uz
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Kanalga Telegram’da o‘tish

Bashewam School Grade 1-8

Ko'proq ko'rsatish
2 784
Obunachilar
+624 soatlar
+317 kunlar
+8630 kunlar
Postlar arxiv
Share '1-- 4ኛ ባለው የትምህርት እርከን በሶስተኛው ሩብ አመት በየክፍሉ 1--5 ደረጃ የወጡ ተማሪዎች.pdf'

በአዲስ አበባ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 22 እና 23/2015 ዓ.ም ይሰጣል በ2015 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ በሆነው አዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ቢሮው ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ ነው፡፡ ተፈታኝ ተማሪዎችን በስነ-ልቦና ከማዘጋጀት ባሻገር በትምህርት ቤቶች ቅዳሜና ከመደበኛ ትምህርት ውጭ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም የተማሪዎችን ስነ-ልቦና ለማዘጋጀት የሚያግዝ የሞዴል ፈተና መሰጠቱን ጠቅሰው፤ በፈተናው አበረታች ውጤት ተገኝቷል ነው ያሉት፡፡ በቀጣይም ተጨማሪ የሞዴል ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ነው የተናገሩት፡፡ ይህን ተከትሎ ሰኔ 22 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና እንደሚሰጥ ዘላለም (ዶ/ር) የገለጹት። የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 75ሺህ 102 ተማሪዎች የኦንላይን ምዝገባ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ በፈተና ወቅት ኩረጃ እንዳይኖር በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸው በመጀመሪያ ዙር የሞዴል ፈተና ወቅት ኩረጃ እንዳይኖር የሚያስቸሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል። በተመሳሳይ የስምንተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 19 እና 20 ቀን 2015 ዓ.ም በከተማ ደረጃ የሚሰጥ ሲሆን፤ 78ሺህ 78 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library

ቀን 19/8/2015 ዓ.ም "የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶ
+1
ቀን 19/8/2015 ዓ.ም "የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡ ፈተናው ልክ እንደባለፈው ዓመት በኹለት ዙር የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር የነበሩ የፈተና ችግሮችን ዘርዝረው ለቀጣዩ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑንና የተፈታኞች መረጃ በአግባቡ እየተደራጀ መሆኑን አብራርተዋል። ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍና አመለካከቱን ለመቀየር፣ ብቁና አገር ተረካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም በ2016 የሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኦን ላይን እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ... TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc