cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

የአሳምነው ድምፅ VoiceOfAsaminew

ይህ የአሳምነው ድምፅ የቴሌግራም ገፅ የአማርኛ አገልግሎት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰኞ፤ ማክሰኞ፤ ረቡዕ እና ቅዳሜ በ17.685 ሜጋ ኸርዝ በ16 ሜትር አጭር ሞገድ ባንድ እንደ ኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ አንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል ስርጭቱን ያስተላልፋል። ቴሌግራም፦ https://t.me/VoiceOfAsaminew Twitter:https://twitter.com/VoiceOfAsaminew

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
1 353
Obunachilar
+2224 soatlar
+497 kunlar
+18730 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ድርጅታችን የቆመው መርህ እና ዓላማ ላይ ነው:: ማዕከላዊነቱን በጠበቀ ድርጅታዊ አሰራር ማመን የአመራሩም የአባሉም ግዴታ ነው። የተሸከምነው ቅዱስ ዓላማ ስትራቴጅክ እይታ እና ቁርጠኝነትን የተላበሰ አመራር ይፈልጋል። ቁርጠኝነታችን ጠላት  ላይ ብቻ ሳይሆን ራሳችን ላይም ይሰራል:: የምንመራው ግዙፍ የሆነ ፖለቲካዊ እና ወታድራዊ ኃይል ነው:: እንደማንኛውም ሰው ሁልግዜም ፍፁም አይደለንም። ስንሰራ እንሳሳታለን። ስንሳሳት እተራረማለን:: በዚህ ሂደት ያለማንም ጣልቃ ገብነት እና አድሎ ተሳስተዋል ብለን ባረጋገጥነው መሰረት የትግል አጋሮቻችን ላይ ከቀላላ ማስጠንቀቂያ እስከ እስራት የሚደርሱ ተገቢ እርምጃወችን ወስደናል:: እንወስዳለንም:: ሆኖም ዓላማው ማረም /መተራረም እና መማር እንጅ በቀል አይደለም:: የማንንም የቡድንም ሆነ የግል ፍላጎት ለማስደሰት ወይም ሌላዉን ለማስከፉት የምንወስነው ውሳኔ የለም። በዚህ እርግጠኛ መሆን ያስፈልጋል። በዚህ አጭር ግዜ ውስጥ ተዓምር የሚባል ለውጥ ያመጣ ትግልን መምራት የሚጠይቀውን የአመራር ጥበብ ለመላበስ ብዙ ውጣ ውረድ ማለፍ ነበረብን። በእያንዳንዱ ውሳኔያችን እና እንቅስቃሴያችን ውስጥ በአፍላ እድሜያቸው የተሰው ታናናሾቻችንን፣ እምቦቀቅላ ልጆቻቸውን ትተው የወደቁ እኩዮቻችንን፣  ከትምህርት ገበታ የተገለሉ ሚሊዮን ታዳጊወችን፣ በድሮን እና በነፍስ ወከፍ መሳሪያ በወራሪ የተጨፈጨፈውን ህዝባችንን፣ በበርካታ ስቃይ ውስጥ ሆኖም ከጎናችን ያለውን ወገናችንን ታሳቢ እናደርጋለን። እያንዳንዱ እርምጃ እና ተግባር አይቀሬውን ድል ለመጨበጥ የሚያበቃ እንዲሆን ተገቢው ጥንቃቄ ይደረጋል። በተረፈ በተለያዬ መንገድ የውስጥ አሰራራችን ላይ ጣልቃ ለመግባት እና  ያልተገባ ጫና ለማሳደር ለሚሞክሩት ቦታ እንደሌለን መታወቅ አለበት። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ! ©አስረስ ማረ ዳምጤ የአማራ ፋኖ በጎጃም የፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 #ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ💪 8/11/16 ዓ.ም @NISIREamhra
Hammasini ko'rsatish...
