ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish672
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+37 kun
-130 kun
Postlar arxiv
✨✨✨🍂🍂✨🍂🍂✨🍂🍂
ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስን የፊቱን ውበት ተመልክቶ ልሔድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ አለ :: ቅዱስ ጴጥሮስም በደብረታቦር በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው ብሎ የአምላኩን ፊት ዘወትር እያየ ሊኖር ተመኘ::
አረጋዊው ስምኦንም ከድንግል እቅፍ ክርስቶስን ተቀብሎ መለኮታዊ ውበቱን ከተመለከተ በኃላ "ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና " እንደ ቃልህ ባርያህን አሰናብት ብሎ ዘወትር የአምላኩን ውበት ወደ ሚያይበት ሊሔድ ተቻኮለ : (ሉቃስ 2:30-31፤ ) ፤:
✨✨🍂🍂
ሰማእታት ለአንድ ነፍሳቸው ሳይራሩ ደማቸውን የሚያፈሱት ከፊታቸው ከተደቀነው ሰይፍ ጀርባ የክርስቶስ መልኩ ስለሚታያቸው ነው :: መናንያንም ከዓለም ወጥመድ አምልጠው በባዕታቸው የሚያጸኑት የክርስቶስ የፊቱ ውበት ጎልቶ ስለሚታያቸው ነው::
አይሁድ ክርስቶስን ዓይተውታል ነገር ግን ያዩት በሥጋዊ ዓይናቸው እንጂ በልባዊ ዓይናቸው ስላልሆነ ብዙ ነቢያት እና ጻድቃን ፊቱን ሊያዩት የተመኙትን አምላክ ከፊታችን ዘወር በልልን አሉት:: የልቡናቸው ዓይን በጥላቻ ስለታወረ የክርስቶስ መለኮታዊ ውበቱ ሊታያቸው አልቻለም ::
✨✨🍂🍂
አንድ ሰው የልቡ ዓይን በርቶ የክርስቶስን መልክ አንድ ጊዜ ማየት ከቻለ ከእርሱ በፊት ዓይቶ ያደነቃቸው የዓለም ውበቶች በሙሉ ከንቱ ይሆኑለታል:: ቅዱስ ባስልዮስ "የዓለም ውበት የሚማርከህ የክርስቶስን የመለኮቱን የውበት ፀዳል ስላለየህ " ነው ይላል::
የኛ አባቶች ሲመርቁ "እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ " ይላሉ :: ይህ እንዴት ያለ ምርቃት ነው ? እግዚአብሔር ፊቱን ሲያበራልን እንደ ጴጥሮስ "ለእኛ በዚህ መሆን መልካም ነው " ብለን በአማናዊቷ ደብረታቦር በቅድስት በቤተክርቲያን ጸንተን እንኖራለን :: እንደ አረጋዊው ስምኦን የሞት ፍርሐታችን ተገፎ "ዓይኖቼ ማዳንህን ዓይተዋል እና ባርያን አሰብናብት " ብለን ሞታችንን እንለምናለን:: እግዚአብሔርን ፊቱን ሲያበራልን በዓለም የምንኖር እንኳን ቢሆን ከኃጢአት ዓለም እንሰዳደላን::
እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልን !📝ዲ/ን ዶ/ር ዳዊት ከበደ ✨✨✨🍂🍂✨🍂🍂✨🍂🍂
Baga bara barnotaa 2018tiif issin gahe!
"Ati garuu isa barsiifamte, cimsitees itti amante sana eenyufa'i irraa akka barte waan beektuuf, isatti qabamii jiraadhu!" 2ffaa Ximo 3÷14Akka bara darbeeti mani barumsaa sanbata kenyaa barumsaa afuraa bara kanaafis barsisudhaaf qophi isaa xumurre isiin baratota galmesaa jiraa. Bara kanaas afaan lachun afaan orommo fi afaan amaaraa barsisudhaaf baratotaa haraa fi baratota turan kutaa 1-9faatii barsisuuf baratota galmesaa jira. Galma' baradhaa! Bakka galmee 👉Yerro hundaa sa'atti 10:00 iraa kaase waltaji irrati, galma mana barumsaa sanbatichaati fi mana kitaabati 👉Sa'aatti hojjitin mana gurgurtaa meshaale qulqullu M/B/sanbatichaati 👉 Sa'aati barbaadan bakka jirtaan iraa linkii armaan gadditin( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 ) galmaa'u ni dandessan Dabalataaf 👉0968903347 👉0998646565 👉0938117125
እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!
