uk
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Відкрити в Telegram
913
Підписники
-124 години
+27 днів
-730 днів
Архів дописів
ሰኔ 20/2018 ዓ.ም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሴቶች ልማት ህብረት ስትሪንግ ኮሚቴዎች በተጠናከረና በተቀናጀ አግባብ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተባለው የወረዳው ሴ/ህ/ጉ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ4 ኛ ሩብ ዓመት የወረዳው የሴቶች ስትሪንግ ኮሚቴ የውይይት መድረክ ዛሬ ተካሂዶ በዋለበት ወቅት ነው። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ ለመድረኩ የተዘጋጀ ዕቅድ አፈጻጸም ሰነድ አቅርበው ጥልቀት ያለው ውይይትና ምክክር ተደርጓል። ከተሳታፊዎች በኩል ከተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች መካከል በበጀት ዓመቱ ሴቶችን በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርትና በንግድ መስኮች ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ የተጀመሩ ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ፣ የሴቶች ልማት ህብረቶችን ቁመና ማጠናከር እንደሚገባ ያወሱት ተሳታፊዎች ከትምህርት  ነፃ የህግ አገልግሎት ስራ ተቀጣጥሎ ሊሰራበት እንደሚገባ የሚሉትን ጨምሮ የመሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት ኦዲት አገልግሎት ስራ መጠናከር ይኖርበታል ሲሉ ተሳታፊዎች አንስተዋል። የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ዘይነብ ወራቄ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የሴቶች አደረጃጀቶችን በተገቢው ጥቅም ላይ በማዋል ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል። አያይዘውም የሴቶች ልማት ህብረቶችን በሚፈለገው መጠን ልክ ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰው ማህበራዊ ዘርፍ ላይ እና የሴቶች ውሳኔ ሰጪነት ሚና በተመለከተ እንዲሁም አጽንኦት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም በመግለጽ ተቋሙ በግብዓትነት የተሰጡ ሃሳብና አስተያየቶን የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አድርጎ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል። የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ በበኩላቸው ከመድረክ የተሰጡ ግብዓቶች የቀጣይ ዕቅድ አካል9 አድርገው እንደሚሰሩ አስታውቀዋል። አክለውም የሪፖርት ቅብብሎሽ ጋር በተገናኘ የሚስተዋለው ጉድለት ተወስዶ መታረም እንደሚገባው በማንሳት የስትሪንግ ኮሚቴ ቅንጅታዊ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበት አስገንዝበዋል።

የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ።

ሰኔ 18/2018 ዓ/ም በወረዳው ያለውን የሰላም እሴት ለማፅናት የፀጥታው መዋቅር እያከናወነ ያለውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ወረዳዊ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታን አስመልክቶ ለወረዳው አመራርና ለፀጥታ አካላት የወይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው። ለውይይት መነሻ የሚሆን የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በወረዳው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥና የህዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ያተኮረ ሰነድ በዝርዝር አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን እንዳሉት የወረዳውን ዘላቂ ሠላም እና ፀጥታ ማስከበር ቀዳሚው የሴክተሩ ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል። የውይይት መድረኩ በወረዳው ያለውን አስተማማኝ ሰላም ወደ ዘላቂ ሰላም ለማፅናትና የህግ የበላይነትን ማስከበርና አጠናክሮ ማስቀጠልን ያለመ መሆኑን ገልፀው ባለፉት ዓመታት በወረዳው ሰላምን ለማስፈን የተሰሩ አበረታች ስራዎችን በቀጣይም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሁሉም አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል፡፡ የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በበኩላቸው ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከልና ተፈፅመው ሲገኙም እርምጃ ለመውሰድ ጠንካራ የቁጥጥር ስራ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን በተገቢው መወጣት እንዳለባቸው አስታውቀዋል። በመድረኩ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው አስተባባሪ አካላት፣የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች የጸጥታ መዋቅር አመራሮች እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 17/2018 ዓ/ም የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በወረዳው በዘንድሮ በጀት አመት182 ቶን የማር ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁን በሁለት ማር መሰብሰቢያ ዙሮች(ወቅቶች) 183.5 ቶን የማር ምርት መሰብሰብ መቻሉን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አክሎ ገልጿል። በወረዳው ጥራት ያለውና በገበያ ተፈላጊ ማር የሚመረት መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑንም በወረዳው ያለውን  ንብ የማነብ እና ማር ውጤቶችን ሳይንሳዊ  በሆነ መንገድ  እሴቶችን ተጨምሮ በማሻሻል በዘርፉ ያለውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በዚህ ዘርፍ በካልም ፕሮጀክት የታቀፉ ማህበር፣ የግል ባለሀብቶችና አርሶ አደሮች የማር ምርቶችን ከራሳቸው ባለፈ ለገብያ በማቅርብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ ይገኛሉ። የወረዳው በግብርና ፅ/ቤት በካልም P4R ፕሮግራም በታቀፉ ንኡስ ተፋሰሶች ላይ በተደራጁ አባላት ከ50 ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለመዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አቅርቧል።