የአቶ ስንታየሁ ቸኮልን አጠቃላይ ሁኔታ 1.ከሀምሌ30/2015-ነሐሴ15/2015 ድረስ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ 2.ከነሐሴ15/2015-ህዳር 28/2016 ድረስ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ 3.ከህዳር28/2016-ጥር14/2016 ድረስ አፋር ክልል ሰመራ በሚገኘው ጊዜያዊ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማቆያ እስር ቤት በአስቸጋሪ ሁኔታ አሳልፏል በመቀጠል 4.ከጥር14/2016-የካቲት18/2016 ለ2ተኛ ጊዜ አዋሽ አርባ በሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ 5.ከየካቲት18/2016-መጋቢት20/2016 በፌ/ፖ/ወ/ምርመራ የመጀመሪያ ክሳቸው ■ ከዚህ በፊት በፌደራል ፖሊስ የተመሰረተውና በዋስ እንዲወጣ የተወሰነለትን ክስ ድጋሜ ዐቃቢ ህግ ክሱን በመቀስቀስ:-በኮምፕዩተር ሥርዓት አማካኝነት በህዝቡ መካከል አመፅ እና ሁከት/ግጭት እንዲፈጠር የሚያነሳሳ ፅሁፍ በማዕበራዊ ሚድያ በማሰራጨት በሚል የነበረውን ክስ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ታይቶ ፍርድ ቤቱ በ30ሺ ብር ዋስ እንዲወጣ ወሰነ ነገርግን አልተፈታም 6.ከመጋቢት20/2016-ሚያዝያ19/2016 አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን 7.ከሚያዚያ19/2016-ግንቦት24/2016 ለ3ተኛ ጊዜ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ሁለተኛ ክሳቸው 8.ከግንቦት24/2016-ሰኔ10/2016 ወደ አዲስ አበባ ፌ/ፖ/ወ/ም በማምጣት በእስር ካቆዩት በኃላ ሰኔ 10/2016 ጠዋት 3:00 ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንዲወሰድ በኮማንደር አዱኛ ረጋስ በተባለው የፌ/ፖ/ወ/ምርመራ ክፍል ሀላፊ ትዕዛዝ በሁከት እና ብጥብጥ መዝገብ ተከፍቶ ጨለማ ቤት ውስጥ እንዲታሰር አዟል::በዚህ በተከፈተው መዝገብ ሰኔ11/2016 በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ችሎት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ክስ 1ሳምንት ቀጠሮ ተሰቶ ሰኔ17/2016 የምርመራ መዝገቡን ይዞ እንዲመጣ በሰጠው ብይን መሰረት ሰኔ17/2016 በዋለው ችሎት የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን ያቀረበው ክስ ተቋርጦ ጉዳዩን የፌ/ፖ/ወ/ምርመራ እንዲመለከተው በመጠየቁ መዝገቡ ተቋረጠ በዚህም ያላበቃው ስቃይ ቀጠለ ሦስተኛ ክሳቸው 9.ሰኔ18/2016 የፌ/ፖ/ወ/ምርመራ በሽብር ወንጀል የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በመክፈት ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ሲሆን ሰኔ19/2016 ፍርድ ቤቱ የ10ሺ ብር ዋስትና ከፍሎ እንዲወጣ ብይን ቢሰጥም ይግባኝ በመጠየቅ ሰኔ 25/2016 ጠቅላይ ፍርድ ቤት የታች ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ አፅድቆ እንዲፈታ ትዕዛዝ ቢሰጥም እራሱን ከህግ እና ከተቋም በላይ በማድረግ አልፈታውም 10.ከሰኔ25/2016-ሀምሌ3/2016 ለአባባሉ በህገ-ወጥ መንገድ አስቀምጠውታል አራተኛ ክሳቸው 11.ሀምሌ3/2016 በቁጥር 5 ላይ ከተቀስኩት ክስ ጋር በይዘቱ ተመሳሳይ ክስ ከሰሱት:-አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ የጦር መሳሪያ እንዲያነሳና የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲከሰት በማሰብ በማህበራዊ ሚድያ በመፃፍ ከፍተኛ የሆነ ህዝባዊ አመፅ እና ግጭት እንዲከሰት ገፋፍቶል የሚል ክስ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ሲሆን ፍርድ ቤቱ ለሰኞ ቀን 8/11/2016 8:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል:: ተስፋ አንቆርጥም ተሰፋ እግዚአብሔር ነው!!! https://t.me/Moamediamoresh
Hammasini ko'rsatish...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

አስቸኳይ አስቸኳይ - ምስራቅ ጎጃም! ወደ ደጀን ከተማ ለስብሰባ ሂደው የነበሩና "ስራ አጥ፣ ግንበኛ ወዘተ" የሚል መታወቂያ የያዙት የምስራቅ ጎጃም ዞን የወረዳ አመራሮች ለትናንት አስበውት የነበረውን ጉዞ በመሰረዝ ለዛሬ ሐምሌ 08/2016 ዓም ለጉዞ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ታውቋል። ተነጣጥለው ለህዝብ ትራንስፖርት መጓዝም አቅደዋል። የአካባቢው ቀጠና ፋኖዎቻችን ዝግጁ! መረጃው ይዛመት ይዳረስ!
Hammasini ko'rsatish...
