ግጥም
Kanalga Telegram’da o‘tish
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post ADMIN 👉 @Big_jor
Ko'proq ko'rsatish5 412
Obunachilar
+524 soatlar
+457 kun
+18330 kun
Ma'lumot yuklanmoqda...
O'xshash kanallar
Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Sentabr '26
Sentabr '26
+125
0 kanalda
Avgust '26
+289
4 kanalda
Get PRO
Iyul '26
+335
4 kanalda
Get PRO
Iyun '26
+275
3 kanalda
Get PRO
May '26
+315
4 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+178
1 kanalda
Get PRO
Mart '26
+199
5 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+87
3 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+107
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+129
1 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+133
1 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+150
1 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+126
1 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+112
2 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+137
2 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+160
1 kanalda
Get PRO
May '25
+199
3 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+169
3 kanalda
Get PRO
Mart '25
+170
3 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+186
3 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+353
3 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+394
5 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+431
6 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+373
5 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+271
6 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+404
12 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+173
15 kanalda
Get PRO
Iyun '24
+108
1 kanalda
Get PRO
May '24
+172
15 kanalda
Get PRO
Aprel '24
+388
28 kanalda
Get PRO
Mart '24
+376
26 kanalda
Get PRO
Fevral '24
+139
15 kanalda
Get PRO
Yanvar '24
+205
22 kanalda
Get PRO
Dekabr '23
+601
41 kanalda
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 15 Sentabr | +5 | |||
| 14 Sentabr | +9 | |||
| 13 Sentabr | +5 | |||
| 12 Sentabr | +5 | |||
| 11 Sentabr | +15 | |||
| 10 Sentabr | +13 | |||
| 09 Sentabr | +11 | |||
| 08 Sentabr | +8 | |||
| 07 Sentabr | +3 | |||
| 06 Sentabr | +6 | |||
| 05 Sentabr | +10 | |||
| 04 Sentabr | +3 | |||
| 03 Sentabr | +16 | |||
| 02 Sentabr | +7 | |||
| 01 Sentabr | +9 |
Kanal postlari
#ማነው_ስልጡን_ታዲያ?
ቀሚስ ገዛሽ አሉ በውድ ሸምተሽ፣
ለምን አለበስሽም? እንደናትሽ ፈትለሽ?
ጭኗ እዝርት አያውቀው ይልሻል ሀገሩ፣
ስለምን አቃተሽ? ከእናት ስር መማሩ?
አለላ ቢሰጡሽ ሰበዝ ገዝተው ዛሬ፣
መስፋቱ ተስኖሽ ትሪ ሞላ ሀገሬ።
አገልግል መሶቡ የእናትሽ ፈጠራ፣
ተዘነጋሽ እንዴ? እንቅጩን እናውራ?
ስንደዶ ተገዝቶ ቢሏት ስፊ ሰፌድ፣
ተጠቀመችበት እሳቱን ለማንደድ።
አንች የከተሜ ልጅ ልውሰድሽ ወይ ገጠር፣
እራስ ፈትሎ መልበስ ከናፈቀሽ ማማር!
ሗላ ቀር ይሏታል ባለሀገሯን ጉብል፣
ከፊት ግን ቀድማለች ተውባ በባህል፣
አንች ገዝተሽ ልበሽ ሰልጥኝ በመግዛት፣
የገጠሯ እህቴን በሙያ ላትቀድሚያት፣
ፈትላ ትለብሳለች ሰፍታ ትበላለች፣
ከተሜዋ እፈሪ ቀድማሽ ሰልጥናለች።
ውብ ኢትዮጵያዊት በኩታ ደምቃለች፣
የእናቷን ጥበብ ውርስ ጠብቃ ዘልቃለች!!!
ያንች ማወቅ ከንቱ ሸምቶ መልበስ ነው፣
እስኪ እንጠያየቅ ማነው የሰለጠነው?!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ
| 2 | #መጭውን_ጠበቅሁት
ከማዶ እሚመጣው፥ ዘመድ ነው እንግዳ
ከላይ የተለጋው፥ ኳስ ነው ወይስ ናዳ
ብየ መች ጠየቅሁኝ
መጭውን ጠበቅሁት
ድንጋይ ላይ ቁጭ ብየ፤ ጸሀይ እየሞቅሁኝ፥
መከራም አላጣም፥ ተድላም አልጎደለኝ
ደንታ ነው የሌለኝ፥
ባካል በስሜትም፥ ታሞ ላገገመ
ወድቆ ለተነሳ ፥ እየደጋገመ
ከገዛ ጉድጓዱ ፥አጽሙን ለሚለቅም
ሞትም ብርቅ አይደለም፥ ትንሳኤም አይደንቅም ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም | 572 |
| 3 | #ሰው_ማጣት_ነው_ክፉ!!
የኔን ሆድ ለመሙላት አትሽቀዳደሙ
ይልቅ ፍላጎቴን ጭንቅላቴን ስሙ
እርሱ የሚላችሁን ህመሙን አክሙ
ሰው ነው የጎደለው ሰው በመሆን ቁሙ
ስጋ ጉርስ አያጣም አሽቃብጦም ይበላል
ሰው ምግብ አይነፍግም አሽሟጦ ይሰጣል
ጭንቅላት ነው እንጅ ሰው አምጡ የሚለው
ሆድስ ስልቻ ነው በህል ነው የሚቆመው
ከርስማ ይሞላል ለምኖም ይጠግባል
ከባሰበት ደግሞ ሀገርን ይዘርፋል!
ሆዴ መች ጎደለ ሳይሰራም ይጎርሳል
ቁራሽ ዳቦን በልቶ መኖርን ለምዶታል
እኔን የሚርበኝ የሚያንገበግበኝ
አላስተኛ ብሎ እንቅልፍ የሚነሳኝ
ሰው መሆን ጠፍቶብኝ ግራ ቢገባኝ ነው
ሰው ሁኑኝ እያልኩኝ ሰው የምፈልገው
ሆዴን የሚሞላ ወዳጅ መቸ አጣሁኝ
ምግብን የሚሰጥ ሰው እኔ አልጠየኩኝ
እውነት የሚያስተምር አጥቼ አለቅሳለሁ
ለመኖር በመቅመስ ገዜ እጠብቃለሁ!!!
በድቅድቅ ጨለማ ፀሀይ እሞቃለሁ
ውሃንም በወንፊት ስቀዳ እኖራለሁ
ሰው በሌላት ሀገር ሰው እየናፈኩኝ
ከተከመረ ጭድ መድፌ እየፈለኩኝ
በቀን ፋኖስ ይዠ መብራት አበራለሁ
ደግሞ በጨረቃ ፀሐይ እሞቃለሁ!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 962 |
| 4 | 🌼እንኳን ለ 2019 አዲስ ዓመት በሰላም፣ በጤና እና በፍቅር አደረሰን!🌼
አዲሱ ዓመት፡ የጤና፣ የሰላም እና የፍቅር፤
የታሰቡት መልካም ምኞቶች ሁሉ የሚሳኩበት፤
የስኬት እና የበረከት ዓመት ይሁንላችሁ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
🌼🌼🌼መልካም አዲስ አመት!🌼🌼🌼 | 1 039 |
| 5 | #እኔ_ወድሻለሁ
እኔ ወድሻለሁ
ታስሮ እንደ መፈታት
እንደ ጣኦስ ውበት
እንደ ዝሆን ብርታት
ዳዊትን ከጎልያድ
ደርቦ እንደመምታት፤
እኔ ወድሻለሁ
ጦም ውሎ እንደመጉረስ
ወልዶ እንደመታረስ
ቶምቦላ እንደመድረስ
ካላሙዲ ንብረት
ግማሽ እንደመውረስ፤
እኔ ወድሻለሁ
እንደ መቅደስ እጣን
እንዳፍለኛ ስልጣን
ያንች ልዝብ ሰይጣን።
እኔ ያንች ቡዳ
ያንች ልዝብ ሰይጣን።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ገብረ ክርስቶስ ደስታ | 1 318 |
| 6 | #እኔ_ሞኙ_ልጅሽ
አንችን ገላጭ ቅኔ አንች ገላጭ ዜማ
የውበትሽን ጥግ የክብርሽን ግርማ
ብሞክር ባስሞክር በስንኝ ቋጠሮ
ቤት ባልመታ ግጥም በቃል እጉርጉሮ
በሀገር መስዬ ላወድስሽ ብጥር
አልገልጽልህ አለኝ እኔስ ያንችን ፍቅር
አናት ከማለት ውጭ ሌላው ቀለለብኝ
ብጽፈው ባጽፈው ሚዛኑ አነሰብኝ!
የፍቅርሽን ልኬት የደግነት ጥልቀት
የትኛው ቃል ይሆን ገላጭ እናትነት
ቃል አዋቂ ፈለኩ የተማረ አብዝቶ
ከውስጡ የሚፈስ ዜማ ቅኔ ሞልቶ
ግን አላረካኝም ውበቱ አነሰብኝ
ለደግነትሽን ክብር በቂ ቃል አጣሁኝ
ያወቁ የበቁ ሽህ አመት ቢመክሩ
ቋንቋ ላይ ተራቀው አብዝተው ቢማሩ
እናት ነው ውብ ቃሉ ረቂቅ ቀመሩ
ሌላ ስም የላትም አትመራመሩ!
አልኳቸው እናቴ እኔ ሞኙ ልጅሽ
ቢሳነኝ በቅኔ በዜማ ልገልጽሽ
ሌላ ቃል ፈልጌ አስፈልጌ ባጣ
ከደጋ እስከቆላ ወርጄ ስወጣ
ከፊደላት ድምር እናት የሚል መጣ
እየደጋገመ እርሱው ከአፌ ይውጣ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 1 501 |
| 7 | አንዳንዴ...
ባልተገራ ፈረስ
በፈጣን ድንጉላ
ኑሮን ባቦ ሰጠኝ
ህይወትን በመላ
በዚህ በኩል ሲሉህ
ንጎድ ወደ ሌላ፤
እስከመቼ ድረስ
ዳር ዳሩን መራመድ ፤ በጭምት ሰው ስሌት
በክብር ካልመጣ፤ ሞክረው በቅሌት
ሰው ቅፅር አይደለም፤ በእሾህ የታጠረ
እንድትጥሰው ነው፤ ህግ የተፈጠረ::
አይሰለቺህም ወይ
መኖር በተጠንቀቅ
አንዳንዴ
አየር ላይ ደንሰህ ፤ በግንባርህ ውደቅ
አንዳንዴ
ኮርቻህን እርሳት
ርካህብህንም ሳት
ፋይዳ አይጠፋምና፤ ወድቆ ከመነሳት !
በትቢያ ላይ ወድቀው
የተነሱ አሉና፤ በሉል ባልማዝ ደምቀው !
አንዳንዴ
ልጉዋሙን ልቀቀው!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም | 1 692 |
| 8 | #ማሪኝ_እንዳትለኝ
ውዴ ትዝ ይልሀል ያኔ እንደጀመርን
እኔና አንተ ሁነን ፍቅርን ስንወጥን
ወሬህ ማይጠገብ ንግግርህ ጣፋጭ
የጨዋታህ ለዛ ቃላቶችን መራጭ
በስሜንኳ አጠራኝ ቁልምጫህ የብቻ
አስተዋይነትክ የትም የለህ አቻ
ቀልቤን ማንነቴን እኔነቴን ወሰድክ
ልቤንም ሰጠሁህ ሁሉን ተቆጣጠርክ
ባሌ ብቶን ብዬም አብዝቼ ተመኘሁ
ያንተ ሆኜ ልኖር ህይወቴንም ሰጠሁ
አንተ ግን °°°
መሸነፌን አይተህ ባንተ መረታቴን
መውደዴን አቅለህ አሳንሰህ ፍቅሬን
ሌላ ሰው ሆንክብኝ የማላቀው ትናንት
ፍፁም ተቃራኒ ካለፉት ግዚያት
ያሳየኸኝ ነገር ያ ሁሉ ቀነሰ
ፍቅሩም ቁልምጫውም እያደር አነሰ
መምረጡም ቀረና ቃላቱን ማሳመር
በእሾክ ንግግርህ ታሳምመኝ ጀመር
ልቤን ስለፈተሽክ የመውደዴን መጠን
የትም አቴድ ብለህ ጀመርክ መጨከን
ምን አጠፋሁ ውዴ?
ታምኜልህ በኖርኩ ሁሉን ነገር ትቼ
ጥፋት ስተትህን በይቅርታ አጥፍቼ
ሁሉን ረስቼ
ቁም ነገር ባሰብኩኝ ለነጋችን በሚል
አብረን እንድንኖር ጎጆ እንድንደለድል
ምነው የምወድህ ታድያ ምን አደረኩ
ነውር ሰራሁ እንዴ አንተን ስላፈቀርኩ
ያ ሁሉ ሳያንሰኝ
ላንተ ስል ደክሜ ላንተ ስል ታምሜ
ከሳቅ ተጣልቼ ጠፍቶ ያ ሰላሜ
በእንባ ስገፋ ዕልፍ የሆኑ ቀናት
ሀዘን ያጀባቸው ምሽትና ንጋት
አንተ ግን ጉዳቴን ሰምተህ ህመሜንም
እንዴት ሆነች እንኳ ብለህ አልጠየክም
አንደምን አስቻለህ...?