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በላቀ ደረጃ ለማሳደግ፣ ዘርፉን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት ብለዋል። አቶ አ/ረሂም ርዳ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

በወረዳው የሚታየውን የግብርና ምርታማነት ስራዎችን በማሳደግና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት ውጤታማ አርሶ አደር ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል  ብለዋል። አቶ ሚፋታ ሁሴን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ

"በ7ኛው ዙር አገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ በማጠናቀቅ የተገኘውን ድል በማስቀጠል በቀጣይ ጊዜ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በሚደረገው ርብርብ መላው አመራርና አባላት ከልማት ወዳዱ ህዝብ ጎን በመሰለፍ የበኩሉን ድጋፍ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል" አቶ ሚፋታ ሁሴን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ

ሰኔ 15/2018 ዓ/ም በ2018/19 ምርት ዘመን 20 ሺህ 518 ሄክታ በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት የ2018/19 ዓ.ም የመኸር የተቀናጀ የግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ ''የተቀናጀ ግብርና ለቤተሰብ ብልጽግና "በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ መድረክ ባካሄደበት ወቅት ነው ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን የመክፈቻ ንግግር የግብርና ልማት የወረዳችንና የሃገራችን ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በመሆኑ ይህንን አማራጭ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ዘርፉን ለማዘመንና የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መንግስት ልዩ ትኩረት ሠጥቶት እየሰራ እንደሚገኝና ተጨባጭ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ገልጸዋል። የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሁሴን ለመድረኩ የተዘጋጁ የወይይት ሠነድ እቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጓበታል። የግብርናው ዘርፍ ለማዘመንና ውጤታማ ለማድረግ የተሻሻለ ዘር ማቅረብ ፣በዘርፉ የሰለጠነ የባለሙያ ድጋፍ ክትትል ውስንነት መኖር፣ መሬትን አሟጦ ለእርሻ ስራ አለማዋል፣ የቡና ችግኝ ተደራሽነት አናሳ መሆን በወቅቱ መቅረብ አለመቻሉን፣አርሶ አደሩ ላመረተው ምርት የገበያ ትስስር መፈጠር እንደሚገባ፤አሲዳማ መሬቶች በኖራ በመታከማቸው ምርት መስጠት መቻላቸው ፤በማሳ ውስጥ ያሉ ዛፎች ማስነሳት እንደሚገባ በውይይት መድረኩ ከተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች መካከል በዋናነት ተጠቃሾች ናቸው። ለተነሱ ሀሳብ አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን ወረዳችን እውቅና እያገኘባቸው እየመጣ ያለው የቡናና የማር ምርት ይበልጥ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አርሶ አደሩ በትኩረት በመስራት በቀጥታ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባ አብራርተዋል። ዛፍን በማንሳትና የማይታረሱ የወል ፣ የማህበር፣ የተቋማትና የግል መሬቶች በማረስ የማይታረስ መሬት ዜሮ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባ ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እየተከናወ ያለው የመኸር ስራ በጥራት በመስራት ምርታማነት ለማሳደግ FTC፣የማህበራት እርሻዎች የግልና የተቋማት ማሳ ላይ ትኩረት በማድረግና የተቋሞች አቅም በማጠናከር  ራሳቸው መቻል እንዳለባቸው ገልጸዋል። አቶ አ/ረሂም አክውም በወረዳው የሚታየውን የግብርና ምርታማነት ስራዎችን በማሳደግና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋት ውጤታማ አርሶ አደር ለማፍራት መስራት ያስፈልጋል በማለት የታቀዱ ተግባራት  እንዲሳኩ ሁሉንም አደረጃጀቶች መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል።፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው በኩታ ገጠም ዘር መዝራት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ ጠቅሰው ለክላስተር ማሳ ልዩ ትኩረት እንደሚደረግና ከምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ በቂ ዝግጅት እንደተደረገ ማሳ ውስጥ ያሉ ዛፎችን ለማስነሳት በመመሪያ መሰረት ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በመድረኩም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣ የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው የግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የወረዳው አመራሮች ፣ የቀበሌ ስራ አስኪያጆችና አስተዳደሮች ፣ጽ/ቤቱ የማኔጅመንት አካላት እንዲሁም የቀበሌ አመራሮች የግብርና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።