uz
Feedback
ግጥም

ግጥም

Kanalga Telegram’da o‘tish

በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post ADMIN 👉 @Big_jor

Ko'proq ko'rsatish
4 799
Obunachilar
+1224 soatlar
+507 kunlar
+22630 kunlar
Postlar arxiv
#ረስተሽ_ካልሆነ ነግሬሽ ነበረ ነገሬ በዝቶብሽ ረሳሽው እንጂ አንቺም ነግረሽኛል ዛሬ ብረሳውም ረስተሽኝ ስትሄጂ ስላንቺ የፃፍኩት ያሰብኩት በሞላ የተኮረጀ ነው ካለም የተቀዳ ገና ያልተብላላ ረስተሸ ካልሆነ አዝማሪ ወዳለሁ በማሲንቆ ቅኝት ነፍሴን አደምጣለሁ አናልሽ በቀደም አዝማሪ ቤት ሆኜ የጠጁን ብርሌ አፌ ላይ ደቅኜ ከኔ ባርጩማ ጎን አንድ ድንክ ቁጭ ብሏል መላጣውን ሲያዩት ዲያስፖራ ይመስላል አዝማሪው ይዘፍናል ለድንኩ ሰውየ አዲስ ዜማ ፈጥሮ ከባቲ ዋሆየ ‹‹የጎፈሬህ ጫካ መሸፈት ያሰኛል›› ‹‹መለሎው ቁመትህ አክሱምን ያስንቃል›› ድንኩ ወዳጃችን በጎፈሬው ፋንታ መላጣው ያበራል በርጩማ ላይ ቆሞ አዝማሪው ግምባር ላይ መቶ ብር ይመርጋል ከኔ አለፍ ብለው ኣናረጅም ያሉ ሁለት አሮጊቶች ይፍለቀለቃሉ ባዝማሪው ቃላቶች ‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ አንገትሽ ብርሌ›› ‹‹ስከተልሽ ልኑር አርጊኝና ሎሌ›› ነገርና ብቅል ናላውን ያዞረው አንዱ ስክር ያለ ላዝማሪው ጠየቀው ‹‹ጡትሽ ማለት ሎሚ ብለህ የገጠምከው›› ‹ጡትሽ ሀምሳ ሎሚ ልትል ፈልገህ ነው?›› ሁለቱ አሮጊቶች ሁለት ነገር ሰሩ ሰካራሙን ጠጪ ከቤት አስባረሩ አዝማሪው ግምባር ላይ ረብጣ ጋገሩ ህይወትን ስንፈታው መንታ ትርም አዝሏል እውነትን መናገር ከደጃፍ ያስጥላል በውሸት ማሞገስ ሽልማት ያዘንባል ‹‹ አንቺ ማለት ለኔ የምስራቅ ፀሀይ ነሽ ›› ‹‹ንጋት እና ምሽት ቀን የምቆጥርብሽ›› ብየ የጻፍኩልሽ ያንድ ቀኑ ግጥም እርሽው አታስታውሽው ለኔም አልገባኝም አንቺ ማለት ለኔ በቃ አንቺ ማለት ነሽ በልቤ ጎዳና ወክ አድርገሽ ያለፍሽ የሆነ ቀን መጣሽ በሆነ ምሽት ሄድሽ ስትመጪ ግቢ አልኩሽ ስትሄጂ ረሳሁሽ መርሳት በሽታየ መርሳት መዳኒቴ በመርሳት ታምሜ ዳንኩኝ በመርሳቴ አንድ ሰው ነበረ እንደኔ ሚረሳ ሲተኛ ይፅፋል እቃዎቹን ሁሉ የት እንዳኖራቸው ‹‹ጫማየ ቴብል ስር ካልሲዎቼ ደግሞ ጫማ ውስጥ ናቸው›› ‹‹ሸሚዜ ሻንጣ ውስጥ ሱሪየ ወንበር ላይ›› ‹‹ሞባይሌ መሬት እኔ ደሞ አልጋ ላይ ›› በጠዋት ይነሳና ደብተሩን ይገልጣል ሱሪና ሸሚዙን ሞባይል ሰአቱን ካሉበት ያነሳል አንድ ነገር ብቻ ከፃፈበት ያጣል አልጋው ባዶ ሆኗል እናም እንዳልረሳሽ ልፅፍሽ ስሞክር አንቺን ከሌላዋ ለይቼ ማሰፍረው አጣሁ ልዩ ነገር ተመሳሳይ ሀሳብ ባዲስ ገፅ መፃፍ ደብተር መጨረስ ነው ብእርን ማንጠፍጠፍ ይህ የፃፍኩት ግጥም ሀሳብና ቋንቋው ለዛና ፍሰቱ እንዳይሆን የሆነው ላንቺ መታሰቢያ አንቺን እንዲመስል የሳልኩት ስዕል ነው፡፡         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ ዘላለም ምህረቱ

Welcome to the IBM Quantitative Trading Platform Quickly earn the difference through quantitative trading on the platform The
Welcome to the IBM Quantitative Trading Platform Quickly earn the difference through quantitative trading on the platform The most secure quantitative trading platform in 2025 ☄️ Note: The stored value amount initiates the corresponding version and receives a percentage of the current version.For example, with a storage value of 60USDT activated VIP-2 version, the single quantization return is 60×20.41%%=12.2USDT The platform takes 2% of the quantified revenue as operating costs. Official Registration:https://2025ibm.com/#/register?ref=467773

#ታስፈልጊኛለሽ! በተለይ በክረምት ፡ ሙቀት ሲያስፈልገኝ በተለይ በምሽት ፡ የብቻየን ስገኝ ! ብርድና ባዶነት ፡ ተባብረው ሲመጡ ባንች ተገፍትረው ፡ ፈጥነው እንዲወጡ ከላየ ቁጭ በይ ፡ ግርማየ ሞገሴ እቅፍፍፍ ስታደርጊኝ ፡ ትሞቃለች ነፍሴ ጌጤ ነሽ ለአካሌ ፡ ክብርና ውበቴ በይ ነይ ልደርብሽ ፡ ከታናሿ ቤቴ ታ ...ስ ......ፈ ..........ል ..............ጊ .................ኛ .....................ለ .........................ሽ !       ወፍራሟ ጃኬቴ¡         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ መላኩ አላምረው

"To all my Muslim subscribers, I wish you a very Happy Eid! May this special day be filled with joy, peace, and beautiful mom
"To all my Muslim subscribers, I wish you a very Happy Eid! May this special day be filled with joy, peace, and beautiful moments with your loved ones.”         ✨Eid Mubarak!          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

"To all my Muslim subscribers, I wish you a very Happy Eid! May this special day be filled with joy, peace, and beautiful mom
"To all my Muslim subscribers, I wish you a very Happy Eid! May this special day be filled with joy, peace, and beautiful moments with your loved ones.” ✨Eid Mubarak!

#የወንድ_ስንብት ሊሄድ ያሰበ ሰው — ልቡ የሸፈተ በሌት በጽልመቱ ምንም ሳይናገር — በር እየከፈተ እንዳለፈ ክረምት ...እንደ ጠዋት ጤዛ እንደ ቡና ሐሜት ...እንዲሁ እንደዋዛ ሄደ ...ሄደ ....ሄደ ...ሄደ ኮበለለ ይሰጠው  ይሆናል — ዕጣው የተሻለ። እንደኔ ያለው ግን "ደህና ሁኚ" ብሎ — ዕንባውን ያዘራል የኀዘኑን ጨሌ — ሙዳይሽ ይሰፍራል “ቻው” ይላል ዐሥሬ ያለ ምንም ፍሬ... ጓዙን ይሸክፋል ወዲያ ወዲህ ያልፋል... ይስማል ፍዝ ጉንጭ ያቅፋል ልዝብ አንገት — እግሩም አይወጣለት የወንድ ስንብት “መልሺኝ” መሆኑን — ምነው ብታውቂለት?         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ ሄኖክ በቀለ

#የፍቅር_ዘመኑ ወጣቱ ......... አስር – ከሰባቱ ፀሐይን  በጉያህ ጨረቃን  በኪስህ ዩኒቨርስን  ጠቅላዩን በመዳፍህ  ይዘህ ፍቅርን  በቃጠሎ በትንታግ   ታውቃለህ። ወሬዛው........ ሰላሳ – ካምስቱ ፀሐይ  በቦታዋ ጠዋት  ትወጣና  ማታ  ትጠልቃለች ጨረቃም  በምሽት በፀሐይ  ዳረጎት  በልመና  ጨረር አንሳ  ታበራለች። ፍቅርም   እንደልምዱ ከልቦናህ  ያድራል  ከተፈጥሮ  ግንዱ። አዛውንቱ ....... ሰባ – ከስምንቱ ፀሐይ  ከቦታዋ ጥልቁን  ትርቃለች ጨረቃም  ተማፅና  ጨለማ  መግፈፊያ ብርታቷን  ታጣለች። – በፈንታው – ትዝታ  ክራሩን ያለፈ  ቅኝቱን ፊትህ  ላይ ያከርራል ዘላለሙን ላይለቅ ፍቅርን ያላዝናል።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ ዮሐንስ ሀብተማሪያም

#ቢታነፅ_ቢወቀር እኔም አንድሰሞን ልክ እንደሶሎሞን "ሁሉም ከንቱ ከንቱ ነፋስን መከተል" ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል እያልሁ አጨልሜ በራሴ ለግሜ እፈላሰፍ ነበር:: ከዚያ አንቺን አገኘሁ በጉዋሮ በር በኩል: ሰሎሞኔን ሸኘሁ መፈጠሬን ወደድሁ ነፋስ አሳድጄ እንደቆቅ አጠመድሁ:: ከፀሓይዋ በታች :ግልገል ፀሃይ ፈጠርሁ ለኦናው አምፖሌ: ብርሃን አበደርሁ ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ "ከንቱ "የነበረው "አንቱ "ሆኖ ታየኝ:: ለካስ ጠቢብ ቢያስተምረው መከራ ቢመክረው አካሉና ልቡ : ቢታነፅ ቢወቀር ሰው አቅሙን አያውቅም : ካልወደደ በቀር::         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ      ✍ በዕውቀቱ ስዩም

#ጨረቃ_ናት_ፍቅሬ ባልዳብስሽ እንኳ: ሳላይሽ ከከረምኩ ይለኛል ቅር ቅር ህይወቴ ይዛባል ይላል ምንቅርቅር ሰላም ነስተሽኛል: ልክ እንደ ምትሀት እንደ መስተፋቅር፣ የኔ እንደማትሆኚ እያወኩኝም እንኳን ስንት ዘመን ሆነኝ: ልቤ ላይ ከጣልኩኝ የምኞቴን ድንኳን፣ ደግሞ አንዳንድ ግዜ: ብሶት ይወረኛል ለራሴ አዝናለሁ መዝጊያዬን ቆልፌ እንሰቀሰቃለሁ፣ ይኸው ዛሬ ከፍቶኝ... ወደ ውጭ ወጥቼ ከፍቼ የቤቴን በር ጨረቃን እያየሁ ግጥም ልፅፍ ነበር፣ ግና የሀሳቤን መቼ ከወንኩና ፈዝዤባት ቀረሁ መፃፌን ተውኩና፣ ይገርማል አንዳንዴ... ስንት ዘመን ሙሉ: በፍቅርሽ ሰቀቀን ስንገላታ ኖሬ በ2 ደቂቃ ተፋሁሽ አንቅሬ በይ ደህና ሰንብቺ: ከእንግዲህ በኋላ ጨረቃ ናት ፍቅሬ::         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ እዮብ ዘ-ማርያም

#ትወጂኛለሽ እኔ እየፈራሁሽ፣ ልቤ እየደፈረሽ እኔ እየናቅኩሽ ፣ ልቤ እያከበረሽ እኔ እየጠላሁሽ ፣ ልቤ እያፈቀረሽ ከራሴ ስጣላ... እኖራለሁ እንጂ ፣ የልቤን ሀቅ ይዤ አንድም ቀን አልፎልኝ.... ልቤን እንደልቤ ፣ አላውቅም አዝዤ፡፡ አንቺም ልክ እንደኔ... ልብሽን እንደልብ ፣ ማዘዝ አትችይም ልብሽ ይወደኛል ፣ ጠላሁህ ብትይም፡፡ ባትወጂኝም እንኳን... የመጥላትሽ መጠን ፣ የቱን ያህል ቢያክል አንቺን አላምንሽም ፣ ልብሽ ነው ትክክል፡፡         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

#የዘመን_ፈተና ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤ የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤ የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡ የሰው ሃሳብ መብላት፤ የሰው ቃል መጠጣት ፤ የሰው ህልም ማየት፤ መቆም የሰው ቁመት፡፡ ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤ የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤ የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡ በሰው አድማስ ማሰስ፤ በሰው ድምፅ መቀደስ፤ በሰው ሽንፈት መፍረስ፤ መሾም በሰው መንገስ፡፡ ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤ የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤ የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡ የሰው ፍርሃት መራድ፤ የሰው ንዴት ማበድ፤ የሰው እዳ መክሰር፤ የሰው ሞት መቀበር፡፡ ከራስ ጋር መግባባት ከራስ ጋር መስማማት፤ የራስ ህይወት መኖር መሞት የራስን ሞት፤ የዘመኑ ረሃብ የዘመኑ ቅቅት፡፡ ታመሃል ሲሉ እህ ዳንክ ሲሉ አሃ፤ ገነት ሲስሉልህ በጠፉ በረሃ፤ አጣህ ሲሉህ እህ አለህ ሲሉ አሃ፤ ሆድክን ሲሞሉልህ በቀቢጸ አመሃ፤ ሄድነ ሲሉህ እህ ቀረን ሲሉ አሃ፤ አለን ሲሉ እህ ሄድነ ሲሉ አሃ፤ ቆምነ ሲሉ እህ ሮጥን ሲሉ አሃ፤ እህ አሃ እህ አሃ እህ እህ አሃ አሃ፤ በመንገድ በርግገህ በመንገድ ቀረሃ፡፡         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ        ✍ ነብዩ ባዬ

#ግን_አንድ_ሰው_አለ እርጅና ሲጫንሽ እድሜ ተጠራቅሞ ፥እንዳስም ሲያፍንሽ ሽበት እንዳመዳይ በጭንቅላትሽ ላይ በድንገት ሲፈላ ያይንሽ ከረጢቱ ፥ በንቅልፍሽ ሲሞላ ምድጃ ዳር ሆነሽ መጣፍሽን ከፍተሽ ያለፈውን ዘመን ፥ ከፍተሽ ስታነቢ የኔን  ቃል አስቢ፦ ስንቶች አፈቀሩት ፥ በሐቅ በይስሙላ የገፅሽን አቦል፥ የውበትሽን አፍላ ግን አንድ ሰው አለ ከሌሎች ወንዶች ጋር ፥ ያልተመሳሰለ በእፁብ ድንቋ ነፍስሽ ፥ ፍቅር የነደደ የመልክሽ ፀደይ ሲያልፍ ልክ እንደ መስቀል ወፍ ፤ጥሎሽ ያልነጎደ።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ በዕውቀቱ ስዩም

#የፍቅር_ቃጠሎ ጉንጭሽ ፅጌረዳ ሞቆት የፈነዳ፤ አይንሽ የጠዋት ጨረር የበራ ማለዳ፡፡ የማትጠገቢ የሥንዴ ራስ ዛላ አገዳ ጥንቅሽ፤ ጠብ አትይ አንጀቴ ባኝክ ብመጥሽ፡፡ ቆንጀ ነሽ አንቺዬ እሳት ነበልባል ነሽ ንዳድ ባከላቴ፤ ሆነሻል ሙቀቴ፤ ሆነሻል ህይወቴ፡፡ የጋለው ትንፋሽሽ፤ የሞቀው ምላስሽ፤ ማርኮኝ በከንፈርሽ፤ እጄን ሰጥቻለው፤ እስረኛ ሆኛለው፡፡ ያንቀጠቅጠኛል ወባ ቅናት ገብቶ፤ ልቤን አስፈራርቶ፤ ትኩሳት አምጥቶ፡፡ ፍቅርሽ አቃጠለኝ በመልክሽ ልተክዝ፤ እቀፊኝ ልቀዝቅዝ፤ ንከሺኝ ልደንዝዝ፡፡         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ ገብረ ክርስቶስ ደስታ

#Ad Only for risk taker and interested 👉Launched March 13 👉Minimum investment 600 birr 👉100 birr registration bonus daily income 125 birr https://www.fanucvip.net/h5/reg/channelId/50150/top/B2J1GS.html

#treasure የዶግስ ፕሮጀክት ነው እየባተለ ነው። እንዲሁም አሁን ቫይራል ሆነዋል። ለመጀመር ከታች ያለው ሊንክ ይጠቀሙ https://t.me/treasury_official_bot/app?startapp=5305703538

#እስከዚህም_ፍቅርሽ እስከዚህም ፍቅርሽ: ከሰንደል ጭስ በላይ: ደምቆ የማይገዝፈው: ምንሽን ልፃፈው ? እስከዚህም ፍቅርሽ በጧት የረገፈው: ከዕድሜ እሬሳ ውጭ ዋኝታ ምኑን ታውጣው ነብሴ ከባለፈው ? እስከዚህም ፍቅርሽ: ዘመን ያሳረጠው: ምኑን አስታውሼ ሣጌን እየማኩኝ : እንባዬን ልዋጠው ? እስከዚህም ፍቅርሽ ሲነድፍ ያለሰንኮፍ: መታሁ ቢልም ለኮፍ: እንኳንና ሰምበር ስምሽስ ማን ነበር ?         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ኑረዲን ኢሳ

#አቅፌ_ልሸኘው ህልሜን ካመከነ ማገሬን አላልቶ፥ ቃሉን ካፈረሰ አደራውን በልቶ፥ መውደዴን በመውደድ ካልመለሰች ልቡ፥ ፍቅሬን ረግጦ መሄድ ከሆነማ ሀሳቡ፥ ክፉ ሳልናገር መጥፎ ቃል ሳይወጣኝ፥ ፊቴን ሳላጠቁር ማኩረፍም ሳይቃጣኝ፥ ደረቴን ሳልደቃ አመድ ሳልነሰንስ፥ ከመሬት ሳልተኛ ጥቁር ልብስም ሳለብስ፥ አንገቴን አልደፋ ከቶ ለምን ብዬ፥ ቀን ጨለመብኝ አልል አይፈስም እንባዬ። ጌታ ካልፈቀደ ካልሰጠኝ አጣፍጦ፥ መች በግድ ይሆናል ፍቅርን ተለማምጦ። ደስታው ደስታዬ ነው ሀዘኑም ሀዘኔ፥ ሀሴት ካደረገ በመራቁ ካይኔ፥ መሄድ ከኔ መሸሽ ከሆነ ሚመኘው፥ ላፍታ አይከፋብኝ ሁሌ እያፈቀርኩት አቅፌ ልሸኘው።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

#መለያየት_ማለት ይኸው ትላንትና ከትላንትም በስትያ ያዩሽ ሰዎች ሁላ ከእቅፌ ጉያ ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ እባክሽ የኔ አለም!! ፈጥነሽ ንገሪያቸው ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው ለኔ ና ላንቺ እኮ መለያየት ማለት በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት..... ያለመተያየት መፋቀርም ማለት በምናልባት ተስፋ የምትቆም ህይወት ዘወትር....ዘወትር ምናልባት ምናልባት እያለች የምትኖር ህይወት በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት በታስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን ብለሽ ንገሪያቸው.... ልቤና ልቦናው ተጣብቀዋል በያችቸው እንጂ በኛ መሀል መለያየት ማለት በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት.... በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ ኤፍሬም ስዩም

#የባከነ_ሌሊት!!!! ወይ ሮንድ አላደርኩ ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ የባለጌ ወንበር  ኮርቻ አልተሳፈርሁ ወይ ሰአታት ቁሜ ቤተክስያን ስሜ ሰይጣን አላሳፈርሁ። ሌቦች ደብድበውት አንዱን ምስኪን ላሥር ባምቢስ ድልድዩ ሥር ቆስሎ የወደቀ ገላው በላዩ ላይ  እንደጨርቅ ያለቀ ፊቱ ተሸፍኖ  በደምና አቧራ "በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ ምስኪን አባወራ ብብት ሥር ገብቼ አፋፍሼ አንስቼ ተሸክሜ አድኜ ስፈልግ አምቡላንስ ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ ወይ ምግባር አልሠራሁ ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ  ወይ ፅድቅ አላፈራሁ። አንድ በትረ-ሙሴ ሁለት ስስ አሎሎ ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ ሲባክን ዝምብሎ " እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ" የምትል መለሎ ልቤን ሳትሰውረው አልጋየን ሳትሰብረው። ወግ ቢጤ ሞንጭሬ ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ " እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ። አንዲት ሴት- አዳሪ  ቺቺንያ ምንገድ ላይ እድሉዋ ሰባራ  ሰውነቱዋ አማላይ ካፍያውና እንባዋ  ተጋግዞ ሚያረጥባት ደምበኛ ስትጠበቅ  ደመኛ ጥሎባት አምስት ደፋሪዎች  ከበው ሲያዋክቧት ሲገፉ ሲስቧት " እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን ልመናዋ ስቦኝ እንዳበጀ በለው   በደሏ አንገብግቦኝ ከሁዋላ ደርሼ ነበልባል ለብሼ  ነበልባል ጎርሼ እንደብሩስሊ  እንዳየሩ ጋኔን እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን በማረግ ቃኝቼ ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ። ድል ሳላስመዘግብ ውጥረት ሳለረግብ ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ ያለምንም ጣጣ  ያለምንም ፀጋ አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ በእውቀቱ ስዩም

#ለጤዛ_ተዋድቀን "እድሚያችን ሰባ ነው ቢበዛም ሰማንያ" ይህም ኑሮ ሆኖ ጠዋት ማታ ፍልሚያ አንዱ ካንዱ ጥዋ: ጥቃት የቀመሰ በየደጃፉ ላይ ምሽግ እየማሰ ጦር እንደ ቄጤማ እየነሰነሰ መንደሩን ሸንሽኖ ባጋም እሾህ ቅጥር ወገን እያስለየ ባሰለፈን ቁጥር ጤናችን ሲሸረፍ ቀናችን ሲዘረፍ የት ሸሽተን እንትረፍ የትገብተን እንረፍ? በዶፍ ዝናብ አገር ለጤዛ ተዋድቀን ሰላም እንደራበን ደስታ እንደናፈቀን ትግላችን ሰልፋችን ያከትማል አንድቀን::         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ ✍ በእውቀቱ ስዪም