"አንተ ግን በተማርበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር!" ፪ኛ ጢሞ ፫፥፲፬እነሆ ዘንድሮም እንደአምናው በሰ/ት/ቤቱ የሚሰጠው ተከታታይ መንፈሳዊ ትምርት ለመስጠት ዝግጅታችንን ጨርሰን ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ እንገኛል። በሁለቱም ቋንቋዎች በአፋን ኦሮሞና በአማርኛ ከ1-9ኛ ክፍል ነባርና አዲስ ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል ይምጡና ይመዝገቡ ይማሩ! የመመዝገቢያ ቦታ 👉ዘወትር ቀን ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአውደ ምህረት፣ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽና ቤተ መጽሐፍት 👉ሁሌም በስራ ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ ነዋየ ቅዱሳት መሸጫ 👉 በፈለጉት ሰዓት ባሉበት ሆነው በሚከተለው ሊንክ በመግባት በonline መመዝገብ ይችላሉ( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 ) ለበለጠ መረጃ 👉0968903347 👉0998646565 👉0938117125
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
💐💐💐💐💐💐💐
አይቴ ሀሎ ንጉሠ እስራኤል ዘተወልደ፤
ከመ ነሀብ ሎቱ አምኃ ወሰጊደ፤
እንዘ ይብሉ ሰብአ ሰገል ሰሚዖ ገሃደ፤
ሄሮድስ አሜሃ በእሳተ ቅንዓት ነደ፤
ከመ ይቅትሉ ሕፃናተ ወኢያትርፉ አሐደ፤
እስከ ቤተልሔም እምገሊላ ሐራሁ አዖደ። (ሰቆቃወ ድንግል ቁጥር 2)
ትርጉም ፦ እጅ መንሻ እናቀርብለትና እንሰግድለት ዘንድ የተወለደው የእስራኤል ንጉሥ ወዴት አለ? እያሉ የጥበብ ሰዎች ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። ያን ጊዜም ንጉሥ ሄሮድስ ይህን ሰምቶ “ዘውድ እና ዙፋኔን ሊነጥቀኝ የሚሻ ንጉሥ ተወልዷልን? ” ብሎ ልቡ በቅናት እሳት ነደደ። በቤተልሔም ያሉ ዕድሜያቸው ከኹለት ዓመት በታች የኾኑ ሕፃናትን አንድ ስንኳ ሳያስቀሩ ይገድሏቸው ዘንድ ከገሊላ ጀምሮ እስከ ቤተልሔም ድረስ ጭፍሮቹን ላከ። ማቴ 2 ፥ 1 - 18
🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐
🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐
💐ሥርዓተ ማሕሌት ዘዳግማይ ዓመት🌹
🌹ዘመነ ጽጌ ዘቀዳማይ ሰንበት💐
💐አመ ፪ ለጥቅምት በዓለ ታዴዎስ🌹
🌹ሐዋርያ ወዕረፍቱ ለአባ ሕርያቆስ💐
🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐
🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐🌹💐
ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምዕ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውዐከ ፍጡነ ስምዐኒ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ በአሐቲ ቃል።
✨ነግሥ (መልክዐ ሥላሴ)✨ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡
✨✨ዚቅ✨✨ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት ኀበ ቀደሳ ወአክበራ ለሰንበት ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት ኀበ ባረከ ዓመተ ጻድቃን ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት ኀበ ምድረ ርስት ጽዕዱት ወብርህት ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት ምድረ ርስት ምንባር ለጻድቃን ማኅደር። (ዓዲ ዚቅ) ኀበ ጸገየ ወይን:ወፈረየ ሮማን:ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት:ዬዬዬ:ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት:ውስተ ገነት ብሂል ውስተ ርስቶሙ ለኲሎሙ: ሐዋርያት ብሂል።
🌹የማሕሌተ ጽጌ መግቢያ💐ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት፤ ተሠርገወት ምድር፤ 🌹በኅብረት ኹሉም🌹 በሥነ ጽጌያት፤ ለመርዓዊሃ ትብሎ መርዓት፤ ወልድ እኁየ ወረደ ውስተ ገነት።
