cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

በክርስቶስ

በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው ዮሐንስ ወንጌል 3፥36

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
772
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-57 kunlar
-2030 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ፊልጵስዩስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም፥ ⁷ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ ⁸ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ⁹ በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ሁሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ¹⁰ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ ¹¹ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው። ደቀመዝሙር ጌታውን የሚመስል ማለት ነው የጌታውን ፈለግ የሚከተል ጌታው እንዳደረገ የሚያደርግ ጌታው በተጓዘበት የሚጓዝ ጌታው በዋለበት የሚውል የጌታው ታዛዥ ነው። ጌታችን አምላክ ሆኖ ሳለ እራሱን ዝቅ አድርጎ መንገዱን አሳይቶናል እኛም የእርሱ ደቀ መዝሙሮች በመሆን ፈለጉን እንድንከተል ፀጋው ይብዛልን። Humbleness Humility ከጌታችን ናቸውና። @jjjeesuuss @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
👍 3
እግዚአብሔር ትክክል ነው ነገር ሁሉ ለበጎ ነው🥰 @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
Hammasini ko'rsatish...
❤‍🔥 3👍 1
ከዚህ በኋላ በሕይወቴ ይሆናል ብዬ የምጠብቀው ትልቅ ስኬት የለም። ትልቁ ስኬት በኢየሱስ ተሳክቶልኛል ። ኢየሱስ ዘላለማዊ ስኬት ነው። 💐💐💐💐 @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
👍 2
❤#ክርስቶስ #በብሉይ #ኪዳን (#Christ #in #the #Old #Testament ) ❤️ #ዮሴፍ #የኢየሱስ #ጥላ❤️ ✍️ ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ " እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም #ስለ #እኔ #የሚመሰክሩ #ናቸው፤" (የዮሐንስ ወንጌል 5: 39) ✍️ ሉቃስ 24 (ኢየሱስም).... 27፤ ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን #ተረጐመላቸው። ✍️ ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ጥላ ነው!!ብሉይ ኪዳን ስለነ ዮሴፍ የሚያወራ ሳይሆን እነ ዮሴፍን የኢየሱስ ጥላ አድርጎ ስለ ኢየሱስ የሚያወራ ነው፡፡ ✍️መጽሐፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ይናገራሉ!! 😍😍 #የዮሴፍ_ህይወት_ስለ_ኢየሱስ_ #ምን_ይነግረናል? 👍ዮሴፍ እረኛ ነበር ። ዘፍ 37:2 👍ኢየሱስ እረኛ ነው ። ዮሐ 10:11 ❤️ዮሴፍ በአባቱ የተወደደ ነበር ። ዘፍ 37:3 ❤️ኢየሱስ በአባቱ የተወደደ ነው። ማቴ 3:17 ♦️ዮሴፍ ያለ ምክንያት በወንድሞቹ ተጠልቷል ። ዘፍ 37:4-8 ♦️ኢየሱስ ያለ ምክንያት በወንድሞቹ ተጠልቷል ። ማር 3:21 ዮሐ 7:5 👍ዮሴፍ በአባቱ ፈቃድ ወደ ወንድሞቹ ምግብ ይዞ ተላከ። ዘፍ 37:13 👍ኢየሱስ በአባቱ ፈቃድ ወደ ወንድሞቹ ምግብ ሆኖ ተላከ ። ዮሐ 8:42 📌ዮሴፍን ተሳልቀውበታል። ዘፍ 37:19 📌ኢየሱስን ተሳልቀውበታል ። ሉቃ 22:63-65 👍ዮሴፍን ልብሱን ገፈውታል። ዘፍ 37:23 👍ኢየሱስን ልብሱን ገፈውታል። ዮሐ 19:23-24 ❤️በይሁዳ ሀሳብ ዮሴፍ በ 20 ብር ተሽጧል። ዘፍ 37:26-28 ❤️ይሁዳ ኢየሱስን በ30 ዲናር ሽጧል። ማቴ 26:14-16 👍ዮሴፍን ታላቅ የሆነው ሮቤል ሊታደገው ሞክሯል ። ዘፍ 37:21 👍ኢየሱስን መሪ የሆነው ጲላጦስ ሊታደገው ሞክሯል። ዮሐ 19:12 ♦️ዮሴፍ ባሪያ ሆኗል። ዘፍ 39:1-2 ♦️ኢየሱስ ባሪያ ሆኗል። ማቴ 20:28 ፊሊ 2:7 ❤️ዮሴፍ በሀሰት ተመስክሮበታል። ዘፍ 39:14 ❤️ኢየሱስ በሀሰት ተመስክሮበታል። ማቴ 26:59-62 👍ዮሴፍ የበደሉትን ይቅር ብሏል። ዘፍ 45:4 👍ኢየሱስ የበደሉትን ይቅር ብሏል። ሉቃ 23:34 📌ከዮሴፍ ጋር ከታሰሩት አንዱ ወንጀለኛ ድኗል ሌላኛው ሙቷል። ዘፍ 40:1-3 📌ኢየሱስ ጋር ከተሰቀሉት አንዱ ወንጀለኛ ድኗል ሌላኛው ሙቷል። ሉቃ 23:32-33 👍ዮሴፍ ከውርደቱ በላኃ ከብሯል። ዘፍ 41:41 👍ኢየሱስ ከውርደቱ በኃላ ከብሯል። ሉቃ 24:26 & ፊሊ29:11 ❤️ዮሴፍ ህዝብን ከርሀብ አዳኝ ሆኗል። ዘፍ 45:5 & 47:25 ❤️ኢየሱስ ህዝብን ከሞት አዳኝ ነው። ማቴ 1:21 & 1ዮሐ 4:14 📌ዮሴፍ ወደ ደረቅ ጉድጓድ በወንድሞቹ መጣሉ ደግሞም ከጉድጓድ መውጣቱ። ዘፍ 37:24 📌ኢየሱስ ወደ ሞት አሸዋ መውረዱ ደግሞም መነሳቱ ። ማቴ 27፡60, ሐሥ 2:38, 1ቆሮ 15:1- ♦️ዮሴፍ በህይወት እንዳለ ያዕቆብ አላመነም ነበር ። ዘፍ 45:26 ♦️ኢየሱስ በህይወት እንዳለ ደቀመዛሙርቱ አላመኑም ነበር። ሉቃ 24:10-11 & ማር 16:9-12 👍ዮሴፍ ከኪዳን ውጪ የሆነችውን አስናትን አገባ። ዘፍ 41:45- 👍ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ምስጢር የነበረችውን ቤተክርስቲያንን የራሱ አደረገ። ኤፌ 5:30 ❤️ዮሴፍ ከፈርኦን ጋር በሰረገላ ተቀመጠ በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ ተሾመ። ዘፍ 41:40-43 ❤️ኢየሱስ በአባቱ ቀኝ በዙፋን ተቀመጠ። ኤፌ 1:20-22 👏 ዮሴፍ በመጨረሻ አባቱን እና ወንድሞቹን አገኛቸው ከርሃብ አዳናቸው። ዘፍ 46:1- 👏 ኢየሱስ የእስራኤላውያን ከቅሬታ ከመከራው ዘመን በማዳን ለ 1ሺ አመት ከቤተክርስቲያን ጋር ይነግሳል። ራዕ 20:3-6 መጽሐፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ይናገራሉ!! " እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።" (ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2: 17) ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
Hammasini ko'rsatish...
❤‍🔥 1
ኢየሱስ አማላጅ ነው!!! " የ ኢየሱስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ " "ክፍል አንድ" 👉 ምልጃ ማለት በሁለት አካላት መካከል ባለ ጠላትነት ወይም በተፈጠረ አለመስማማት በሌላ ሶስተኛ ወገን የሚቀርብ ፀሎት ፣ልመና እና የማስታረቅ ክንውን ነው። 👉 ምልጃ በ በዳይ እና በ ተበዳይ አካላት የተፈጠረን ግጭት ለመፍታት ሌላ ሶስተኛው ወገን በ በዳዩ ስም ተበዳዩን የሚለምነው ልመና ነው። 👉 አማላጅ ማለት ደግሞ በሁለት የተጣሉ፣ የተራራቁ፣ የተቀያየሙ አካላት መካከል ገብቶ እርቅን ለማምጣት ወይም ለማስታረቅ ምልጃን የሚያቀርብ ነው። 📌 ኢየሱስ አማላጅ ነው ወይም ያማልዳል ሲባል በ ሰው እና በ እግዚአብሔር መካከል የነበረውን ጠላትነት ለመሻር ፣የሰውን ልጅ ከ እግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ፀሎትን ፣ ልመናን እና ምልጃን የራሱን ደም በማፍሰስ አቅርቦለናል ማለት ነው ። 📌 የ ኢየሱስ ክርስቶስ ምልጃ በ መፅሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ከ ብሉይ ኪዳን ጀምረን እስከ አዲስ ኪዳን ያሉትን ከዚህ በታች እንመልከት:- 📌 1). “ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”   — ኢሳይያስ 53፥12 👉 ነብዩ ኢሳያስ ከ ኢየሱስ ልደት ሰባት መቶ ዓመት አስቀድሞ ስለ ኢየሱስ ምልጃ ተናግሯል። 👉 ኢሳያስ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ ማለቱ ሃጥያተኞች ሳለን አመፃችንን እንዳይቆጥርብን ወደ እግዚአብሔር ለመነልን ።( ሉቃ 23:34) 👉 " ማለደ " የሚለው ቃል የ ዕብራይስጥ አቻው (יַפְגִּֽיעַ׃) ወይም (yap‌-gî-a‘) የሚል ነው ትርጉሙም አማለደ ማለት ነው። 👉 የ እንግሊዘኛ አቻውም ( made intercession ) የሚል ነው ትርጉሙ ምልጃን አደረገ ማለት ነው። 📌 2). ኢሳይያስ 59 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁵ እውነትም ታጥቶአል፥ ከክፋትም የራቀ ሰው ለብዝበዛ ሆኖአል። እግዚአብሔርም አየ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ። ¹⁶ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። 👉.እግዚአብሔር አምላክ ወደርሱ ምልጃን ሊያቀርብ የሚችል ማንም ሰው እንደሌለ በተረዳ ጊዜ የገዛ ክንዱ (ኢየሱስ ) መድሃኒት አመጣለት አማላጅም ራሱ ልጁ ሆነለት። 📌 3 ).“በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።”   — ዮሐንስ 1፥29 👉 ዮሐንስ ኢየሱስን የ እግዚአብሔር በግ ያለበት ምክንያት በ ሙሴ ሕግ ለ ሀጥያት ስርየት የሚሆነው ከ መንጋው በጎች በደል የሌለበት በግ ስለሆነ ነው ዘሌዋውያን 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ ማናቸውም ሰው ኃጢአት ቢሠራ፥ እግዚአብሔርም፦ አትሥሩ ካላቸው ትእዛዛት አንዲቱን ቢተላለፍ፥ ባያውቅም፥ ያ ሰው በደለኛ ነው፥ ኃጢአቱንም ይሸከማል። ¹⁸ ነውር የሌለበትን አውራ በግ ከመንጋው ለበደል መሥዋዕት እንደ ግምጋሜህ መጠን ወደ ካህኑ ያመጣዋል ካህኑም ሳያውቅ ስለ ሳተው ስሕተት ያስተሰርይለታል፥ እርሱም ይቅር ይባላል። ¹⁹ እርሱም የበደል መሥዋዕት ነው፤ በእውነት በእግዚአብሔር ፊት በደለኛ ነው። 👉 ስለዚህ ኢየሱስ ለ ምልጃ የሚቀርብ የ አዲስ ኪዳን በግ ነው ስለታረደም አማለደን። 📌 4).ሉቃስ 22 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³¹ ጌታም፦ ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤ ³² እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ። 👉.ጌታ ራሱ ስለ አንተ አማለድኩ ብሎ እንዳማለደ በራሱ አፍ ተናግሯል። 👉."አማለድሁ" የሚለው የ ግሪክ ተመሳሳይ ፍቹ "ἐδεήθην" ወይም " edeēthēn"(ኤዴቴን ) የሚል ሲሆን ቀጥተኛ ፍቺው "መለመን "የሚል ነው። 📌5).ሮሜ 8 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³³ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ማን ይከሳቸዋል? የሚያጸድቅ እግዚአብሔር ነው፥ የሚኰንንስ ማን ነው? ³⁴ የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። 👉. እዚህ ላይ ጳውሎስ ራሱ" ስለኛ የሚማልደው "ብሎ ኢየሱስ እንደሚያማልድ እና በ ምልጃዉም ጳውሎስ ራሱ ተጠቃሚ እንደሆነ ነግሮናል ። 👉."የሚማልደው" የሚለው ቃል አገላለፁ አንድ ጊዜ ብቻ ተደርጎ ስለምያበቃ ምልጃ ሳይሆን ቀጣይነት ስለሚኖረው ምልጃ መሆኑን ያሳያል ። 👉. "የሚማልደው " የሚለው ቃል የ ግሪኩ ተመሳሳይ ቃሉ " ἐντυγχάνει" (ኢንቱግካኖ) የሚል ነው ትርጉሙም የሚያማለድ ወይም አማላጅ ማለት ነው ። 👉. እንግሊዘኛውም " interceding" ይላል አማላጅ ማለት ነው ። 👉 የ ግዕዙ ቃል ደግሞ "ወይትዋቀስ በ እንቲአነ " ይላል ትርጉሙም ስለኛ ይከራከራል የሚል ነው ይህም ምልጃውን የሚያሳይ ነው። 📌6). ዕብራውያን 7 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²³ እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤ ²⁴ እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤ ²⁵ ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። 👉. ጳውሎስ በሚገርም ሁኔታ የ ኢየሱስን ምልጃ ሲያስረዳ ምልጃው ያለፈ እና ከዚህ በኃላ የማይሰራ አድርገን እንዳናስበው ሲል "ሊያማልድ" ብሎ ነው ቀጣይነቱን የገለፀው። 👉. እዚህ ላይም "ሊያማልድ " ለሚለው ቃል በ ግሪኩ " ἐντυγχάνειν " ( ኢንቱግካኖ ) የሚል ነው ( to intercede ) ይህም ምልጃውን ሚናገር ቃል ነው ። 👉. እዚሁ ቃል ላይ ማወቅ ያለብን ነገር የ ኢየሱስ ምልጃ ከ ብሉይ ኪዳን ካህናት የተለየ መሆኑን ነው የሚለየውም የነሱ ምልጃ የሚለወጥ እና በ ሞት የሚቋረጥ ሲሆን የ ኢየሱስ ግን ማይለወጥ እና ዘላለማዊ ነው ( ዕብ 7: 23-24) 👉. እዚህ ላይ " ሊያማልድ " ለሚለው ቃል ግዕዙ " ተንበለ " ይለዋል ይህም ምልጃውን ሚናገር ነው። 📌7). 1ኛ ጢሞቴዎስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ ⁶ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤ 👉. መካከለኛው ማለቱ ኢየሱስ ሰውን እና እግዚአብሔርን ለማስታረቅ በመካከል የገባ ስለሆነ ነው ። 👉. ኢየሱስ የ አዲስ ኪዳን መካከለኛ ያስባለው ምክኒያት ለሰው ልጆች በደል እና ሀጥያት ሲል ያፈሰሰው ደም የሚናገር፣ የሚጮህ እና የሚለምን ስለሆነ ነው ። “የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።” — ዕብራውያን 12፥24 @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
00:45
Video unavailableShow in Telegram
🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰 @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
🤷‍♀🤷‍♀🤷‍♀🤷‍♀🤷‍♀🤷‍♀ ✨✨✨✨✨✨✨✨ 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟 🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍 ❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️ 🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍🤍 @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
📍እኛ እንኳን አደረሳቹ የምንባባለው የጨዋታውን ውጤት ስለምናውቅ ነው እንጂ ይሄ ቀን ለደቀመዛሙርቱ ጭንቅ ነበር ያው ውጤቱን የሚያውቅ በጨዋታው በሀል በጭንቅት ቁጭ ብድግ አይልም እንደውም ቁጭ ብድግ ለሚለው ውጤቱን ነግሮ ያረጋጋዋል!!{ወንጌል} ”“በእኔ ሰላም እንዲኖራችሁ፣ ይህን ነግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።”“ ዮሐንስ 16:33 NASV #ኢየሱስ_እየተመራ_ይመስላል_ግን_አሸንፏል #እንኳን_አደረሰን @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
2👍 1
እኛ 1 ኩባያ ውሃ የነፈግነው ጌታ ነው እኮ የዘላለም ህይወት በነፃ የሰጠን😕 #ምን_አይንት_ፍቅር_ነው🥺❤️ @jjjeesuuss
Hammasini ko'rsatish...
👍 3 1