Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 084
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+227 kunlar
+1330 kunlar
Postlar arxiv
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል የህንጻ ግንባታ ለሚሣተፋ የህንጻ ግንባታ ተቋራጮች የቅድመ ጨረታ የመስክ ጉብኝት እና ውይይት ከተቋራጮች እና ከተወካዮች ጋር አካሄደ::
በውይይቱ ላይ በመገኘት ስለ ግንባታውና ስለ SIFA ፕሮጀክት በኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን እንዲሁም የEASTRIP ፕሮጀክት ኮንትራት አድምኒስትሬተር በሆኑት አቶ ሀምዲ ኢብራሂም በኩል በቂ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን በመቀጠልም በመስክ ምልከታው እና በገለጻው ላይ ከተቋራጮች ጋር በቂ ውይይት ተደርጓል::
በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ በኮሌጁ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል ግንባታ በዋናነት 3 ዋና ዋና ስራዎች የሚሠሩ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ የህንጻ ግንባታ የእቃ ግዢ የካሪኩለም እና TTLM ዝግጅት የሚጠቀሱ ናቸው::
የሚያዝያ 08/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from N/a
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ ልዑክ ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እና የስራ ጉብኝት አካሄደ::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ የተጀመሩ የሪፎርምና የመደበኛ ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ የሚያስችለውን ጉብኝ ለማድረግ እንደተገኘም ነው የተገለፀው::
በነበረው መርሃ-ግብርም የኮሌጁ ማኔጅመንት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በኩል ለልዑካን ቡድኑ ባለፉት ስድስት ወራት በኮሌጁ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትን በተመለከት ኮሌጁ ያለውን አፈፃፀም ትኩረት በማድረግ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም ከልዑካን ቡድኑ ጋር ውይይት ተደርጏል።
በተጨማሪም ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ ስልጠና የሚሰጥባቸውን ዲፖርትመንቶችና ወርክሾፖች ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በዚህም የተለያዩ የለውጥ ስራዎችንና ፕሮጀክቶችን መመክከት ችለዋል::
የዚህ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ዓላማም በትግበራ ወቅት የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ልማት እና የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት መሆኑም ተመላቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 08/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ ልዑክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እና የስራ ጉብኝት በዛሬው እለት አከናወነ::
በኮሌጁ የተጀመሩ የሪፎርምና የፕሮጀክት እና የመደበኛ ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ ባለመውና በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራው ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እና የስራ ጉብኝት በዛሬው እለት አከናወነ::
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን በውይይቱ ወቅት ሲገልጹ በባለፉት ስድስት ወራት በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪዎችን የተለዋጭ ምርት ማምረት ላይ ኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ትኩረት በማድረግ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ።
የመስክ ምልከታው ዓላማ በዋናነት መልካም አፈፃፀሞችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ልማት እና የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት መሆኑን በሥራና ክህሎት ሚኔስቴር ሚንስትር ዴኤታ የሆኑት ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ አስታውቀዋል::
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሚያዝያ 08/2016 ድሬዳዋ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራው ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ድጋፉዊ የስራ ጉብኝት ለማካሄድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ከአስተዳደሩ የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ ባለመውና በከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራው ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ድጋፋዊ ጉብኝት ለማካሄድ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በዛሬው እለት በቢ ካፒታል ሆቴል ውይይት ተካሂዶል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውም በውይይቱ ሲገልጹ በባለፉት ስድስት ወራት በአስተዳደሩ በሥራ እና ክህሎት ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የአሰሪና ሰራተኛ፣የስራ እድል ፈጠራ ስራዎችን ተመልክቶ ድጋፍ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ የስራ ጉብኝት መሆኑን ተናግረዋል።
የመስክ ምልከታው ዓላማ በዋናነት መልካም አፈፃፀሞችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የኢንዱስትሪ ሰላማዊ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት መሆኑን በሥራና ክህሎት ሚኔስቴር ሚንስትር ዴኤታ የሆኑት ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ አስታውቀዋል፡፡
በዚህም መሠረት በአስተዳደሩ የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች፣ እየተሰጡ ያሉ ሥልጠናዎችን እና የኢንዱስትሪ ሰላም ጋር ተያይዞ የተከናወኑ ሥራዎችን ጉብኝት በቀጣይ ጊዜያት ያካሂዳል።
ድጋፋዊ ጉብኝቱም ለ10 ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የመንግስት ሰራተኞች የብልፅግና ፓርቲ መሠረታዊ ድርጅት የ2016 ዓ.ም የሶስተኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።
በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንዳሉት መሠረታዊ ድርጅቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ የፖለቲካ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው በተለይ ደግሞ ከመንግስት ሥራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካው ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል።
የመሠረታዊ ፓርቲው ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በአስተዳደሩ ትኩረት የተሰጠውንና የቢሮው ዋነኛና ተቀዳሚ ተልዕኮ የሆነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አባላት ውጤት ሊያስገኝ የሚችልን ስራ በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በግንባር ቀደምነት ልንሰለፍ ይገባል ብለዋል።
በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የመሠረታዊ ድርጅቱ የስድስት ወር የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የቀጣይ 3 ወር እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን በመጨረሻም የእጩነት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ አባላትን ወደ ሙሉ አባልነት በማሸጋገር እና የቀጣይ 3 ወራት መሠረታዊ ድርጅቱ እና የህዋስ አደረጃጀትን የሚመሩ የመሠረታዊ ድርጅትና ህዋስ አመራር ምርጫን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በማከናወን ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ለሁለተኛ ዙር እየተተገበረ የሚገኘው ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት አስመልክቶ ለኢንዱስትሪ ባለቤቶች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ።
በዚህም መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐርቢ ቡህ በመክፈቻ ንግግራቸው በአስተዳደሩ አልፎም በሀገር ደረጃ ፈተና የሆነውን የሥራ አጥነትን ችግር ለመቅረፍ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸው ሥራ ፈላጊ የሆኑ በተለይም የወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሰል ፕሮጀክቶች ፋይዳቸው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንግስት እና በአለም ባንክ የጋራ ትብብር ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ የተሰኘ ፕሮጀክት ወደ ስራ ለማስገባትና ውጤታማ ለማድረግ የባለሃብቶችና የኢንደስትሪ ባለቤቶች ሚና ቀላል አይደለም ብለዋል።
በመድረኩ ተሳታፊ የሆኑ የኢንደስትሪ ባለቤቶች ስለ ፕሮጀክቱ በቂ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን በትግበራው ሂደት ሊፈጠሩ በሚችሉና ግልጽነት በሚያሻቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳቦችን ያነሱ ሲሆን ለኢንደስትሪዎቻቸው እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ ከቢሮው ጋር በጋራ ለመስራት ቃል ገብተዋል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በማጠቃለያው ይህ ፕሮጀክት ሥራ ፈላጊ ወጣቶችንና ኢንደስትሪዎችን በተመሳሳይ ጊዜ በብዙ ሊጠቅም የሚችል መሆኑን ጠቅሰው ከተጠቃሚነታቸው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት እድል የሚፈጥር መሆኑንና ከመጀመሪያው ዙር በተወሰደው ተሞክሮ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የቀበሌ አንድ ማዕከላት የተመዘገቡ ወጣት የሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች ስልጠና ተጀመረ።
በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስራ እድል ፈጠራ እና የቀበሌ አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በዚህ ዙር ከንድ የሚደርሱ ሰልጣኞች ወደ ስልጠና የገቡ መሆኑን ጠቅሰው ሰልጣኞች ይህን ዕድል በሚገባ ተጠቅመው እራሳቸውንና አገራቸውን የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ አሳስበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 5/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሀዘን መግለጫ
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ባልደረባ የሆኑት አቶ ፈቲህ መሀመድ ዘካሪያ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሚያዚያ 03ቀን /2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ቢሮው ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጅ ዘመዶቹና ለስራ ባልደረቦቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡
የሀዘን መግለጫ
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ባልደረባ የሆኑት አቶ ፈቲህ መሀመድ ዘካሪያ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሚያዚያ 03ቀን /2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ቢሮው ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጅ ዘመዶቹና ለስራ ባልደረቦቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡
ኢድ ሙባረክ!!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና የአብሮነት ይሆንልን ዘንድ ከልብ እመኛለሁ።
መልካም በዓል
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛው የዒድ-አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የአብሮነት እንዲሁም የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ!!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት ስልጠና ላይ ተሳትፈው ስልጠናውን ላጠናቀቁ ከ80 በላይ ወጣቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚገኝ ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ ጋር የስራ ትስስር ፈጸመ፡፡
በወጣቶቹ የስራ ትስስር ጉዳያ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ዋና አላማ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በእውቀት፣በክህሎትና በአመለካከት የተቀረጹ ትውልዶችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን ወጣቱን በተለያዩ ስልጠናዎች በሚያገኙት እውቀት መሰረት በተለያዩ ፋብሪካዎች ስራ እንዲያገኙና ከራስ አልፎ ለሃገር መጥቀም የሚችሉ ወጣቶችን ማፍራት ነው፡፡
በዚህ መሰረት ኮሌጃችን በሳለፍነው አመት አቅዶበት ሲሰራበት የነበረውና በእቅዱ መሰረት በርከት ያሉ ሰልጣኞችን የስራ እድል ሲፈጥር ቆይቷል፡፡ዛሬም ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ጋር በተስማማነው መሰረት በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት ስልጠና ላይ ተሳትፈው ስልጠናውን ላጠናቀቁ ከ80 በላይ ወጣቶች ወደ ስራ አስገብተናል ብለዋል፡፡ም/ዲኑ በንግግራቸው በያዝነው አመት በርከት ያሉ ሰልጣኞች በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የስራ ትስስር የምንፈጽም መሆናችንን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በተያያዘ ዘገባ ዛሬ የስራ ትስስር የተፈጸመበት ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ በኮሌጁ ማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል አማካኝነት winding Bering Holder ፣ Heat Exiting Duct እንዲሁም Chiller Machine Assembly and installation የሚባሉ የማሽነሪ ስፔር ፓርት አምርቶ እንዲሁም ገጥሞ ፋብሪካውን በመለዋወጫ እጥረት ምክንያት የሚፈጠርበትን ክፍትት መሙላቱ ይታወሳል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 01/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