🌹ማሕሌተ ጽጌ💐ጽጌ አስተርአየ ሠሪጾ እምዓጽሙ፤ ለዘአምኀኪ ጽጌ ለገብርኤል ምስለ ሰላሙ፤ ወበእንተዝ ማርያም ሶበ ሐወዘኒ ጣዕሙ፤ ለተአምርኪ አኀሊ እሙ፤ ማሕሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፡፡
✨✨ወረብ✨✨መዓዛ ጣዕሙ ለተአምርኪ ሶበ ሶበ ሐወዘኒ፨ ወበእንተዝ ማርያም አሐሊ ለተአምርኪ።
✨✨ዚቅ✨✨ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ናሁ አስተርአየ ጽጌ መርዓቱኒ ትቤ ወልድ እኁየ ይምዕዝ ከርቤ [ና] ዕንባቆም ነቢይ ግብረ ምግባሩ ለወልድ አንከርኩ ይቤ [ና] ንጉሠ ሰላም ክርስቶስ ዐቢይ ልዕልናከ ወመንክር ስብሐቲከ ለዕረፍት ሰንበተ ሠራዕከ፤
🌹ማሕሌተ ጽጌ💐እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፤ አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፤ ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፤ ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፤ ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ
✨✨ወረብ✨✨እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ጸዓዳ ወቀይሕ፨ አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ ሠናይትየ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ።
✨✨ዚቅ✨✨ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናይትየ እንተ ሐዋርያት ይሴብሑኪ መላእክት ይትለአኩኪ ፃኢ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት
🌹ማሕሌተ ጽጌ💐ሰዊተ ስርናዩ ለታዴዎስ ወለበርተሎሜዎስ ወይኑ፤ እንተ ጸገይኪ አስካለ በዕለተ ተከለኪ እደ የማኑ፤ ማርያም ለጴጥሮስ ጽላሎቱ ወለጳውሎስ ሰበኑ፤ ብኪ ምውታን ሕያዋነ ኮኑ፤ ወሐዋርያት መላእክተ በሰማይ ኰነኑ።
✨✨ወረብ✨✨ማርያም ለጴጥሮስ ጽላሎቱ ጽላሎቱ ወለጳውሎስ ሰበኑ፨ ወሐዋርያት መላእክተ መላእክተ በሰማይ ኰነኑ።
✨✨ዚቅ✨✨ኦ መድኃኒት ለነገሥት ማኅበረ ቅዱሳን የዓውዱኪ ነቢያት የዓኵቱኪ ወሐዋርያት ይዌድሱኪ እስመ ኪያኪ ኀርየ ለታዕካሁ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ፤ መላእክት ይኬልሉኪ ጻድቃን ይባርኩኪ አበው ይገንዩ ለኪ እስመ ኪያኪ ኀርየ ለታዕካሁ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ።
🌹ማሕሌተ ጽጌ💐ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ፤ ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤ አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፤ አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡
✨✨ወረብ✨✨ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ፨ አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ።
✨✨ዚቅ✨✨ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወስብሕት በሐዋርያት አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ ወትምክሕተ ቤቱ ለእስራኤል።
🌹ማሕሌተ ጽጌ💐ቅዳሴኪ ማርያም ጸገየ መለኮተ፤ ወፈረየ ብኪ ለቅዱሳን ቅድሳተ ፤ ለላዕካኒሁ እምግዘት ከመ የሀቡ ፍትሐተ፤ አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኃይላተ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኲተ፤ ወለማይኒ ረሰዮ ኅብስተ።
✨✨ወረብ✨✨አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኃይላተ ዐበይተ ኃይላተ፨ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኵተ።
✨✨ዚቅ✨✨ኦ እግዚኦ በከመ አሜሃ ዘንተ ኅብስተ ባርክ ወፈትት ወሀብ ኦ እግዚኦ በከመ አሜሃ ዘንተ ጽዋዐ ዕተብ ወቀድስ ወመጡ። (ዓዲ ዚቅ) ቅድሳት ለቅዱሳን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ።