እንዴትስ አራራህ ...?
እንዲህ ነበር እንዴ ለኔ የሚገባው ?
ለፍቅርህ ለሆንኩት ምላሹና ዋጋው?
ብቻ እንዲ ስትገፋኝ ደርሰህ ስታርቀኝ
ደስታ እንደናፈቀኝ
ባንተ ተስፋ ስቆርጥ ሁሉም ነገር አልፎ
ልቤም ከጉዳቱ ከስብራቱ አርፎ
መከፋቴም ቀርቶ እምባዬም ሲደርቅ
ውስጤም ያንተን ፍቅር ከልቡ ላይ ሲፍቅ
ማሪኝ እንዳትለኝ ከረፈደ ገብቶህ
አዲስ ቀን ሲጀምር ልቤ አንተን ረስቶህ
ሂዎትን ሲቀጥል አንተን ላንተ ትቶህ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ | 1 926 |
| 9 | #እኔ_ልማልብሽ
አብሬሽ እያለሁ በፍቅር ሰክሬ
ልሙትልሽ ያልኩሽ ውዴ ቀባጥሬ
ዛሬ ፀፅቶኛል እውነቱን ልገርሽ
አንቺም እንዳታዝኝ በቃ ልኑርልሽ
ማይብኝ በስሜ ብየ የነገርኩሽ
ዛሬ ግን ሳስበው እኔ ልማልብሽ
አፅምሽ እንዳያዝን በብቸኝነቴ
በሀዘን ተጎድቶ ሳስቶ ሰውነቴ
ይረሳኛል ብለሽ አታስቢ ፍቅሬ
ከጓደኛሽ ጋራ ብኖር ነው አብሬ
ከዚያ ውጭ በፍጹም ከአንቺ ሌላ ማሬ
ድንገት እርሷም ብትሞት ከጓደኛዋ ጋር ብጀምር ነው ፍቅሬ።
እመኝኝ¡¡¡¡¡ ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 2 065 |
| 10 | የማይወዳደር እኩያ የሚያጣ
ከልቤ ግርጌ ስር አንዳች ስሜት ወጣ
ተሰማኝ ወደድኩህ ያንተን ጣዕም ለየሁኝ
ቆዳዬ ቀመሰህ ምላሴን ከዳሁኝ
ከየትኛው አካሌ ፍቅርህ የወደቀው
የሚያርበተብተኝ ጥፍሬን የሚነዝረው
አካልስ አለ ወይ የሚታይ ሚቀመስ
ሴትነት ገላዬን ነክቶ ሚያጎለምስ
ንገረኝ አንተዬ ከደጅ እንዳያድር ዳስም ልጣልለት
እንዲህ ያለ ፍቅር አያድርም ከኔ ቤት
በአዳፋዬ ባያድፍ ንፁህ ጥሩ ፍቅርህ
ከቆሸሸ ገላ ከዚህ በድን ይሽሽ
እንዲህ ያለ ልመና ሚዛን አያነሳም
የፍቅር ባህሪ ዙፋንን አይሻም
የት ጋር ነው የሚሰማኝ ምኔን ነው የያዝከው
የት ጋር ነው ያገኘኸኝ ምኔን ነው ያጣኸው
ብቻ ከልቤ ስር ስሜቴ ይፈልቃል
የደረስክበትን ያልደረስክበትን
ረቂቁ ፍቅርህ እሱ ብቻ ያውቃል።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ረድኤት ተረፈ | 2 292 |
| 11 | #የእድሜ_ሌባ!!!