መረጃ ፓዊ መተከል ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በሆዳሙ ሚሊሻ እና አድማ ብተና አማካኝነት ፓዊ ከተማ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች አማራ በመሆናቸው ብቻ ድብደባ እና እስራት እየተፈፀመባቸው መሆኑን ነው የደረሰን መረጃ የሚጠቁመው። ከቀናት በፊት የወርቁ አይተነው እርሻ ስራ ሃላፊ የነበረ እና አንድ መምህር በአድማ ብተና እና ሚሊሻ ቡድኖች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው ነው የታወቀው። #በተለምዶ ስሙ መንደር 14 እና 24 እንዲህውም 26 በሚባሉ የአማራ አርሶ አደሮች መኖሪያ አካባቢዎች የብርሀኑ ጁላ ገዳይ ቡድን እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ አድማ ብተና በጋራ በመሆን በርካታ አማራዎችን በመደብደብ አካለ ጎደሎ መደረጋቸውን ነው ኗሪዎች የገለጹልን። በተመሳሳይ ግልገል በለስ እና ቻግኒ አማራ በመሆናቸው ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው ሲሆን በርካቶች ወደ ማጎሪያ ቤቶች እንደሚወስዷቸው ነው ለማወቅ የተቻለው።
Hammasini ko'rsatish...
ከባለሞያ የመጣ ምክር ነው ......... የፋኖ አመራሮች አስፈላጊ ካልሆነ በቀር ኢንተርኔት ከመጠቀም እንዲቆጠቡ ይመከራል።  እሱን ለመጠቀም ከወሰኑ የሚከተሉትን የደህንነት እርምጃዎች ይጠቀሙ።   ህመም ቤት ያላቸው ኢተርኔት ስትጠቀሙ ከታች ቁልፍን ጠቃሚ ምክሮች ተጠቅመዋል የተንቀሳቃሽ ስልክ ዳታ ወይም ዋይ ፋይን ስትጠቀሙ የእርስዎን ግላዊነት ለማሻሻል እና የመንግስት ክትትል አደጋን ለመቀነስ የሚከተሉትን ስልቶች ያስቡበት፡ 1. ቪፒኤን ተጠቀም፡- ቨርቹዋል ፕራይቬት ኔትወርክ የኢንተርኔት ትራፊክን ኢንክሪፕት ያደርጋል፣ ይህም የሶስተኛ ወገኖች የኦንላይን እንቅስቃሴህን ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ያደርገዋል። 2. ኢንክሪፕትድድ የመልእክት መላላኪያ መተግበሪያዎችን ተጠቀም፡ እንደ ሲግናል፣ ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ፣ አይኤምኦ፣ ቫይበር፣ ዋየር ያሉ መተግበሪያዎች ለግል ግንኙነቶች ከጫፍ እስከ ጫፍ ምስጠራ ይሰጣሉ። 3. ዋይ ፋይዎን ደህንነቱ የተጠበቀ ያድርጉ፡ ነባሪ የይለፍ ቃላትን ይቀይሩ፣ WPA3 ምስጠራን ይጠቀሙ እና WPSን በቤትዎ አውታረ መረብ ላይ ያሰናክሉ። 4. HTTPS ተጠቀም፡ የሚጎበኟቸው ድረ-ገጾች HTTPS መጠቀማቸውን ያረጋግጡ፣ ይህም በአሳሽዎ እና በድረ-ገጹ መካከል ያለውን መረጃ የሚያመሰጥር ነው። 5. የውሂብ መጋራትን ይገድቡ፡ የመተግበሪያ ፈቃዶችን ወደ አካባቢ፣ አድራሻዎች እና ሌሎች የግል መረጃዎች መዳረሻን ያስተካክሉ። 6. የአካባቢ አገልግሎቶችን ያጥፉ፡ አስፈላጊ በማይሆንበት ጊዜ በእርስዎ መሣሪያዎች ላይ የአካባቢ ክትትልን ያሰናክሉ። 7. ሶፍትዌሮችን አዘውትሮ አዘምን፡- ከተጋላጭነት ለመከላከል የእርስዎን ኦፕሬቲንግ ሲስተም፣ አፕሊኬሽኖች እና መሳሪያዎች ማዘመን ያድርጉ። 8. በግላዊነት ላይ ያተኮሩ አሳሾችን ይጠቀሙ፡ እንደ Brave ወይም Firefox ያሉ ግላዊነትን የሚያሻሽሉ ቅጥያዎችን ያስቡ (ለምሳሌ፡ uBlock Origin፣ Privacy Badger)። 9. ሚስጥራዊነት ላላቸው ግብይቶች ይፋዊ Wi-Fiን ያስወግዱ፡ ከተቻለ በወል የዋይ ፋይ አውታረ መረቦች ላይ ስሱ መረጃዎችን ከመድረስ ይቆጠቡ። 10. ስለ አስጋሪ እና ማጭበርበሮች ይጠንቀቁ፡ ሁልጊዜ የመረጃዎን መረጃ ለመስረቅ ተንኮል አዘል ሙከራዎችን ለማስቀረት ሁልጊዜ የሊንኮችን እና የኢሜል ምንጮችን ያረጋግጡ። እነዚህን ልምዶች በማጣመር የመስመር ላይ ግላዊነትዎን እና ደህንነትዎን በከፍተኛ ሁኔታ ማሻሻል ይችላሉ።
Hammasini ko'rsatish...
ሰበር ዜና! በወልድያ ከተማ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመ ጥቃት ስድስት የፖሊስ አባላት ሲገደሉ አምስቱ ተማርከው መወሰዳቸው ተሰማ! የሰሜን ወሎ ዞን ዋና መቀመጫ በሆነችው ወልድያ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ አዳሩን በተፈፀመ ጥቃት በቁጥር ስድስት የፖሊስና የአድማ ብተና አባላት ሲገደሉ አምስቱ ደግሞ ተማርከው መወሰዳቸውን የአማራ ድምፅ ሚዲያ ጥቃቱን የፈፀሙ የፋኖ አባላትና አመራሮችን እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎችን በማነጋገር ለማረጋገጥ ችሏል። ሙት እና ምርኮኛ ከሆኑት የአድማ ብተናና የፖሊስ አባላት በተጨማሪ ሰባት የጣቢያው አባላት ቆስለው ወደ ሕክምና የተወሰዱ ሲሆን ከነዚህ መካከል ሦስቱ በጠና ታመው ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ነው የአይን እማኞች ለጣቢያችን የገለፁት። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ሐምሌ 07/2016 ዓ/ም ለዛሬ አጥቢያ ለሊት 7:00 ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ባለው ነው የተባለ ሲሆን ጥቃቱን የፈፀሙት የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ብርጌድ ፋኖዎች መሆናቸውንም ለማረጋገጥ ተችሏል። በከተማዋ ራስ አሊ ክ/ከተማ ስር የሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመው ጥቃት ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ከሆኑ የአድማ ብተናና ፖሊስ አባላት በተጨማሪ አንድ የፖሊስ ጣቢያው ተሽከርካሪ መውደሙንም  የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት አራት ስታር ሽጉጥን ጨምሮ 25 የሚደርስ ክላሽንኮቭ መሣሪያና በርካታ ቁጥር ያለው ተተኳሽ የማረኩት የፋኖ አባላቱ፡ የማረኩትን መሣሪያ በማረኳቸው የፖሊስ አባላት አሸክመው ከተማዋን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል። ከቆሰሉት ሰባት የፖሊስ አባላት መካከል ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር የተባሉት ሦስቱ የፖሊስ አባላት ክፉኛ በመጎዳታቸው የመትረፍ እድላቸው አነስተኛ ነው ሲሉ ሁኔታውን በቅርብ ርቀት ሁነው ሲከታተሉ የነበሩ የክ/ከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። "በፖሊስ ጣቢያው ላይ ጥቃቱ ሲፈፀም ዝም ብላችሁ ተመልክታችኋል፡ ለምን አባሎቻችንን አላገዛችሁም?" በሚል ዛሬ እረፋዱን ለእስር የተዳረጉ በርካታ የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች መኖራቸውም ታውቋል። የአማራ ድምፅ ሚዲያ
Hammasini ko'rsatish...
