ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Ko'proq ko'rsatish672
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+37 kun
-130 kun
Postlar arxiv
"እኔ በስምሽ አምናለሁ፥ አንቺም ስለእኔ ትማልጃለሽ፥ ልጅሽም ስለአንቺ የልመናዬን ዋጋ ይሰጠኛል።"
— ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
+1
" ኃዘኑ የአረርቲ ደብረ ገነት ማርያም አገልጋይ ካህናትና የከተማዋ ምእመናንን ብቻ ሳይሆን የመላው ኦርቶዶክሳዊያን ኃዘን ነው " - ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ርብራብ የእንጨት ተደርሞሶ ሕይወታቸውን ባጡ ምእመናን የተሰማቸውን ጥልቅ ኃዘን ገለጹ።
" የቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ተጠናቆ ምርቃቱን በጉጉት እየጠብቀን ባለንበት ይህ አስከፊ ኀዘን በመከሰቱ ጥልቅ ኃዘን ተሰምቶናል " ብለዋል።
" ኀዘኑ የአረርቲ ደብረ ገነት ማርያም አገልጋይ ካህናትና የከተማዋ ምእመናንን ብቻ ሳይሆ የመላው ኦርቶዶክሳዊያን ኃዘን ነው በደረሰው ጉዳትም ልባችን ተሰብሯል " ያሉት ብፁዕነታቸው ለካህናቱና ለሕዝበ ክርስቲያኑ መጽናናትን ተመኝተዋል።
" በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን የቅዱሳን አምላክ ነፍሳቸውን በደጋጎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን አጠገብ ያሳርፍልን ጉዳት ደርሶባቸው በጤና በሆስፒታል በሕክምና ለሚገኙ ወገኖቻችን ፈጣሪ በምሕረቱ እንዲጎበኛቸው እንጸልያለን " ብለዋል። #EOTCTV
የመስቀል ደመራ በዓል በአሰላ #ortodox #duet #yotubeshorts
https://youtube.com/shorts/LBZ3maUgLmY?si=YMBIhHxgvZACrMe1
“በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ፡፡"
(1ኛ ቆሮ. 9፥24)
የመስቀል ደመራ በዓል በአሰላ #ortodox #duet #yotubeshorts
https://youtube.com/shorts/LBZ3maUgLmY?si=YMBIhHxgvZACrMe1
✥ ብርሃን ወጣ ✥
ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ የሚያንጸባርቅ፣
የአምላክ እና የሰው ልጆች እውነተኛ እርቅ፣
ደስ ይበለን በትንሣኤው ብርሃን፣
እልል እንበል በአንድነት ሆነን፣
ተነሣልን መድኃኒታችን።
ከፊት ለፊት በመሣሉ የመስቀሉ ነገር
የሚወደው ሐዋርያ የወንጌል መምህር
ዮሐንስም ስቅለቱን በማየቱ
አለቀሰ እስከ ዕለተ ሞቱ
ቢያሠቅቀው ሞቱ ግርፋቱ
ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
በዓለም ጥበብ ለሚኖሩት እውነት ተስኗቸው
ለጠቢብ ሰው በመንፈስ ለሚኖረው
የመዳን ቀንድ እውነተኛ አርማ ነው
ከገሃነም እሳት የሚያድን ነው
እስከ መሞት ላልተለየው ቅዱስ ሐዋርያ
ለዮሐንስ ለወንጌል ሰው የፍቅር ባለሞያ
ምስጋናችን በምድር ይድረሰው
እንድናለን በሰጠን ምሳሌው
ሰዎች ሁሉ እንከተለው
መዝሙር
በሊቀ መዘምራን ይልማ
"ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክሕት ከእኔ ይራቅ።"(ገላ 6÷14)
ክርስቶስን ላመኑ ሁሉ መመኪያቸው የክርስቶስ መስቀል ነው ሐዋርያውም እያለን ያለው ከክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ መመኪያ የለኝም የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ከፈጸመልኝ የመስቀሉ ሥራ ውጪ ሌላ የምመካበት ከእኔ ወይም ከሌላ የሆነ ነገር የለኝም ትምክህቴ መስቀሉ ነው እግዚአብሔር ዘለዓለሜን የሠራው መስቀል ላይ ነው በመስቀል ላይ ሁሉም ተፈጽሟል
