የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
916
Obunachilar
-124 soatlar
+27 kun
-730 kun
Postlar arxiv
ሰኔ 21/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በደነብ ቀበሌ በወዶ ጫንጮ መንደር የሙዝ ልማት በክላስተር ተካላ ተጀመረ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የሙዝ ልማት ክላስተር በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በደነብ ቀበሌ በወዶ ጫንጮ መንደር ተመሰረተ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በተከላ ወቅት ተገኝተው በወረዳው ያሉ እምቅ ሀብቶችን በመጠቀም እንዲሁም ያሉ አቅሞችን ወደ ውጤት በመቀየርና የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሁሉም እርሶ አደር ሰይሰላችና በእንክብካቤ በማልማት አሁን የተተከለውን ችግኝ ፍሬ አፍርቶ ለማየት ሁሉም አካላት በርብርብ ሊሰሩ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
የወረዳው ም/አስተዳደርና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው አርሶአደሩን በክላስተር በማደራጀት ፣ የክህሎት ስልጠና በመስጠት ከመሬት ዝግጅት ጀምሮ እስከ ተከላ ድረስ በባለሙያ ድጋፋዊ ክትትል ከተቋም ጀምሮ ጠንካራ ስራ መሰራቱን ጠቅሠው ቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል።
ክላስተሩ እንዲመሰረትና የተሻሻለ የሙዝ ዝርያ G-ካቪዴሽን የተባለ ዝርያ በማቅረብ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ከ4500 ሺህ በላይ ችግኝ ሙሉ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸው በተቋማቸው ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቶ ከድር መርጋ አቅርበዋል።
የሙዝ ልማት ክላስተር ምስረታና ተከላ ፕሮግራም ላይ
የወረዳው ዋናአስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣
የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ጠይብ አስፍር፣የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የጽ/ቤት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች
ሰኔ 21/2018 ዓ.ም
🎤 የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሴቶች ልማት ህብረት ስትሪንግ ኮሚቴዎች በተጠናከረና በተቀናጀ አግባብ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በወረዳው ያለውን የሰላም እሴት ለማፅናት የፀጥታው መዋቅር እያከናወነ ያለውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የገደባኖ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላለፉት ለሶስት አመታት ያስተማራቸው 64 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ለ3ኛ ዙር በታላቅ ድምቀት አስመረቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በ2018/19 ምርት ዘመን 20 ሺህ 518 ሄክታ በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 "ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸንፋለች! ኑ አገር በጋራ እንገንባ"በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የህዝብ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሴቶች ልማት ህብረት ስትሪንግ ኮሚቴዎች በተጠናከረና በተቀናጀ አግባብ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተባለው የወረዳው ሴ/ህ/ጉ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ4 ኛ ሩብ ዓመት የወረዳው የሴቶች ስትሪንግ ኮሚቴ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዶ በዋለበት ወቅት ነው።
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ ለመድረኩ የተዘጋጀ ዕቅድ አፈጻጸም ሰነድ አቅርበው ጥልቀት ያለው ውይይትና ምክክር ተደርጓል።
ከተሳታፊዎች በኩል ከተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች መካከል በበጀት ዓመቱ ሴቶችን በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርትና በንግድ መስኮች ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ፣ የሴቶች ልማት ህብረቶችን ቁመና ማጠናከር እንደሚገባ ያወሱት ተሳታፊዎች ከትምህርት ነፃ የህግ አገልግሎት ስራ ተቀጣጥሎ ሊሰራበት እንደሚገባ የሚሉትን ጨምሮ የመሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት ኦዲት አገልግሎት ስራ መጠናከር ይኖርበታል ሲሉ ተሳታፊዎች አንስተዋል።
የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዘይነብ ወራቄ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የሴቶች አደረጃጀቶችን በተገቢው ጥቅም ላይ በማዋል ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
አያይዘውም የሴቶች ልማት ህብረቶችን በሚፈለገው መጠን ልክ ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰው ማህበራዊ ዘርፍ ላይ እና የሴቶች ውሳኔ ሰጪነት ሚና በተመለከተ እንዲሁም አጽንኦት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም በመግለጽ ተቋሙ በግብዓትነት የተሰጡ ሃሳብና አስተያየቶን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አድርጎ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ በበኩላቸው ከመድረክ የተሰጡ ግብዓቶች የቀጣይ ዕቅድ አካል9 አድርገው እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
አክለውም የሪፖርት ቅብብሎሽ ጋር በተገናኘ የሚስተዋለው ጉድለት ተወስዶ መታረም እንደሚገባው በማንሳት የስትሪንግ ኮሚቴ ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።
የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ።
ሰኔ 18/2018 ዓ/ም
በወረዳው ያለውን የሰላም እሴት ለማፅናት የፀጥታው መዋቅር እያከናወነ ያለውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ወረዳዊ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለወረዳው አመራርና ለፀጥታ አካላት የወይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።
ለውይይት መነሻ የሚሆን የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በወረዳው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥና የህዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ያተኮረ ሰነድ በዝርዝር አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን እንዳሉት የወረዳውን ዘላቂ ሠላም እና ፀጥታ ማስከበር ቀዳሚው የሴክተሩ ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።
የውይይት መድረኩ በወረዳው ያለውን አስተማማኝ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማፅናትና የህግ የበላይነትን ማስከበርና አጠናክሮ ማስቀጠልን ያለመ መሆኑን ገልፀው ባለፉት ዓመታት በወረዳው ሰላምን ለማስፈን የተሰሩ አበረታች ስራዎችን በቀጣይም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሁሉም አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል፡፡
የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በበኩላቸው ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡
የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከልና ተፈፅመው ሲገኙም እርምጃ ለመውሰድ ጠንካራ የቁጥጥር ስራ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን በተገቢው መወጣት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
በመድረኩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው አስተባባሪ አካላት፣የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች የጸጥታ መዋቅር አመራሮች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 17/2018 ዓ/ም
የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው በዘንድሮ በጀት አመት182 ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን በሁለት ማር መሰብሰቢያ ዙሮች(ወቅቶች) 183.5 ቶን የማር ምርት መሰብሰብ መቻሉን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አክሎ ገልጿል።
በወረዳው ጥራት ያለውና በገበያ ተፈላጊ ማር የሚመረት መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑንም በወረዳው ያለውን ንብ የማነብ እና ማር ውጤቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እሴቶችን ተጨምሮ በማሻሻል በዘርፉ ያለውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በዚህ ዘርፍ በካልም ፕሮጀክት የታቀፉ ማህበር፣ የግል ባለሀብቶችና አርሶ አደሮች የማር ምርቶችን ከራሳቸው ባለፈ ለገብያ በማቅርብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ ይገኛሉ።
የወረዳው በግብርና ፅ/ቤት በካልም P4R ፕሮግራም በታቀፉ ንኡስ ተፋሰሶች ላይ በተደራጁ አባላት ከ50 ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለመዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አቅርቧል።
በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በላቀ ደረጃ ለማሳደግ፣ ዘርፉን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት ብለዋል።
አቶ አ/ረሂም ርዳ
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
በወረዳው የሚታየውን የግብርና ምርታማነት ስራዎችን በማሳደግና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት ውጤታማ አርሶ አደር ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
አቶ ሚፋታ ሁሴን
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ
