የአሳምነው ድምፅ VoiceOfAsaminew
ይህ የአሳምነው ድምፅ የቴሌግራም ገፅ የአማርኛ አገልግሎት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰኞ፤ ማክሰኞ፤ ረቡዕ እና ቅዳሜ በ17.685 ሜጋ ኸርዝ በ16 ሜትር አጭር ሞገድ ባንድ እንደ ኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ አንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል ስርጭቱን ያስተላልፋል። ቴሌግራም፦ https://t.me/VoiceOfAsaminew Twitter:https://twitter.com/VoiceOfAsaminew
Ko'proq ko'rsatish- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Ma'lumot yuklanmoqda...
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!
ይህ የአሳምነው ድምፅ የቴሌግራም ገፅ የአማርኛ አገልግሎት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰኞ፤ ማክሰኞ፤ ረቡዕ እና ቅዳሜ በ17.685 ሜጋ ኸርዝ በ16 ሜትር አጭር ሞገድ ባንድ እንደ ኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ አንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል ስርጭቱን ያስተላልፋል። ቴሌግራም፦
https://t.me/VoiceOfAsaminewTwitter:
https://twitter.com/VoiceOfAsaminewየቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!
#አይበገሬው ሰሜናዊ ኮከብ"
ዝና፣ እና ክብር ዓለም ዓቀፍም ሽልማት በተገቢው ስፍራ እና ቦታ፣ በፍትሃዊ ማደሪያው ይገኝ ዘንድ ምድሪቷ በሀቅ መንገድ ብትራመድ ይሄን ብርቱ ከዐለት የጠነከረው #ሰው የሚያልፈው አንዳች ክብረ ሞገስ ባልኖረ…
#ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ… አዎ፣ ስለርሱ ላወራችሁ ነው። የዛሬው የዓውደ ፋኖ ገፅ እንግዳዬ ነው።
ስለዚህ፣ መንጋ እና ቲፎዞ አልባ ታጋይ ጥቂት ልል ብችል እንጅ… የዘመኑን ምልዐት፣ የትውልድ ውርስ በደም ዋጋ የታጀበ በሰቆቃ አመታት ውስጥ የተሻገረ፣ ዛሬው በተጋድሎ ዐውድ ላይ ስለሚገኘው መራራ መርህ መር ታጋይነቱን በዚህች ቅፅበት አትቼ አልጨርሰውም።
እርሱ ግን፣ ፍፁም ትሁት ነው። እጁን ጨብጦ ከፍ በማድረግ "ትግልን ከኔ በላይ ለዐሳር" ሲል አታዩትም።
ሲበዛ አይን አፋር እና የደግነት ባለ ፀጋ ነው። በጋዜጠኝነት ደሞዙ… 4 በኦሮሚያ ቤተሰቦቻቸው በግፍ የተገደሉባቸው ወላጅ አልባ ህፃናትን ያሳድጋል፣ እጅ ሲያጥረው በስሙ ይለምንላቸዋል። ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ ያልተገለጠ መፅሀፍ ነው።
ይህ፣ ሰው… ለውጥ የተባለው ጎርፍ ገፍቶ ያመጣው ሰሞነኛ ፖለቲከኛ፣ የዩቲዩብ አማላይ ክፍያ ወደ ሜዳ ያወጣው ጋዜጠኛም አይደለም። ከዚህ በታች… የማወጋላችሁ በጀብዱ የተሞላው ታሪከ ማስታወሻው… ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ ያልተዘመረለት ካባ ያልደረብንለት ፣ የሰራን ቆፍረን አክባሪ ያለመሆናችንን ያሳብቅብናል።
አባይ ዘውዱ… ሰሜናዊ ነበልባል #ፋኖ ኮከባችን…
በኦህዴድ መራሹ የብልጽግና አገዛዝ ዳግም በግፍ እስር ላይ የሚገኘው ዓባይ ዘውዱ ማን ነው⁉️
ስለ ዓባይ ዘውዱ አጠር ያለ መረጃ ለማጋራት ወደናል።
ዓባይ ዘውዱ ደመቀ የተወለደው በድሮው አጠራር በሰሜን ጎንደር ዞን በጭልጋ ወረዳ ዳዋ ዳንጉራ ልዩ ስሙ መንደር ጊዮርጊስ በተባለ ለማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ አዋሳኝ በሆነውና መዳረሻውን ሱዳን ድረስ ያደረገው የጓንግ ወንዝ በሚለዬው ቀበሌ ነው።
ዓባይ ምንም እንኳ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ይወለድ እንጅ እድገቱን ያደረገውና እስከ 6ኛ ክፍልም የተማረው በድሮው አጠራር ታች አርማጭሆ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለአስተዳደር ያመች ዘንድ በሚል ማዕከላዊ አርማጭሆ ተብሎ ራሱን በቻለው ወረዳ ማሰሮ ደንብ ነው።
ዓባይ በልጅነቱ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ የተወሰደው አባቱ አቶ ዘውዱ ደመቀን እና ቤተሰቦቹን "ለለውጥ እየታገሉ ነው፣ እምቢተኛ ናቸው፣ እየተገዙን አይደለም" በሚል ደርግ አባቱን ወደ ጭልጋ አፍኖ በመውሰድ ማሰር እና ማንገላታቱን ተከትሎ ነው።
በወቅቱ ዘውዱ ደመቀ ብቻ አልነበረም ከመንደር ጊዮርጊስ ቀበሌ የታፈነው ምንም እንኳ ከአጭር ጊዜ የእስር ቆይታ በኋላ ከዳንጉራ እስር ቤት የተለቀቁ ቢሆንም አባቱ ደመቀ ሁነኛው፣ ታላቅ ወንድሙ መልካሙ ደመቀ እና ታናሽ ወንድሙ ጌጡ ደመቀም አብረው ታስረው ነበር።
ዘውዱ ደመቀ ግን 'ይህ ነው ዋናው' በሚል ተፈርጆ ወደ ጭልጋ ወረዳ አይከል ማ/ቤት ተወስዶ ከ6 ወራት የግፍ እስር በኋላ መፈታቱን ተከትሎ ነው ባለቤቱን ባንች አምላክ በለጠን እና ልጆቹን ይዞ የጓንግን ወንዝ ከማዶ እና ማዶ ሶስትና አራት ረዣዥም እንጨት ጣል በማድረግ በሰራው ጊዜያዊ መሻገሪያ ድልድይ ተሻግሮ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ያቀናው።
የመጀመሪያ ወይም የበክር ልጅ የሆነው ዓባይ ዘውዱ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ተወልዶ በአርማጭሆ ማሰሮ ደንብ ወረዳ ሳንኪ ሚካኤል ነው እድገቱን ያደረገው።
ዓባይ የተወለደበት ብቻ ሳይሆን ያደገበት አካባቢም በአብዛኛው በተራራ ሰንሰለት እና በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ ነው።
ዓባይ የት ተማረ?
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስከ 6ኛ ክፍል የተከታተለው በማሰሮ ደንብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን የ7ኛ ክፍል ትምህርቱን ደግሞ በታች አርማጭሆ ወረዳ ሳንጃ ት/ቤት ነው።
ዓባይ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የተከታተለው በባህር ዳር ነው።
ይኸውም፦
1) 8ኛ ክፍል_በባህር ዳር ቁልቋል ሜዳ ት/ቤት፣
2) 9ነኛ እና 10ኛ ክፍል_በባህር ዳር ፋሲሎ ት/ቤት፣
3) 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን በባህር ዳር መሰናዶ ት/ቤት እንዲሁም
4) የዩኒቨርስቲ ትምህርቱንም በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፔዳ ካምፓስ የተከታተለ ሲሆን በጋዜጠኝነትና ግንኙነት (Journalism and Communications) ትምህርት ዘርፍ 3.66 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ እና በሽልማት ተመርቋል።
የትግል ሁኔታን በተመለከተ?
በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ በመድረክ እና በጽሁፍ ሲያደርገው የነበረው ትግል እንዳለ ሆኖ በዋናነት ከ2005 ዓ/ም ጀምሮ ነው የህወሀት እና ህወሀት ተሸናፊ እና ተንበርካኪ አድርጎ የሰራውን የብአዴን ስርዓትን አምርሮ በመጥላት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)ን ተቀላቅሎ ታግሏል።
በተለይ በህወሀት በሀይል ከአማራ የተወሰደው የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ እንዲሁም በሱዳን በጎንደር በኩል የሀገር ሉኣላዊነት ተደፍሮ የተወሰደው ሰፊ ለም መሬት እና በተለያዩ አካባቢዎች በአማራ ህዝብ ላይ ይደርስ የነበረው ሁለንተናዊ ግፍ እና በደል ወደ አንድነት ትግሉ በመግባት ከብርቱ ለውጥ ፈላጊ እና የነቁ ጓደኞቹ ጋር በመሆን በአብርሃጅራ ከተማ ቢሮ በመክፈት ጭምር አገዛዙን እንዲታገል ገፋፍቶታል።
በለውጥ ትግሉ መስዋዕት ከሆኑት ነፍሳቸውን ይማርና ከእነ ደስታው ተገኘ፣ አንጋው ተገኘ እና ታናሽ ወንድማቸው ባበይ ተገኘ ጋር በመናበብ አገዛዙን ይታገል ነበር።
ደስታው ተገኘ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ አገዛዙን ለመታገል ሲመለስ በአብደራፊ/ምድረገነት አካባቢ ባጋጠማቸው ውጊያ ዶ/ር ብርሃኑ ከተባለ የትግል ጓዱ ጋር ስለ አማራ ህዝብ እና ስለ ሀገር ሲል በጀግንነት በክብር የተሰዋ ሲሆን ወንድሞቹ አንጋው ተገኘ እና ታናሻቸው ባበይ ተገኘ ደግሞ እምብኝ ለወገኔ በማለት በመጋቢት 2016 ዓ/ም ኦህዴድ መራሹን የብልጽግና አገዛዝ በነፍጥ ሲፋለሙ በክብር የተሰው ጀግኖች ናቸው።
ዓባይ ከእነ እንግዳው ዋኘው፣ ስርዓቱ ለሰላማዊ ትግል ዝግጁ አይደለም በማለት ወደ ኤርትራ በማቅናት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን ተቀላቅለው ሲታገሉ ከነበሩት ከእነ አብርሃም ልጃለም፣ ከአለልኝ እና ከሌሎችም ጋር በመሆን በምዕራብ ጎንደር ዞን አብርሃጅራ ሲታገሉ ነበር።
ከእነ አለላቸው አታለል፣ ቀለብ ስዩም፣ ተገኘ ሲሳይ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ ፈረጃ ሙሉ፣ ሰጠኝ ቢልልኝ፣ አወቀ፣ እንዲሁም ከአነ አግባው ሰጠኝና ከሌሎች ጀግኖች ጋርም በመናበብ አብሮ ለእውነተኛ እና ስር ነቀል ለውጥ ይታገል ነበር።
ዓባይ ዘውዱ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ሲታገል ስለደረሰበት እስር፦
(1) በህወሀት ኢህአዴግ ዘመን
ከጥቅምት 25/2007 ጀምሮ እስከ ህዳር 2010 ድረስ በፈጠራ የሽብር ክስ 4 ዓመት ከ2 ወር ተፈርዶበት ታስሯል።
በአብርሃጅራ፣ በጎንደር 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣በባህር ዳር 9ነኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ በአዲስ አበባ ማዕከላዊ፣ በቂሊንጦ፣ በሸዋሮቢትና በዝዋይ በእስር ተሰቃይቷል።
(2) በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ደግሞ ስለ ሰፊው የአማራ ህዝብ እና ስለተገፉ ወገኖች ድምፅ በመሆኑ 4 ጊዜ ታስሯል።
ይኸውም፦
1) ሀምሌ 10/2013 ዓ/ም
በአዲስ አበባ አውቶብስ ተራ እና በመርካቶ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስለምን ለአማራ ተፈናቃዮች ድምጽ ሆንክ በሚል ታስሯል።Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.