🔥#ሰበር_ዜና‼️ በወልድያ ከተማ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመ ጥቃት ስድስት የፖሊስ አባላት ሲገደሉ አምስቱ ተማርከው መወሰዳቸው ተሰማ! የሰሜን ወሎ ዞን ዋና መቀመጫ በሆነችው ወልድያ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ አዳሩን በተፈፀመ ጥቃት በቁጥር ስድስት የፖሊስና የአድማ ብተና አባላት ሲገደሉ አምስቱ ደግሞ ተማርከው መወሰዳቸውን የአማራ ድምፅ ሚዲያ ጥቃቱን የፈፀሙ የፋኖ አባላትና አመራሮችን እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎችን በማነጋገር ለማረጋገጥ ችሏል። ሙት እና ምርኮኛ ከሆኑት የአድማ ብተናና የፖሊስ አባላት በተጨማሪ ሰባት የጣቢያው አባላት ቆስለው ወደ ሕክምና የተወሰዱ ሲሆን ከነዚህ መካከል ሦስቱ በጠና ታመው ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ነው የአይን እማኞች ለጣቢያችን የገለፁት። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ሐምሌ 07/2016 ዓ/ም ለዛሬ አጥቢያ ለሊት 7:00 ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ባለው ነው የተባለ ሲሆን ጥቃቱን የፈፀሙት የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ብርጌድ ፋኖዎች መሆናቸውንም ለማረጋገጥ ተችሏል። በከተማዋ ራስ አሊ ክ/ከተማ ስር የሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመው ጥቃት ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ከሆኑ የአድማ ብተናና ፖሊስ አባላት በተጨማሪ አንድ የፖሊስ ጣቢያው ተሽከርካሪ መውደሙንም  የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት አራት ስታር ሽጉጥን ጨምሮ 25 የሚደርስ ክላሽንኮቭ መሣሪያና በርካታ ቁጥር ያለው ተተኳሽ የማረኩት የፋኖ አባላቱ፡ የማረኩትን መሣሪያ በማረኳቸው የፖሊስ አባላት አሸክመው ከተማዋን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል። ከቆሰሉት ሰባት የፖሊስ አባላት መካከል ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር የተባሉት ሦስቱ የፖሊስ አባላት ክፉኛ በመጎዳታቸው የመትረፍ እድላቸው አነስተኛ ነው ሲሉ ሁኔታውን በቅርብ ርቀት ሁነው ሲከታተሉ የነበሩ የክ/ከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። "በፖሊስ ጣቢያው ላይ ጥቃቱ ሲፈፀም ዝም ብላችሁ ተመልክታችኋል፡ ለምን አባሎቻችንን አላገዛችሁም?" በሚል ዛሬ እረፋዱን ለእስር የተዳረጉ በርካታ የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች መኖራቸውም ታውቋል። ©የአማራ ድምፅ ሚዲያ #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 #ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ💪 8/11/16 ዓ.ም @NISIREamhra
Hammasini ko'rsatish...
#አሳዛኝ ዜና ቲሊሊ! ዛሬ በቲሊሊ ከተማ መሽጎ የሚገኘውን የአራዊት ቡድን በመክዳት እሩጫ በሚያደርግበት ሰሃት እሩምታ ተኩስ በመክፈት የንፁሃንን ህይወት  ቀጥፈዋል፤ አሰቃቂ ድብደባ በመፈፀም ብዙዎችም የአካል ጉዳተኛ ሁነዋል። ከሰሞኑ በተለየ መልኩ መፍረስ የጀመረው ቡድን ለጊዜ ማራዘሚያነት የሚጠቀማቸው ድፍን ጭንቅላት፤ከርሳም አባላቶች በህዝባችን ላይ ከባድ አደጋ በመደቀን የስልጣን መቆያነት ሁነው እያገለገሉ ይገኛሉ። አንግዲህ በዉል ከምንረዳው ስርዓቱ ሁለት አይነት ሰራዊት ይዞ ይንቀሳቀሳል። #አንደኛው ስርዓቱ ገብቶት አያስፈልግም በማለት በዉስጡ እያረረ ወይንም በገገፈፋ ከየ ከተማው የመጡ ህፃናት የጊዜና የቦታ መመቻቸትን እየጠበቀ የሚገኝ ኢትዮጲያዊ የሆነ ጀግና ሲሆን #ሁለተኛው ደግሞ በተለየ መንገድ ተከፋይ የሆነ አልያም ፍፁም የደነዘዘ አማራጭ የሌለው ፤ የሀገር ፍቅርን የማያውቅ መድረሻ የሌለው የአጋንንት ገባሪ ሰራዊት ነው። ይሄን ተከትሎ የስርዓቱ የመረሻው ግብዓተ መሬት በዚህ አጭር ጊዜ መጠናቀቁ የግድ እየሆነ ስለመጣ የአሸባሪነት ደረጃውን ከፍ እያደረገ ስለሆነ ህዝቡ እራሱን በተቻለ መንገድ እንዲጠብቅ  እናሳስባለን። https://t.me/VoiceOfAsaminew
Hammasini ko'rsatish...