🌹ሰቆቃወ ድንግል💐በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ ሕፀተ ግጻዌ ዘአልቦ፤ ሰቆቃወ ድንግል እጽሕፍ በቀለመ አንብዕ ወአንጠብጥቦ፤ ወይሌ ወላህ ለይበል ዘአንበቦ፤ ከማሃ ኀዘን ወተሰዶ ሶበ ለኵለሄ ረከቦ፤ ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ።
✨✨ወረብ✨✨ከማሃ ኀዘን ከማሃ ኀዘን ወተሰዶ ኀዘን፨ ርእዮ ለይብኪ ዓይነ ልብ ዘቦ ዓይነ ልብ።
✨✨ዚቅ✨✨እወ አማን እምውሉደ ሰብእ አልቦ ምንዳቤ ወግፍዕ ዘከማኪ በውስተ ኵሉ ዘረከቦ።
°༺༒༻° መዝሙር °༺༒༻°ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ትዌድሶ መርዓት እንዘ ትብል ነዓ ወልድ እኁየ ንፃእ ሐቅለ [ት] ንርአይ ለእመ ጸገየ ወይን ወለእመ ፈረየ ሮማን [ት] አሠርገወ ሰማየ በከዋክብት ወምድረኒ በሥነ ጽጌያት፤ [ት] እስመ ውእቱ ወልድ ዋሕድ እግዚኣ ለሰንበት (ማንሻ)፦ ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ፤ ወልድ እኁየ ቃልከ አዳም።
✨️አመላለስ ዘመዝሙር✨ትዌድሶ መርዓት ወትብሎ፨ ወልድ እኁየ ቃልከ አዳም ወልድ እኁየ ቃልከ አዳም።
🌹🌷🌹🌷🌹🌷🌹🌷🌹🌷🌹
"የመዳን ምክንያት የሆነው ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የእሳት ማዕበል ሁሉን ባሰጠመ ነበር።"
🌹🌹አባ ጽጌ ድንግል🌹🌹
🌹🌹🌹
✨🍂✨🍂✨🍂✨🍂✨🍂✨
"ሰላም ለአርሴማ ቅድስት ከመ በቀልት ዘይመስል ቆማ፤ ወዘከለላ ዘመንፈስ ግርማ ዘፈጽመት ገድላ በጻማ ወበመንግሥተ ሰማይ ዐቢይ ስማ"
ትርጉም፦ ገድሏን በሥቃይ የፈጸመች፤ የመንፈስ ግርማ የጋረዳትና ቁመቷ እንደ ዘንባባ የሚመስል ለምትኾን ለቅድስት አርሴማ ሰላምታ ይገባል፤ በመንግሥተ ሰማይም ስሟ ታላቅ ነው።
✨ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ✨
✨🍂✨🍂✨🍂✨🍂✨🍂✨
💠💠💠ቅድስት አርሴማ💠💠💠
ቅድስት አርሴማ እናታችን ከአባቷ ከቅዱስ ቴዎድሮስና ከእናቷ ቅድስት አትናሲያ በስዕለት ተወለደች፡፡ ቤተሰቦቿ እግዚአብሔርን በቅንነት ያገለግሉ ከነበሩ ከከበሩ ካህናት ወገን እንደነበሩ የገድሏ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡
ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከቤተሰቦቿ በሚገባ የተማረች፤ የተማረችውንም በተግባር የተረጎመች፤ በጸሎት ሕይወት የምትተጋ ከቅዱሳት አንስት አንዷ ናት፡፡ ይቺ ታላቅ ሰማዕት በነበረችበት ዘመን በአርመን የነገሠው አረማዊ ንጉሥ ድርጣድስ ይባላል፡፡ ይኸ ንጉሥ እግዚአብሔር አምላክ በሙሴ ላይ አድሮ “ቀልጠው የተሠሩትን የአማልክት ምስሎች ለአንተ አታድርግ” ብሎ የተናገረውን በመቃወም ለጣዖት ይሰግድ ፀሐይንም ያመልክ ነበር /ዘጸ.፴፬፥፲፯/፡፡
በዘመኑ የነበሩ ክርስቲያኖችን “እኔ ለማመልከው አምላክ ወይም ጣዖት መስገድ አለባችኹ፤ ይኽን የማታደርጉ ከኾነ ትእዛዜን ጥሳችኋልና መከራ ይጸናባችኋል” የሚል ዐዋጅ በማውጣት መከራ ያደርስባቸዋል፡፡
ጨካኙ ንጉሥ ድርጣድስ ይኽን ትእዛዙን ባለማክበራቸው መከራና ስቃይ ያደረሰባቸው ክርስቲያኖች ቁጥራቸው ፳፯ ናቸው፡፡ “እኔን የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሌንም ተሸክሞ ይከተለኝ” ያለውን የእግዚአብሔርን ሕግ የፈጸሙ ክርስቲያኖች እሱ ለሚያመልከው ለጣዖት አንሰግድም በማለታቸው ይደበድባቸውና ግፍና መከራ ያጸናባቸው ጀመር፡፡ ይኽን ግፍና መከራ የተመለከተች እናታችን ቅድስት አርሴማ የተጋድሎ ሕይወትን እነሱን አብነት አድርጋ እንደ ጀመረች የሕይወት ታሪኳን የያዘው መጽሐፏ ይነግረናል፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማቴዎስ ወንጌል ‘‘ነገር ግን ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ በምኩራቦቻቸውም ይገርፏችኋልና ከሰዎች ተጠበቁ! ለእነርሱና ለአሕዛብም ምስክር እንዲኾን ስለ እኔ ወደ ገዢዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችኹ… አትጨነቁ! በእናንተ የሚናገር የአባታችኹ መንፈስ ነው እንጂ የምትናገሩት እናንተ አይደላችኹም” /ማቴ.፲፥፲፮-፳/፡፡ ብሎ የተናገረውን በማሰብ ቅድስት አርሴማ በሃያ ዓመቷ የንጉሡን እኩይ ግብሩን በመንቀፍ ስለ ክርስቶስ ከሚሰቃዩ ሰማዕታት ወገኖቿ ጋር በመኾን ስለ እግዚአብሔር አምላክነት ትመሰክር ነበር፡፡
የንጉሡም አገልጋይ በደም ግባቷና በንግግሯ ማማር ተደንቆ በዚች በፈቃዷ ሰማዕትነትን ልትቀበል በወደደች ሴት ምንም ሊያደርግባት ስላልወደደ ወደ ንጉሡ ወደ ድርጣድስ ከሃያ ሰባቱ ክርስቲያኖች ጋር ወሰዳት፡፡ ንጉሡም ብዙ የተነገረላትን ወጣት ሲያይ በውበቷና በንግግሯ ተማርኮ ለዓለማዊ ደስታውና ፍላጎቱ ተመኛት፡፡ ሚስት ትኾነው ዘንድ አብዝቶ ተማጸናት፡፡ ለእጅ መንሻና ለማታለያ የዚኽን ዓለም ወርቅና ብር አቀረበላት፡፡ ቅድስት አርሴማ ግን መልክ ረጋፊ፤ የዚኽ ዓለም ሀብትም ከንቱ እንደኾነ ስለምታውቅ በዓላማዋ ጸናች! ንጉሡንም ‘‘እኔ የንጉሥ የክርስቶስ ሙሽራ እንጂ የዚኽን ዓለም አላፊ ጠፊ የኾነውን ገንዘብና ደስታ የምሻ አይደለኹም፡፡’’ በማለት መለሰችለት፡፡
ንጉሡም ይኽንን ከእርሷ በመስማቱ እጅግ ተቆጣ፤ እግዚአብሔር አምላኳን በማመኗ ተበሳጨ፤ አሽከሮቹንም ጠርቶ በቤተመንግሥቱ የታሠሩትን አንበሶች እንዲለቀቅባቸው አዘዘ፡፡ አንበሶቹ ግን ይደሰቱ ነበር፡፡ በኋላም ፊታቸውን ወደ ንጉሡና አገልጋዮቹ በማዞር ሩጠው እስኪደበቁ ድረስ አሳደዷቸው፡፡
በቅድስት አርሴማ የገድል መጽሐፍ ላይ የሰፈረው ታሪክ በተመሳሳይ መልኩ በትንቢተ ዳንኤል ላይ ሲፈጸም እናያለን፡፡ ነቢዩ ዳንኤል ያለ በደሉ በክፉ ሰዎች ምክር የተራቡ አንበሶች ወዳሉበት ጉድጓድ በተጣለ ጊዜ አንበሶቹ ፈጽሞ ጉዳት አላደረሱበትም፣ እንኳን ሊበሉት የእግሩን ጥፍር እየላሱ ተገዝተውለታል፡፡ “በነጋውም ንጉሡ ማልዶ ተነሣ ፈጥኖም ወደ አንበሶቹ ጉድጓድም ወደ ዳንኤል በቀረበ ጊዜ በኃዘን ቃል ጠራው፤ ንጉሡም ተናገረ ዳንኤልንም፡- የሕያው አምላክ ባሪያ ዳንኤል ኾይ ኹልጊዜ የምታመልከው አምላክኽ ከአንበሶች ያድንኽ ዘንድ ችሎአልን? አለው፡፡ ዳንኤልም ንጉሡን ንጉሥ ኾይ ሺኽ ዓመት ንገሥ በፊቱ ቅንነት ተገኝቶብኛልና በአንተም ፊት ደግሞ ንጉሥ ኾይ አልበደልኹምና አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶችን አፍ ዘጋ፤ እነርሱም አልጎዱኝም አለው” የዳንኤል ከሳሾችን ግን “በአንበሶች ጉድጓድ ጣሏቸው፤ ወደ ጉድጓዱም መጨረሻ ሳይደርሱ አንበሶች ያዟቸው ዐጥንታቸውንም ሁሉ ሰባበሩ” /ዳን. ፮፥፲፱-፳፭/፡፡
ንጉሡ የክርስቲያኖቹ በሰማዕትነት መጽናት ስለነደደው በረኃብ እንዲያልቁ እንዲታሠሩ አዘዘ፡፡ እግዚአብሔርም በአምስተኛው ቀን በብርሃን ቤቱን ሞልቶት የሚበሉትን በመሶብ የሚጠጡትን በጽዋ ከሰማይ አወረደላቸው፡፡
ንጉሡም ይኽንን በማየቱ ከዚያ አውጥቶ በእሳት ውስጥም አስገባቸው፡፡ ሠለስቱ ደቂቅን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ ከእሳት ያወጣቸው እግዚአብሔር አምላክ እነርሱንም አዳናቸው፡፡ የክርስቲያኖቹ የእምነት ጽናት የሚደንቅ ስለነበር ንጉሡ አማካሪዎቹ ጠርቶ “ምን ብናደርግ ይሻላል?” የሚል ምክር ጠይቆ ኹሉንም በሰይፍ ተሰይፈው እንዲሞቱ ስምምነት ላይ ይደርሳል፡፡
እያንዳንዳቸውን ተራ በተራ ሲሰይፋቸው ቅድስት አርሴማ ለሚሰየፉት ኹሉ የድል አክሊል ከሰማይ ሲወርድላቸው ትመለከት ስለነበር የእርሷን ተራ በጉጉት ትጠብቀው ነበር፡፡ በሰማዕትነት አምላኳ እንዲያጸናት እየጸለየች “አይዟችኹ ጽኑ! የዚኽ ዓለም መከራ አያሰቅቃችኹ! አትፍሩ” እያለች ታጽናናቸው ነበር፡፡
ንጉሡም ሌሎቹን አሰይፎ ሲያበቃ ወደሷ ዞሮ በቁጣ እየጮኸ “አንቺን እንደ ባልንጀሮችሽ በቀላሉ አልገልሽም! ስቃይ አጸናብሻለኹ” ብሎ ለአገልጋዮቹ ትእዛዝ በመስጠት ዓይኗን አስወጥቶ በእጇ እንድትይዝ አደረጋት፤ ጡቷን ቆረጠ፤ በኋላም አንገቷን በሰይፍ በመቅላት መስከረም ፳፱ ቀን በዛሬዋ ዕለት በሰማዕትነት እንድታልፍ አድረጋት፡፡
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‘‘ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ’’ እንዲል /መዝ. ፰፥፫/፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‘‘በእኔ ስም አምነሽ የዚኽ ዓለም ተድላና ደስታ ሳያታልልሽ አንገትሽን ለሰይፍ ሰጥተሽ ተሰይፈሻል፤ የሰማዕትነት ተጋድሎ ፈጽመሻልና ስምሽን የጠራ፤ በዓልሽን ያከበረ፤ ዝክርሽን ያዘከረ፤ ገድልሽን የጻፈና ያጻፈ፤ የሰማና ያሰማም እስከ ፲፪ ትውልድ ድረስ እምርልሻለኹ’’ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡
የቅድስት አርሴማ አማላጅነት አይለየን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
Baga bara barnotaa 2018tiif issin gahe!
"Ati garuu isa barsiifamte, cimsitees itti amante sana eenyufa'i irraa akka barte waan beektuuf, isatti qabamii jiraadhu!" 2ffaa Ximo 3÷14Akka bara darbeeti mani barumsaa sanbata kenyaa barumsaa afuraa bara kanaafis barsisudhaaf qophi isaa xumurre isiin baratota galmesaa jiraa. Bara kanaas afaan lachun afaan orommo fi afaan amaaraa barsisudhaaf baratotaa haraa fi baratota turan kutaa 1-9faatii barsisuuf baratota galmesaa jira. Galma' baradhaa! Bakka galmee 👉Yerro hundaa sa'atti 10:00 iraa kaase waltaji irrati, galma mana barumsaa sanbatichaati fi mana kitaabati 👉Sa'aatti hojjitin mana gurgurtaa meshaale qulqullu M/B/sanbatichaati 👉 Sa'aati barbaadan bakka jirtaan iraa linkii armaan gadditin( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 ) galmaa'u ni dandessan Dabalataaf 👉0968903347 👉0998646565 👉0938117125
እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!
"አንተ ግን በተማርበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር!" ፪ኛ ጢሞ ፫፥፲፬እነሆ ዘንድሮም እንደአምናው በሰ/ት/ቤቱ የሚሰጠው ተከታታይ መንፈሳዊ ትምርት ለመስጠት ዝግጅታችንን ጨርሰን ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ እንገኛል። በሁለቱም ቋንቋዎች በአፋን ኦሮሞና በአማርኛ ከ1-9ኛ ክፍል ነባርና አዲስ ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል ይምጡና ይመዝገቡ ይማሩ! የመመዝገቢያ ቦታ 👉ዘወትር ቀን ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአውደ ምህረት፣ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽና ቤተ መጽሐፍት 👉ሁሌም በስራ ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ ነዋየ ቅዱሳት መሸጫ 👉 በፈለጉት ሰዓት ባሉበት ሆነው በሚከተለው ሊንክ በመግባት በonline መመዝገብ ይችላሉ( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 ) ለበለጠ መረጃ 👉0968903347 👉0998646565 👉0938117125
✨✨✨🌿✨🌿✨🌿
"እኛ ከተናገርን እግዚአብሔር ዝም ይላል፤ እኛ ዝም ስንል እርሱ ሥራውን ይሠራል።"✨ብጹእ አቡነ ሽኖዳ✨ ውድ ወንድሜ ሰውን በስብከት ማገልገል የግድ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይደለም፣ ትልቁና ዋነኛው ሰውን በራስ ሕይወት መለወጥ ነው፡፡ ስለዚህ በሕይወትህ ለብዙዎች አብነት እንድትሆን እንጂ የግድ ስብከት አዘጋጅተህ መድረክ ላይ መቆም ብቻ አይጠበቅብህም፡፡ እንዲህ አይነት ሰው ከሆንክ ሰዎች ፊትህን ባዩት ጊዜ የዋህነትን፣ ሩህሩህነትን ይማራሉ፣ ንግግርህንም በሰሙ ጊዜ መንፈሰ ጠንካራነት፣ ታማኝነት፣ ፍፁምነትና ፍቅርን ያገኛሉ፡፡ ✨ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ - ከመንፈስ ነፃነት የተወሰደ✨ "ከንስሐ አባትህ ጋር ስትሆን ጥያቄህን እንጂ ውሳኔህን አታቅርብላቸው፤ በልብህ ካሰብከው ጋር እንዲስማሙ ሳይሆን በሀሳብህ ላይ ሀሳባቸውንና ምክራቸውን እንዲሰጡህ አድርግ።" ✨ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ✨ “ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን? እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡" ✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ✨
