቶ ባካሄደው የሰብአዊ መብቶች ክትትል የተለዩ ግኝቶች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ውይይት አካሂዷል። ክትትሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ትግራይ ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ የተሐድሶ ማእከላት እና የሪፈራል ሆስፒታሎች ላይ የተከናወነ ነው፡፡
በውይይቱ ላይ የጤና፣ የትምህርት እና የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የሕክምና ተቋማት፣ የአካል ተሐድሶ ማእከላት፣ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት እንዲሁም ሌሎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩም የተሐድሶ አገልግሎት ምንነት እንዲሁም የተሐድሶ አገልግሎትን የተመለከቱ ዓለም አቀፍ እና ሀገራዊ የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፎች ላይ ገለጻ ተደርጓል። በተጨማሪም በኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል የተለዩ አዎንታዊና አሳሳቢ ሁኔታዎች ቀርበዋል። የተሐድሶ አገልግሎትን የተመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች መኖራቸው፣ አንዳንድ አጋዥ መሣሪያዎችና ቁሳቁሶች በሀገር ውስጥ መመረት መጀመራቸው፣ የዘርፉ ባለሙያዎች ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተከተለ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ፣ የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት በንጽጽር የተሻለ የአጋዥ መሣሪያዎች አቅርቦት ያለው መሆኑ በአዎንታዊ ሁኔታ ተጠቅሰዋል።
በአንጻሩ የተሐድሶና አጋዥ መሣሪያዎች አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አነስተኛ መሆን፤ ሩቅና ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ የገጠር አካባቢዎች ተደራሽ አለመሆን፤ በዘርፉ ከፍተኛ የሆነ የሰው ኃይል እጥረት መኖር እና የተሐድሶ አገልግሎት ትምህርት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አለመሰጠት በአሳሳቢነት የተለዩ ነጥቦች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአጋዥ መሣሪያዎች፣ ቴክኖሎጂዎች እና ማሽኖች አቅርቦት እጥረት፤ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ መሣሪያዎችና ማሽኖች ያረጁና የተበላሹ መሆናቸው፤ የተሐድሶ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ምቹ አለመሆን፤ ለሁሉም የአካል ጉዳት ዓይነቶች አገልግሎት የሚሰጥ ሁሉን አቀፍ (comprhensive) የተሐድሶ አገልግሎት አለመኖር፤ ዘርፉ የሚመራበት የፖሊሲ ማዕቀፍና የድርጊት መርኅ ግብር አለመኖር እና ከፍተኛ የበጀት እጥረት መሻሻል የሚገባቸውና በአሳሳቢነት የተጠቀሱ ጉዳዮች ናቸው።
የውይይቱ ተሳታፊዎች የተሐድሶ አገልግሎት የሚፈልገው የሕዝብ ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ የተሐድሶ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት በመሣሪያና በሰው ኃይል እንዲደራጁ፣ ዘርፉ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት፣ መንግሥት የተሐድሶ አገልግሎት ፖሊሲ በመቅረጽ ለዘርፉ ትኩረት እንዲሰጥ እና በቂ በጀት እንዲመድብ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በስፋት እንዲያከናውን ጠይቀዋል።
የኢሰመኮ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር መሐመድ አሕመድ የአካል ጉዳተኞች የተሐድሶ እና አጋዥ መሣሪያዎች አገልግሎት የማግኘት መብት እንዲረጋገጥ ኢሰመኮ የሚያከናውናቸውን የክትትል እና የውትወታ ሥራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ አክለውም፣ በክትትል ግኝቶቹ መነሻነት የቀረቡ ምክረ ሐሳቦች እንዲፈጸሙ፣ በዘርፉ እያጋጠመ ያለው የአጋዥ መሣሪያዎችና የሰው ኃይል አቅርቦት እጥረት እንዲቀረፍ፣ የተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ እንዲሻሻል እንዲሁም ተቋማት ተደራሽ እንዲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያበረክቱ እና በትብብር እንዲሠሩ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=37923
#Ethiopia #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