እግዚአብሔር በመስቀሉ የሠራው ዘለዓለማችንን ነው
ክርስቶስ ኃጢአታችንን የቀጣው የእዳ ደብዳቤያችንን የሻረው በመስቀሉ ነው
"በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው።ርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።"(ቆላ 2÷14)
በመስቀሉ ጠላታችንን ከመንገዳችን ላይ አስወግዶታል አሁን መንገዳች ከጠላት ሥጋት ነጻ ሆኗል በመንገዳችን ላይ አፋኝ ወይም አጋች የለም በነጻነት እንድንኖር በመስቀሉ ነጻ አውጥቶናል
"በርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና።"(ቆላ 1÷20)
በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ ይቅር ተብለናል በመስቀሉ ደም ምሕረት ታውጆልናል እኛ አሁን የቁጣ ልጆች አይደለንም
መስቀል ምልክታችን ብቻ ሳይሆን ሕይወታችንም ነው ክርስትና ያለ ክርስቶስ መስቀል ነፍስ የተለየው ሥጋ ማለት ነው የክርስትና መሠረቱም ማዕከሉም ጉልላቱም የክርስቶስ መስቀል ነው መስቀሉ በአሮጌውና በአዲሱ መካከል ድንበር ሆኖ ገብቷል
መስቀል ከክርስቶስ በፊት መግደያ ነበር መስቀል በክርስቶስ መሞቺያ ሆኗል ፍጥረታዊ ማንነታችን ሁሉ በመስቀሉ ሞቶ አዲሱ ማንነታችን በአዲስ እስካልጀመረ ድረስ ከአሮጌው ወደ አዲሱ መሻገር ፈጽሞ አይታሰብም መስቀል የግብዓተ መሬት ዋዜማ ነው በመስቀል ያልሞተ በትንሣኤ በኩል መገለጥ አይችልም የአማኞች ኑዛዜ የሚጸናው በመስቀል ነው
ሁለ ነገራችን በክርስቶስ መስቀል መጠቅለል አለበት በመስቀል አሮጌው ይወገዳል በትንሣኤ አዲሱ ይወለዳል መስቀል የአሮጌው ማክተሚያ ነው
ትንሳዔ የአዲሱ የመነሻ ነጥብ ነው
የእግዚአብሔር ልጅ ለእኛ የከፈለው የሕይወት ዋጋ ነው እርሱም መስቀል ይባላል ስለ እኛ የተቀበለው መከራ ሁሉ መስቀል ይባላል እግዚአብሔር በመስቀሉ ላይ ዘላለማችንን ሠርቶ ጨርሷል
በመስቀል ላይ በዋለው ችሎት በእርሱ ያመንን ሁሉ ምህረት ተደርጎልናል ከዘለዓለም እስራት ለዘለዓለም ተፈተናል በእርሱ ቁስል ተፈውሰናል ዳኛው ክርስቶስ ራሱ የእኛ ምትክ ሆኖ የእኛን ፍርድ ተቀብሎ በእኛ ምትክ ታሥሮ እኛ ነጻ ናችሁ ተብለናል ነጻነታችን በመስቀሉ ታውጇል ለክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ እንኳን ለበዓለ መስቀሉ የምስቀሉ ጌታ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ
መልካም የመስቀል በዓል ይሁንላችሁ!!!
ኑ የመስቀል ደመራ ቦታን በጋራ እናጽዳ!
ነገ ሐሙስ መስከረም 15/2018ዓ.ም ሁላችንም ከማለዳው 12 ጀምሮ በቦታው በመገኘት ቦታውን እናጽዳ
"ሰዎችን ከፍቅር በላይ በየትኛውም ዓይነት መንገድ ከክፋታቸው ልንመልሳቸው አንችልም። ፍቅር ግን ሰዎችን ከአውሬነታቸው መልሳ ሰዎች እንዲሆኑ የምታደርግ ታላቅ መምህርት ናት።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
+1
❤️ትምህርት የማይጠግቡ ሊቅ❤️
ትምህርት እውቀት በተጠላበት በዚህ ዘመን በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰላ ወረዳ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የሚገኙት የአቋቋም መምህር ክቡር ርዕሰ ደብር አምደ ብርሃን ኃይሌ በትናንትናው ዕለት በአሰላ መንበረ ጵጵስና ርዕሰ ገዳማት ወአድባራት ደብረ ምፅላል ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በሚገኘው የቅኔ ጉባኤ ቤት በቅኔ መምህርነት ተመርቀዋል።
አባታችን እንኳን ደስ አሎት። ቸሩ መድኃኔዓለም ፀጋውን ያብዛሎት። ከዚህም በላይ ከፍ ያድርጎት።
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