ከህይወት ሰሌዳ ከእድሜ ያልተማረ
በሽበቱ ደምቆ በአንቱ ያልከበረ
ኮረዳ ፍለጋ ዘቅጦ የዛከረ
የእድሜ " ፐ " ላይ ደርሶ ግን የደነቆረ
በቅሌት ጎዳና የሚመላለሰው
የትዳሩን ዋጋ አንሶ ያሳነሰው
ንሯል አትበሉኝ በከንቱ እድሜ ቁጥር
ሳይኖር የሞተ ነው ያልታደለ ፍቅር
ከልጆቹ እኩያ አስረሽ ምችው ዜማ
የሚርመሰመሰው በሀብት ከተማ
እድሜውን ዘንግቶ ቁልቁል የወረደ
ጤነኛ ምትሉት ግን እርሱ ያበደ
የምትሰግዱለት ሲወጣ ሲገባ
መሆኑን እወቁ እርሱ የእድሜ ሌባ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 2 443 |
| 12 | #እስክትመጪ_ልበድ
ፍቅር አበደ አሉ መውደድ እንዴት ያብዳል፤
ማበድ የሚሉት ቃል ላበደው ይቀላል፡፡
ታችአምና መስከረም አንቺን እንደሸኘሁ፤
ማን አለብኝ ብዬ ራሴን ጥያለሁ፡፡
የኖርንበትም ቤት ሊበላኝ ደረሰ፤
የተጫወትንበት እቃቃው ፈረሰ፡፡
በትናንት ረመጥ ዙሪያዬን ታጥሬ፤
ከጎጆ የሸሸች ስደተኛ አፍቅሬ፡፡
ከጎዳና ልውጣ ልሩጥ ጨርቄን ልቅደድ፤
ማትቀሪ ከሆነ እስክትመጪ ልበድ፡፡
እብዱና ጤነኛው በሌበት ሀገር፤
ከአንድ ቤት ሲያድሩ ቀልድና ቁም-ነገር፡፡
ሰው በዚች ሀገር ላይ አ..በ..ደ ሚባለው፤
………………………….ጨርቁን የቀደደ፤
…………………………እርቃኑን የሄደ፡፡
…………………………ፀጉሩን ያጎፈረ፤
………………………..ጎዳና ያደረ፡፡
……………………….ከሰው ያልቀረበ፤
……………………….ምግብ የተራበ፡፡
……………………….ብቻውን ሳቀ፤
……………………….ዝናቡን ፀሀዩን በአንድ ላይ የሞቀ፡፡
……………………….መሆኑን አውቃለሁ፡፡
በእዚች ሀገር ሰው አ..በ..ደ ሚባለው፤
ከላይ ያልኳቸውን ፎርም የሚያሟላ ነው፡፡
……………………….እናልሽ ዓለሜ!
ማበዴ እንዲታወቅ ጨርቄን ቀድጃለሁ፤
……………………….እርቃኔን ሄጃለሁ፡፡
ፀጉሬን አጎፍሬ ጎዳና አድሬያለሁ፤
እብደቴ እንዲያሳምን ብቻዬን ስቄያለሁ፡፡
በሰው አሉባልታም ልቤ ከሚደማ፤
መኖር ይሻለኛል አብዶ በጨለማ፡፡
ፋኖስ እንዳለኩስ ይዘሽው ጠፍተሻል፤
አፍቃሪዬም ያልሽው ጨርቁን ጥሎልሻል፡፡
ከሰው ሳልስማማ ከሰው ሳልጠጋ፤
ክረምቱ አለፈና ደግሞ መጣ በጋ፡፡
ፀጉሬን አንጨበረርኩ ፂሜን አጎፈርኩኝ፤
ልብሴን ቀዳድጄ በናፍቆት አበድቁኝ፡፡
ከቆሻሻ ዋልኩኝ ገላዬ ከረፋ፤
በእብደት ስጠብቅሽ በጭላንጭል ተስፋ፣
ከመንገድ ባላይሽ አዲስ ጎህ ሲቀደድ፤
ሰው መቅረቤን ትቼ እስክትመጪ ልበድ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ | 2 645 |
| 13 | #አስታምምሻለሁ
ደስስስስስ . . . ይለኛል ባንቺ፡፡
እንደአራጣ ብድር፣
ህግ ተላልፌ፤
አተርፋለሁ ብዬ፤
የእጄን በትኜ፣ በተስፋ ታጅዬ፤
ተአምር ያምረኛል፣ በፈጣሪ አምናለሁ፤
‹‹ማፍቀሬ ይባረክ››፣ ሱባኤ ገባለሁ፡፡
ተአምር ያምረኛል፤
ፍቅርሽ ደስስስ ይለኛል፡፡
ቅርርርርር . . . ይለኛል ባንቺ፡፡
እንደክረምት ጎርፍ . . . .
ደመናው ሲገፍፍ፣
መስከረም ሲጠባ፣ አደዩ ሲረግፍ፤
ብትደርቂስ እያልኩ፣ ከልቤ ሸለቆ፤
ዛሬያችን ጸዳሉ፣
ነገ ላይ ደለሉ፣
ከአድማሴ ግርጌ፣ በእጦት ጨፍቆ፤
አቁሞ ያስቀረኛል፤
ፍቅርሽ ያስፈራኛል፡፡
እና ስለፍቅርሽ ...
ባንዱ ጎኔ ተስፋ፣
ባንዱ ጎኔ እጦት፣
እንደእርጥብ ሌጦ፣ ግራ ቀኝ ገድግዶኝ፤
አስታምምሻለሁ፣ አደርገው ቸግሮኝ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በድሉ ዋቅጅራ | 2 460 |
| 14 | #ልጫር_ልሞጫጭረው!!!
ቃላት አሽሞንሙኖ በፊደላት ደምቆ፣
በምሁር ቃል ጠቀስ ቢመጥቅ ተራቆ፣
ቅኔው ቢወሳሰብ አንባቢ ካልፈታው፣
ጠቢባዊው ሁሉ ለማነው የሚጽፈው ?
ህግጋት ጠብቆ ቀለማትን ቆጥሮ፣
ምጣኔን መጥኖ ሀረጋትን ቋጥሮ፣
ምሁሩ ወንድሜ ቅኝት ተከትሎ፣
እኔን ፊደላዊ ከጥበብ ነጥሎ፣
እርሱ ባወቀው ልክ መብቴን ከልሎ፣
ሲከሰኝ ይውላል እንዳትገጥም ብሎ።
አንተሙ ለተማሩት ለተመራመሩ፣
እኔም ለቢጤየ ፊደል ለሚገድፉት፣
በተሰጠን ድንበር እውቀታዊ ልኬት፣
አንተም እንዳዋቂ ሳድስን ዝለላት፣
እኔ ግን ስወዳት ስን እንዴት ልጣላት?
ለስሜ መጠሪያ ሁልጊዜም ከፊት ናት።
አንተም ለተማሩት ለተመራመሩ፣
ስንቴም እጭራለሁ ፊደል ለሚገድፉት፣
ግን ማወቅ ጥሩ ነው አለማወቅ ክፉ፣
ሳያውቁ አውቂያለሁ እረዘመ ሰልፉ፣
አንተ አስተምረኸኝ ለእውቀት እስከበቃ፣
ልጫር ልሞጫጭረው አትከልክለኝ በቃ!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 2 509 |
| 15 | #ተረሳሽ_ወይ
ምነው ተረሳሽ ወይ ያሳለፍነው ሁሉ፣
እኔ እንዳልረሳዉ ያቃጭላል ቃሉ፣
ውዴ ፣ ፍቅሬ ፣ የኔ ይህ ሁሉ ቀረና ፣
ሆድሽ ቂም አርግዞ ተለየሽኝና ፤
ጆሮሽ ማይወደውን የሰው ወሬ ሰምቶ ፣
የመጀመሪያውን የ'ውነት ፍቅሩን ረስቶ ፤
እስቲ ላስታውስሽ ተረሳሽ ወይ ፍቅሬ :
ታክሲ ተቀምጠሽ እያለሽ ከጎኔ ፣
ያንን ውብ አይንሽን እያየሁኝ በዐይኔ ፤
ወክ ያረግንባቸው እነዛ ምሽቶች
ሊነጥፉ የማይችሉ ውድ እንቁ ቀናቶች
የነፋሡ ቃና የወፎቹ ዜማ ፣
መች የሚረሳ ነው የፍቅራችን ሻማ ፡፡
እስቲ ላስታውስሽ ተረሳሽ ወይ ፍቅሬ ፡
ነገ ልንገናኝ ዛሬ ተቀጣጥረን ፣
እስከምንገናኝ እርስ በርስ ተናፍቀን
ና እኔ መጥቻለውሁ፣
በጣም ናፍቀህኛል ላገኝህ እሻለሁ ፤
ትይኝ ነበር ፍቅሬ
ስመሽኝ ፣ አቅፈሽኝ ፣ አውርተሽ ማትጠግቢኝ ፣
ኧረ እንዴት አስችሎሽ ጨክነሽ ረሳሽኝ ፤
እስቲ ላስታውስሽ ተረሳሽ ወይ ፍቅሬ ፡
እኔና አንቺ'ኮ _....
ስንተያይ ውለን ሌቱ የማይበቃን ፣
ስናወራ አድረን ቀኑ የሚያጥርብን ፤
ላፍታ ተራርቀን ናፍቆት 'ሚበርደን ፣
ላፍታ ተለያይተን ናፍቆት የሚቀጣን ፤
እስቲ ላስታውስሽ ተረሳሽ ወይ ፍቅሬ ፡
ላትከጅኝ ላልከዳሽ ፣
ላትርቂኝ ላልርቅሽ ፣
ጨረቃ ፊት ሆነን የማልነውን ተረሳሽ? ፤
እየተጎራረስን ፣ እየተሳሳቅን ፣
እየተጨዋወትን ፣ እየተሯሯጥን ፤
የሳለፍነው ጊዜስ ፣ ያሳለፍነው ደስታ ፣
ኧረ እንዴት ተረሳሽ ንገሪኝ በጌታ ፤
ፍቅሬ ፦
የኔና አንቺስ ፍቅር እንደዚ በወሬ ፤
ከዚህ እስከ ጨረቃ ሸራ ተዘርግቶ ፣
ዓለምን የሚያህል መፅሃፍ ተሰርቶ ፤
ተፅፎ ፣ ተነቦ ፣ ተስሎ መች ያልቃል ፤
በትረካ ቢቀርብ ከልጅ ልጅ ይደርሳል ፡፡
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ | 2 604 |
| 16 | አሁን የራቀውን አቅርቤ ሳስበው
ወገን በየፊናው ፥
የሚሻል ፍለጋ፤ ካምና ከታች አምናው
የሁዋላውን ትቶ ፥ ይሻማል የፊቱን
ዛፍ እንኳን፥ ሲታደስ ይጥላል ቅርፊቱን
ምን ሆኘ ነው እኔ?
ለሚመጣው ጊዜ፥ ጀርባየን ምሰጠው
በጥንቱ ደጃፍ ላይ፤ የምቀላውጠው
ስንት ጊዜ አለፈ? ሰንት ቀን? ስንት ሌት
አይመች ለስሌት
ዘመኑ በርክቶ
በርምጃ የኖርነው፥ ስንዝር ተለክቶ
ያደርግነው ሁሉ፥ ውብ ተረት ሲመስል
መውጊያሽ መናደፍያሽ ፤ ስለቱ ደንዞ
ያተምሽብኝ ቁስል
እንዳልፎ- ሂያጅ ኮከብ ፥ እያደር ደብዝዞ
አሁን የራቀውን አቅርቤ፥ ሳስበው
የደስታ ጸዳል ነው፥ ፊቴን የሚከበው ::
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ በእውቀቱ ስዩም | 2 529 |
| 17 | #መንፈሴን_አመመኝ!!!
ሰምቶ ለሚያሰማ ችግሬን ነግሬ
ስሜ አደባባይ ነው የሚውለው ዛሬ
ይረዳኛል ያልኩት ያመንኩት ቢከዳኝ
አልቅስ አልቅስ አለኝ በድንገት ሆድ ባሰኝ
ለካስ እህ እያለ ችግሬን መስማቱ
ሊረዳኝ አይደለም አቤት ሰው ክፋቱ
ደግፈኝ ያልኩት ሰው ገፍትሮ ቢጥለኝ
ከስጋዬ በላይ መንፈሴን አመመኝ።
ከአረገልኝ በላይ ያደረገኝ ብሶ
ሆዴን እየባሰው ይቀናኛል ለቅሶ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 2 686 |
| 18 | #በበላ_ልበልሀ
በሉ ተባባሉ ጉዳዩ ምድነው ?
በዳይ ተበዳይን ሰምተን እንወቀው
ሚዛናዊ ፍርዱን ውሳኔ እድንሰጠው
ከከሣሽ እንጀምር አቤት ባይ እሱነው።
ከሣሽ-አመሠግናለሁ ስለፈቀዱልኝ
በደሌ ይሄነው ልናገር አዳምጡኝ
እንክርዳዱን ጠምቃ ቀምሳ አጣጥማው
በቅላሏ ሞላችው ተዋዳ ከጠላው
እኔ ላላይባት ሰውራ አስቀምጣው
ወዳጄ እያልኳት አምኛት እንደሰው
መሀላ አፈረሰች በደሌ ይሄውው ነው፡፡
ተከሳሽ - እክርዳድ አይደለም ቅሌን የሞላሁት
ወቅጦ በሰጠኝ ነው ጠንስስሼ የጠመኩት
ከገንቦዬ ቅድሚያ እሱን ነው ያቀመስኩት
ከሳዘሬ ይመስክር ያለው ከጎተራ
ጠይም እንኳ የለው እንክርዳድ ሊያፈራ
ተከሣሽ-- የጠየመን ስንዴ እንክርዳድ ካለው
ከገንቦዬ ጠልቆ ከጠላው ባይቀምሰው
ሸንጎው ፍርዱን ይስጠኝ ጥፋቴ ምድነው?