የአሳምነው ድምፅ VoiceOfAsaminew

ይህ የአሳምነው ድምፅ የቴሌግራም ገፅ የአማርኛ አገልግሎት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰኞ፤ ማክሰኞ፤ ረቡዕ እና ቅዳሜ በ17.685 ሜጋ ኸርዝ በ16 ሜትር አጭር ሞገድ ባንድ እንደ ኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ አንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል ስርጭቱን ያስተላልፋል። ቴሌግራም፦

https://t.me/VoiceOfAsaminew

Twitter:

https://twitter.com/VoiceOfAsaminew

2) ጳጉሜ 3/2014 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአባ ሳሙኤል ታስሯል። 3) መጋቢት 28/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ እና በአዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ) ታስሯል። 4) ነሃሴ 4/2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ሜክሲኮ፣ አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ እና በቂሊንጦ ታስሯል፤ በአማራዊ ማንነቱ እና በጋዜጠኝነት ሙያው ለህዝብ ድምፅ በመሆኑ እና ስር ነቀል ስርዓታዊ ለውጥ እንዲመጣ በመታገሉ አሁንም በግፍ እስር ላይ ይገኛል። ዓባይ በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ-ደቡብ እዝ መከላከያ ካምፕ ለ6 ወራት ያህል በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ታግቷል፤ በሜክሲኮ የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮም ከ2 ወራት በላይ ከሌሎች የአማራዊ ማንነት ታጋቾች ጋር በሩ እንዲዘጋ ተደርጎ ታስሯል፤ ከሜክሲኮ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ተዛውሮም ታስሯል። ዓባይ አሁን ላይ የፈጠራ የሽብር ክስ ተመስርቶበት በቂሊንጦ እስር ቤት ይገኛል። 4 ዓመት ከ6 ወራት በላይ በታች አርማጭሆ እና በምዕራብ አርማጭሆ ወረዳዎች በባህል እና ቱሪዝም የፕሮሞሽን ባለሙያነት እንዲሁም በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገለው ዓባይ ዘውዱ ህዳር 1/2010 ዓ/ም ከዝዋይ ማ/ቤት ተፈታበት ጊዜ ጀምሮም በጋዜጠኝነት ሙያው በሽብር ተግባር የተሰማራውንና የህወሀት ኢህአዴግ ተቀጥላ የሆነውን የኦህዴድ ብልጽግን አገዛዝና የስሪቱን ገመና በማጋለጥ ጭምር እየታገለ ይገኛል። ዓባይ ዘውዱ እና ቤተሰቦቹ ስለ እውነተኛ ለውጥ በሚል ኢሰብአዊነትን በመቃወም የከፈሉት መስዋዕትነት ከባድ ነው። በማንኛውም ስርዓታዊ ፈተና ሁሉ ከጎኑ የቆሙ ወገኖችን በሙሉ በእጅጉ ያመሰገነው ዓባይ ህዝባዊ ትግል ማሸነፉ አይቀርም ይሏል። ፍትሃዊ የሆነው የአማራው የህልውና፣ የነፃነት፣ የክብር፣ የእኩልነት እና የአብሮነት ትግል ያሸንፋል! ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት ይሁን! ፍትህ ለሁሉም! #ድል፣ ለመላው አምሓራ ፋኖ! https://t.me/Moamediamoresh
Hammasini ko'rsatish...
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ የትግል ልሳን፣ ይከተሉን!