ኃጥእ በንስሓው ጊዜ የሚያለቅሰው እንባና ስለ እግዚአብሔር ብለው የሚያፈሱት የሰማዕታት ደም አንድ ናቸው። ሁለቱም ጸጋ እግዚአብሔርን ለማሰጠት የሰለጠኑ ናቸውና።✨መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 69✨ ✨✨✨🌿✨🌿✨🌿
🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱
“እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።”
፪ኛ ጴጥሮስ ፩፥፯
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ቸሩ መድኃኔዓለም በዕለተ ቀኑ ቸር ወሬ ያሰማን🙏
✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨
✨እንኳን ለፆመ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ ✨
ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው፡፡
በግዕዝ ጸገየ ማለት አበበ ፤ አፈራ ፣ በውበት ተንቆጠቆጠ ማለት ነው፡፡
በማኀሌቱም እመቤታቸንን 3 ዓመት ከ6 ወር በግብፅ ከዚያም የአሥራት ሀገሯ በሆነችው በኢትዮጵያ የተሰደደችበትን ወቅት በማሰብ በጽጌና በአበባ እመቤታቸንን እና ጌታቸንን በመመሰል ሲያመሰግኗት ፣ ከልጇ ጋር ያየችውን መከራ እያሰቡ እና ምልጃዋን ሲለምኑ ያድራሉ ፡፡
✨✨🌹
''እምግብጽ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን፤ ለቅዱሳን ክብር ልጄን ከግብጽ ጠራሁት››
በማለት ነቢዩ ሆሴዕ በምዕራፍ ፲፩ ቍጥር ፩ እና ፪ ላይ አስቀድሞ እንደ ተናገረው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በልጅነቱ ወደ ምድረ ግብጽ (ምስር) የተሰደደው የነቢያት ትንቢት ይፈጽም ዘንድ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕፃናትን በመፍጀት ከሚታወቀው ከአረመኔው ንጉሥ ከሄሮድስ ለማምለጥ ነው፡፡ አምላካችን ክርስቶስ ያለጊዜው (ዕለተ ዓርብ) ደሙ አይፈስምና፡፡ ስለዚህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ፤ ሄሮድስ ሕፃኑን ለመግደል ይፈልጋልና›› ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለዮሴፍ በነገረው ቃል መሠረት ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በሌሊት ወደ ግብጽ ምድር ተሰደደ፡፡ ይህንን ስደት አስመልክቶ #ሰቆቃወ ድንግል የሚባለውን ቃለ እግዚአብሔር ካህናቱ በሚያሳዝን ዜማ ያደርሳሉ፤ ያቀርባሉ፡፡
✨✨🌹
በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ሄሮድስ አስፈጅቷል፡፡ ‹‹ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ለቅሶና ብዙ ዋይታ፡፡ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች፡፡ መጽናናትም አልወደደችም፤ የሉምና›› የሚለው ትንቢትም ተፈጸሟል፡፡
ከሦስት ዓመት ከመንፈቅ የግብጽ ስደት በኋላ ሊቃውንቱ፡-
‹‹ተመየጢ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ፣ በላዕሌኪ አልቦ ዘያበጽሕ ሁከተ፣ ወኢትጎንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ፣ ዘየኀሥሦ ለወልድኪ ይእዜሰ ሞተ፣ በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ›› እያሉ ከስደት መመለሷን ያበሥራሉ፡፡ትርጉሙም፡-
‹‹ማርያም ሆይ! ወደ ሀገርሽ ወደ ናዝሬት ተመለሺ፡፡ በአንቺ ላይ ሁከት የሚያመጣ ማንም የለም፡፡ ቤት እንደሌለሽ ሁሉ በግብጽ አትቆይ፡፡ ለዮሴፍ በሕልሙ መልአክ እንደ ነገረው የሕፃኑን ነፍስ የፈለገው (ጠላት ሄሮድስ) ሞቷልና››ማለት ነው፡፡ ✨✨🌹 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በዐርባው ቀን (በዘመነ ጽጌ) ወቅት የማርያምን የሽሽትና የመመለስ (የሚጠት) ታሪክ እያነሡ ውዳሴ የሚያቀርቡትና ማኅሌት የሚቆሙት በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ለእመቤታችን ክብር ሲባል የፈቃድ ጾም የሚጾሙ ምዕመናንና ምዕመናትም ብዙዎች ናቸው በመሃል ኢትዮጵያ በፈቃድ ጾምነት ሲጾም ; በሰሜኑ አካባቢ ተጹሞ ከሰዓት ይቀደሳል ሌሎች ጋር ግን ጠዋት ያበቃል፡፡ የእመቤታችን ምልጃ ና ጸሎት አይለየን ምንጭ: የማኅሌተ ጽጌ ምንጭና ትርጉም: መዝገበ ታሪክ:የቤተክርስቲያን ታሪክ መረጃወች ✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨
ማኅሌተ ጽጌ በየ 7 ዓመት ዐውድ በማኅሌቱ ላይ የሚባሉት ቀለሞች ይለያያሉ። ማኅሌቱ ስንተኛ ዓመት እንደሆነ ለማወቅ መጀመሪያ የማኅሌተ ጽጌ የመጀመሪያው ቁመት (የመጀመሪያው እሑድ) መቼ እንደሆነ መለየት ያስፈልጋል። ያው መስከረም 26 ጾሙ ይጀመራል። ስለዚህ የመጀመሪያው ዓመት ወይም 1ኛ ዓመት የሚባለው ማኅሌተ ጽጌ የመጀመሪያው ቁመት የሚቆመው መስከረም 26 ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ነው።
በ1ኛ ዓመት መስከረም 26
በ2ኛ ዓመት ጥቅምት 2
በ3ኛ ዓመት ጥቅምት 1
በ4ኛ ዓመት መስከረም 30
በ5ኛ ዓመት መስከረም 29
በ6ኛ ዓመት መስከረም 28
በ7ኛ ዓመት መስከረም 27 የመጀመሪያው ቁመት ይቆማል ማለት ነው።
ዘንድሮ መስከረም 26 ሰኞ ይገባና በጥቅምት 2 ቅዳሜ ለእሑድ የመጀመሪያው ማኅሌት ይቆማል ማለት ነው።
በዚህ ዓመት ማኅሌተ ጽጌ ለ5 ተከታታይ ሣምንታት ይቆያል።
1ኛ ሣምንት ጥምምት 2
2ኛ ሣምንት ጥቅምት 9
3ኛ ሣምንት ጥቅምት 16
4ኛ ሣምንት ጥቅምት 23
5ኛ ሣምንት ጥቅምት 30
ይሆናል
"ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።"
1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:2-3)
+2
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ የኃዘን መግለጫ
“ ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም " (ራዕ 20 ÷6)
መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡45 በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ በምትገኘው የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ዓመታዊውን የቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓል በማክበርና አዲስ እየተሠራ ያለውን ሕንጻ ቤተክርስቲያን በመጎብኘት ላይ የነበሩ ወገኖቻችን የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ርብራብ ተደርምሶ ሕይወታቸው በማለፉና የአካል ጉዳት በመድረሱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰማው ኃዘን ጥልቅ ነው፡፡
ምንም እንኳን የምንወዳቸው የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ባልተጠበቀ ሁኔታ በሥጋ ከእኛ መለየታቸው የሚያስደነግጥና የሚያሳዝን ቢሆንም ከሞተ ሥጋ አስቀድሞ በሚኖረው ሕይወተ ዓለም ኅሊናቸውን ለእግዚአብሔር ዙፋን አድርገው በቤቱ የኖሩት ሁሉ በሥጋቸው ቢሞቱም ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን እንደሌለው ስናስብ እንጽናናለን፡፡
በመሆኑም በቤተ መቅደሱ እያመለኩ፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በዓል ለነሢአ በረከት እያከበሩ ባሉበት በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ከመካከላችን ያጣናቸው ወገኖቻችን ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንደነገረን ከድካማቸው አርፈው ከእርሱ ጋር ለዘለዓለም የሚነግሡ መሆናቸውን ያለ ጥርጥር እናምናለን፡፡(ራእይ 20.6)
በመጨረሻም በአደጋው ምክንያት ለሞቱት ወገኖቻችን እግዚአብሔር አምላክ ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጣቸው ፤ለቤተሰቦቻቸው ሁሉ መጽናናቱን እንዲያድላቸው እና አካላዊ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችንም ፍጹም ፈውስን ሰጥቶ ወደ ተሟላ ጤንነታቸው እንዲመልስልን እንመኛለን፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት
መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ/ም