ዳኛው ከሣሽ ፣ተከሣሽን ሁሉንም ሠማነው
ማሳህ ያተ ሆኖ ስንዴ የዘራኸው
እንክርዳድ አይደለም ጠይሞ ብታየው
ይሄ አያጣላም ከጠላህ አፍቅረው
ይቅር በላት አሁን የህል ክፉ የለው።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ግዛቸው ማሞ | 2 776 |
| 19 | #ያማል
ራሴን ልሰጥክ
ወስኛለሁ ብላ፤
ማታ ቀጠረችኝ
ከለመድናት ቦታ።
ሰአቴን ጠብቄ
ከቦታው ተገኘሁ፤
ቃሏን እያሰብኩኝ
ትእዛዝ እየሰጠሁ፤
ጥቂት እንደቆየሁ
እሷ መጣችና፤
በምግብ በመጠጥ
ትንሽ ጠገብንና፤
ወደክፍሉ አመራን
ወደያዝነው አልጋ፤
በፍቅር ቀለጥን
ለሊቱ እስኪነጋ።
ይሄ ውብ ቃላችን
እራስን የመስጠት፤
ችግር መሃል ገብቶ
ቃልን በቃል ሲያስት፤
በቃ አልፈልግህም
ሂድልኝ አለችኝ፤
ለካስ የዛን ምሽት፤
አካሏን ነው እንጂ መች ልቧን ሰጠችኝ።
የስሜቱን ነገር
እንደውለታ ቆጥራ፤
ችግሩ ሲፈጠር
ቀረች ተሰውራ።
ችግሩ ምንድነው
መባል ስለማይቀር፤ ልናገር
(HIV)፤ positive ነኝ እኔ
በውልደቴ ጀንበር፤
በእኔ ጥንቃቄ፤
ጤነኛ መሆኗን እርግጠኛ ስትሆን፤
እራሷን ልሰጠኝ
ቃሏን እንዳልሰጠች፤
ህመምህ ህመሜ
ብላ እንዳላለች፤
የፍቅርን ትርጉም
እሷ መች አወቀች፤
ለወደዱት መሞት
እሷ ስላልቻለች፤
መልካም ናት አውቃለሁ
እርቃኝ ሄዳለች፤
ሌላ አፍቃሪ እንዲሞት
እድሉን ሰጥታለች፤
ፍቅርን ለሞት ጥላ
ሸሽታ ኮብልላለች፤
ቀድማኝ እንደማትሞት
ግምቷን ሰጥታለች።
አንድ ቀን ሲገባት፤
የማይገኝ ፍቅርን መሞት እንደቀማት፤
ሞት ግን ስለማይቀር
ያማል ፍቅር ማጣት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ | 2 771 |
| 20 | #ያኔ_እንዳደረግነው!!!
እንታረቅ ውዴ በትንሽ ጣታችን
በለመድነው ኩርፊያ በልጅነታችን
ቂም በማይቋጥረው በለጋነት ውበት
ያኔ እንዳደረግነው ጥልቅ የፍቅር ስሜት
ዛሬም እንድገመው ጣልቃ ሳናስገባ
በትንሽ ጣታችን እኛው እንግባባ
ኩርፊያችን የፍቅር
ይቅርታችን ከምር
የልጅነታችን
በትንሽ ጣታችን
ዛሬም እንታረቅ እሽ በይኝ ውዴ
ቂም መያዝሽን ተይ ይቅር መናደዴ
መጣላታችንን ማንም ሰው ሳይሰማ
እንደጥንቱ ዛሬም እኛው እንስማማ
ጣትሽን ሳሚልኝ ጣቴን እስማለሁ
ፈገግ በይልኝ እኔም እስቃለሁ
አድገን እንድገመው ያለሽማግሌ
ስሜትሽ ስሜቴ አካልሽ አካሌ!
የውሸት ተጣልተን የምር እንታረቅ
በንጹህ ፈገግታ ጥርሳችን ይፍለቅለቅ
አምላክም ብሎናል ህፃናት ምሰሉ
መጽደቅን ብትሹ ቂም አታንከባሉ
ልባችን የልጆች እድሚያችን የትልቅ
እንታረቅና እኛው ለኛ እንሳቅ!!
አምጭ ትንሿን ጣት
እኔም ልጎትታት
ፍቅር ማለት ለካስ ያኔ ነበር የእውነት
በከንፈር ተኳርፎ በጣት ለመግባባት
ያኮረፈን ከንፈር ፈልቅቆ ማላቀቅ
ያለሽማግሌ ተግባብቶ መታረቅ!!!
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
✍ ስንታየሁ ሀብታሙ | 2 494 |