⭐️⭐️⭐️💡ዓውደ ፋኖ💡⭐️⭐️⭐️ 🫵 🫵 "#አይበገሬው ሰሜናዊ ኮከብ" ዝና፣ እና ክብር ዓለም ዓቀፍም ሽልማት በተገቢው ስፍራ እና ቦታ፣ በፍትሃዊ ማደሪያው ይገኝ ዘንድ ምድሪቷ በሀቅ መንገድ ብትራመድ ይሄን ብርቱ ከዐለት የጠነከረው #ሰው የሚያልፈው አንዳች ክብረ ሞገስ ባልኖረ… #ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ… አዎ፣ ስለርሱ ላወራችሁ ነው። የዛሬው የዓውደ ፋኖ ገፅ እንግዳዬ ነው። ስለዚህ፣ መንጋ እና ቲፎዞ አልባ ታጋይ ጥቂት ልል ብችል እንጅ… የዘመኑን ምልዐት፣ የትውልድ ውርስ በደም ዋጋ የታጀበ በሰቆቃ አመታት ውስጥ የተሻገረ፣ ዛሬው በተጋድሎ ዐውድ ላይ ስለሚገኘው መራራ መርህ መር ታጋይነቱን በዚህች ቅፅበት አትቼ አልጨርሰውም። እርሱ ግን፣ ፍፁም ትሁት ነው። እጁን ጨብጦ ከፍ በማድረግ "ትግልን ከኔ በላይ ለዐሳር" ሲል አታዩትም። ሲበዛ አይን አፋር እና የደግነት ባለ ፀጋ ነው። በጋዜጠኝነት ደሞዙ… 4 በኦሮሚያ ቤተሰቦቻቸው በግፍ የተገደሉባቸው ወላጅ አልባ ህፃናትን ያሳድጋል፣ እጅ ሲያጥረው በስሙ ይለምንላቸዋል። ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ፣ ያልተገለጠ መፅሀፍ ነው። ይህ፣ ሰው… ለውጥ የተባለው ጎርፍ ገፍቶ ያመጣው ሰሞነኛ ፖለቲከኛ፣ የዩቲዩብ አማላይ ክፍያ ወደ ሜዳ ያወጣው ጋዜጠኛም አይደለም። ከዚህ በታች… የማወጋላችሁ በጀብዱ የተሞላው ታሪከ ማስታወሻው… ጋዜጠኛ አባይ ዘውዱ ያልተዘመረለት ካባ ያልደረብንለት ፣ የሰራን ቆፍረን አክባሪ ያለመሆናችንን ያሳብቅብናል። አባይ ዘውዱ… ሰሜናዊ ነበልባል #ፋኖ ኮከባችን… በኦህዴድ መራሹ የብልጽግና አገዛዝ ዳግም በግፍ እስር ላይ የሚገኘው ዓባይ ዘውዱ ማን ነው⁉️ ስለ ዓባይ ዘውዱ አጠር ያለ መረጃ ለማጋራት ወደናል። ዓባይ ዘውዱ ደመቀ የተወለደው በድሮው አጠራር በሰሜን ጎንደር ዞን በጭልጋ ወረዳ ዳዋ ዳንጉራ ልዩ ስሙ መንደር ጊዮርጊስ በተባለ ለማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ አዋሳኝ በሆነውና መዳረሻውን ሱዳን ድረስ ያደረገው የጓንግ ወንዝ በሚለዬው ቀበሌ ነው። ዓባይ ምንም እንኳ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ይወለድ እንጅ እድገቱን ያደረገውና እስከ 6ኛ ክፍልም የተማረው በድሮው አጠራር ታች አርማጭሆ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለአስተዳደር ያመች ዘንድ በሚል ማዕከላዊ አርማጭሆ ተብሎ ራሱን በቻለው ወረዳ ማሰሮ ደንብ ነው። ዓባይ በልጅነቱ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ የተወሰደው አባቱ አቶ ዘውዱ ደመቀን እና ቤተሰቦቹን "ለለውጥ እየታገሉ ነው፣ እምቢተኛ ናቸው፣ እየተገዙን አይደለም" በሚል ደርግ አባቱን ወደ ጭልጋ አፍኖ በመውሰድ ማሰር እና ማንገላታቱን ተከትሎ ነው። በወቅቱ ዘውዱ ደመቀ ብቻ አልነበረም ከመንደር ጊዮርጊስ ቀበሌ የታፈነው ምንም እንኳ ከአጭር ጊዜ የእስር ቆይታ በኋላ ከዳንጉራ እስር ቤት የተለቀቁ ቢሆንም አባቱ ደመቀ ሁነኛው፣ ታላቅ ወንድሙ መልካሙ ደመቀ እና ታናሽ ወንድሙ ጌጡ ደመቀም አብረው ታስረው ነበር። ዘውዱ ደመቀ ግን 'ይህ ነው ዋናው' በሚል ተፈርጆ ወደ ጭልጋ ወረዳ አይከል ማ/ቤት ተወስዶ ከ6 ወራት የግፍ እስር በኋላ መፈታቱን ተከትሎ ነው ባለቤቱን ባንች አምላክ በለጠን እና ልጆቹን ይዞ የጓንግን ወንዝ ከማዶ እና ማዶ ሶስትና አራት ረዣዥም እንጨት ጣል በማድረግ በሰራው ጊዜያዊ መሻገሪያ ድልድይ ተሻግሮ ወደ ማዕከላዊ አርማጭሆ ወረዳ ማሰሮ ደንብ ያቀናው። የመጀመሪያ ወይም የበክር ልጅ የሆነው ዓባይ ዘውዱ በጭልጋ ወረዳ መንደር ጊዮርጊስ ተወልዶ በአርማጭሆ ማሰሮ ደንብ ወረዳ ሳንኪ ሚካኤል ነው እድገቱን ያደረገው። ዓባይ የተወለደበት ብቻ ሳይሆን ያደገበት አካባቢም በአብዛኛው በተራራ ሰንሰለት እና በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ ነው። ዓባይ የት ተማረ? የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን እስከ 6ኛ ክፍል የተከታተለው በማሰሮ ደንብ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ሲሆን የ7ኛ ክፍል ትምህርቱን ደግሞ በታች አርማጭሆ ወረዳ ሳንጃ ት/ቤት ነው። ዓባይ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የተከታተለው በባህር ዳር ነው። ይኸውም፦ 1) 8ኛ ክፍል_በባህር ዳር ቁልቋል ሜዳ ት/ቤት፣ 2) 9ነኛ እና 10ኛ ክፍል_በባህር ዳር ፋሲሎ ት/ቤት፣ 3) 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን በባህር ዳር መሰናዶ ት/ቤት እንዲሁም 4) የዩኒቨርስቲ ትምህርቱንም በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፔዳ ካምፓስ የተከታተለ ሲሆን በጋዜጠኝነትና ግንኙነት (Journalism and Communications) ትምህርት ዘርፍ 3.66 በማምጣት በከፍተኛ ማዕረግ እና በሽልማት ተመርቋል። የትግል ሁኔታን በተመለከተ? በተለያዩ ጊዜያት በልዩ ልዩ በመድረክ እና በጽሁፍ ሲያደርገው የነበረው ትግል እንዳለ ሆኖ በዋናነት ከ2005 ዓ/ም ጀምሮ ነው የህወሀት እና ህወሀት ተሸናፊ እና ተንበርካኪ አድርጎ የሰራውን የብአዴን ስርዓትን አምርሮ በመጥላት አንድነት ለፍትህ እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)ን ተቀላቅሎ ታግሏል። በተለይ በህወሀት በሀይል ከአማራ የተወሰደው የወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ እንዲሁም በሱዳን በጎንደር በኩል የሀገር ሉኣላዊነት ተደፍሮ የተወሰደው ሰፊ ለም መሬት እና በተለያዩ አካባቢዎች በአማራ ህዝብ ላይ ይደርስ የነበረው ሁለንተናዊ ግፍ እና በደል ወደ አንድነት ትግሉ በመግባት ከብርቱ ለውጥ ፈላጊ እና የነቁ ጓደኞቹ ጋር በመሆን በአብርሃጅራ ከተማ ቢሮ በመክፈት ጭምር አገዛዙን እንዲታገል ገፋፍቶታል። በለውጥ ትግሉ መስዋዕት ከሆኑት ነፍሳቸውን ይማርና ከእነ ደስታው ተገኘ፣ አንጋው ተገኘ እና ታናሽ ወንድማቸው ባበይ ተገኘ ጋር በመናበብ አገዛዙን ይታገል ነበር። ደስታው ተገኘ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ አገዛዙን ለመታገል ሲመለስ በአብደራፊ/ምድረገነት አካባቢ ባጋጠማቸው ውጊያ ዶ/ር ብርሃኑ ከተባለ የትግል ጓዱ ጋር ስለ አማራ ህዝብ እና ስለ ሀገር ሲል በጀግንነት በክብር የተሰዋ ሲሆን ወንድሞቹ አንጋው ተገኘ እና ታናሻቸው ባበይ ተገኘ ደግሞ እምብኝ ለወገኔ በማለት በመጋቢት 2016 ዓ/ም ኦህዴድ መራሹን የብልጽግና አገዛዝ በነፍጥ ሲፋለሙ በክብር የተሰው ጀግኖች ናቸው። ዓባይ ከእነ እንግዳው ዋኘው፣ ስርዓቱ ለሰላማዊ ትግል ዝግጁ አይደለም በማለት ወደ ኤርትራ በማቅናት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርን ተቀላቅለው ሲታገሉ ከነበሩት ከእነ አብርሃም ልጃለም፣ ከአለልኝ እና ከሌሎችም ጋር በመሆን በምዕራብ ጎንደር ዞን አብርሃጅራ ሲታገሉ ነበር። ከእነ አለላቸው አታለል፣ ቀለብ ስዩም፣ ተገኘ ሲሳይ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ ፈረጃ ሙሉ፣ ሰጠኝ ቢልልኝ፣ አወቀ፣ እንዲሁም ከአነ አግባው ሰጠኝና ከሌሎች ጀግኖች ጋርም በመናበብ አብሮ ለእውነተኛ እና ስር ነቀል ለውጥ ይታገል ነበር። ዓባይ ዘውዱ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ሲታገል ስለደረሰበት እስር፦ (1) በህወሀት ኢህአዴግ ዘመን ከጥቅምት 25/2007 ጀምሮ እስከ ህዳር 2010 ድረስ በፈጠራ የሽብር ክስ 4 ዓመት ከ2 ወር ተፈርዶበት ታስሯል። በአብርሃጅራ፣ በጎንደር 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣በባህር ዳር 9ነኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ በአዲስ አበባ ማዕከላዊ፣ በቂሊንጦ፣ በሸዋሮቢትና በዝዋይ በእስር ተሰቃይቷል። (2) በኦህዴድ ብልጽግና አገዛዝ ደግሞ ስለ ሰፊው የአማራ ህዝብ እና ስለተገፉ ወገኖች ድምፅ በመሆኑ 4 ጊዜ ታስሯል። ይኸውም፦ 1) ሀምሌ 10/2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ አውቶብስ ተራ እና በመርካቶ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ስለምን ለአማራ ተፈናቃዮች ድምጽ ሆንክ በሚል ታስሯል።
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.