uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 088
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+227 kunlar
+1330 kunlar
Postlar arxiv
እንኳን ለ128ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሰን!
እንኳን ለ128ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሰን!

ዓድዋ-የጥቁር ሕዝቦች ድል!

ለዩኒቨርስቲ እና ኮሌጅ ምሩቃን ስራ ፈላጊዎች የማይንድ ሴት ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ሥራ ፈላጊዎች ተቀጥሮ መስራት ላይ ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ በሚያነሳሳ መልኩ ቀርቧል። በዚህም ተሳታፊ የሆኑ የዩኒቨርስቲ እና የኮሌጅ ምሩቃን ሥራ ፈላጊዎች ከዚህ በፊት ተቀጥሮ ለመስራት ብቻ ይጠብቁ የነበሩ ከስልጠናው ባገኙት ግንዛቤ በግልም ሆነ ተደራጅቶ ለመስራት መነሳሳት እንደተፈጠረባቸው ገልጸዋል። ቢሮው በአስተዳደሩ ትኩረት  የተሰጠውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ የተለያዩ ስራዎችን በተለይም ከኢንዱስትሪዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠርና ተመራቂዎች ተደራጅተው ወደ ሰራ እንዲሰማሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ገልጸዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 21/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ኢንተርፕራይዞች ፍትሃዊ መንግስታዊ ድጋፎች ተጠቃሚ በማድረግ የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት መድረክ ከአንቀሳቃሾችና ከባለድርሻ አካላት ጋር አደረገ። በአስተዳደሩ የሚገኙ ሁለቱ መንግስታዊ ኮሌጆች በተለይም በ4ቱ የድጋፍ ማዕቀፎች የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችንና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪግ ኢንደስትሪዎችን የምርትና ምራታማነት በማሻሻልና  ብቁ የሆነ የሰዉ ሐይል በማፍራትና የሥራ እድል እንዲፈጥሩ በማስቻል ድጋፍ እየሰጡ እንደሚገኙ ይታወቃል፤ በቢሮው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት  ይህን መድረክ ሲያዘጋጀ ኢንተርፕራይዞችና ለባለድርሻ አካላት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጽንሰ ሃሳብ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በፊት በነበሩ ድጋፍ አሰጣጥና ምዘና ጋር በተያያዘም ደካማ ጎኖችን በመንቀስ ለቀጣይ የመፍትሔ አማራጮች ተጠቁመዋል፤ በመድረኩም ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በቀጣይም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፉን በተቀላጠፈ ሁኔታና በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያችል ሰፋ ያለ ውይይትም የተደረገ ሲሆን የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተመላክቷል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት(EDI) የሚተገበረው የሴቶች ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ፕሮጀክት(WEP) ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር  ለ45 ቀናት የሚቆይ በቆዳና ቆዳ ውጤቶች ላይ ያተኮረ ስልጠና  ለ42 ሴቶች በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮች በዚህ ስልጠና ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሰልጣኞችን በአካል በመገኘት ያበረታቱ ሲሆን ኮሌጁ ስልጠናውን ለሰልጣኞች ምቹ በሆነ አግባብ እየሰጠ በመሆኑም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በተያያዘ ኢንስቲትዩቱ በሚተገበረው የሴቶች ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ፕሮጀክት(WEP) ከ2006 ጀምሮ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የስራ ዘርፍ ለተሰማሩ ሴት ኢንተርፕርነሮች የሥልጠና፣ የብድርና የንግድ ልማት አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

• የዓድዋ ጀግኖችን አኩሪ ተጋድሎ ለትውልድ እናሻግራለን!
+1
• የዓድዋ ጀግኖችን አኩሪ ተጋድሎ ለትውልድ እናሻግራለን!

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የግማሽ አመት ዕቅድ አፈፃፀም መገማገሚያ መድረክ ተጠናቀቀ። የተካሄደው የመገማገሚያ መድረክ በዛሬው ዕለት ቀጥሎ ሲጠቃለል የወረዳ አንድ ማዕከላት የስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ተሳታፊዎች ጥንካሬና ድክመት ባሏቸው ጉዳዮች ላይ  አስተያየትና ትችት የሰጡበት ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት በተካሄደው የማህበረሰብአቀፍ ውይይት ላይ የተገኘ ልምድና ተሞክሮም ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት ዋናዋና በዕቅድ አፈጻጸም የተመላከቱ ውጤቶች በጥቂቱ •  2748 መደበኛ ስልጠና አጠናቃቂዎችን የሙያ ብቃት በምዘና ለማረጋገጥ የታቀደ ሲሆን 1882 መመዘን ተችልዋል፡፡ ከተመዘኑት ውስጥ  1259 ብቁ ሆነዋል፡፡ •  በበጀት ዓመት ስድስት ወራት 3,265 አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ ለማድረግ ታስቦ ፣ አፈጻጸም 3,665 (ከ100% በላይ) ወንድ 1,619 ሴት 2,046 አዲስ ሰልጣኝ ቅበላ ተፈጽሟል፡፡ •  በአጠቃላይ በቋሚ እና ጊዚያዊ 9,004 የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ ወንድ 4,957 ሴት 3,664 ድምር 8,621 የስራ እድሎችን መፍጠር ተችሏል፡፡ •  በአጠቃላይ  265  ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ሲሆን የአባላት ብዛት ወንድ 1,403 ሴት 358 በድምሩ 761 ናቸው፡፡ •  በሙያ ደህንነት ፣ ጤንነትና የሥራ አካባቢ አጠባበቅ ዙሪያ በወጡ በፖሊሲዎች ፣ መመሪያዎች ዙሪያ  ለ250 ፣ለባለድርሻ አካላት እና ለአሠሪና ሠራተኞች ስልጠና ለመስጠት በእቅድ ተይዞ ለ256 ስልጠና መስጠት ተችልዋል፤ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴ/ሙ/ት/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደተናገሩት የቅንጅት እና የመረጃ ልውውጥ ስራዎች ላይ በተለይ ከወረዳ አንድ ማዕከላት ጋር ሁሉም ዘርፎች በቅርበት ሊሰራበት የሚገባ ሲሆን ለዚህም የቢሮውን የለውጥ ስራዎች አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያግዙ ስራዎችን የውስጥ አቅምን በማሰባሰብ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል። በመጨረሻም በኮሌጆች መካከል ያለውን የጋራ የመተባበርና ተጋግዞ መስራት ላይ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውንና የህንንም የኮሌጆች አቅም በተለይ ለረጅም ጊዜ በመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ የቆየውን የገጠሩን ማህበረሰብ ተደራሽነት በሞባይል ቴ/ሙ/ት/ስ ምላሽ የሚሰጡ ስራዎች በቀጣይ ስድስት ወራት እንደሚሰሩ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የማጠቃለያ አስተያየትና ቀጣይ አቅጣጫ ከሰጡ በኋላ የቢሮው ሰራተኛ ሆነው የጡረታ መውጫ ጊዜያቸው ደርሶ ለተሰናበቱ አቶ ተስፋዬ አበራ እና ወ/ሮ ዘለቃ ዘውዴ የክብር ሽኝት በማድረግ ተጠናቋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 16/2016 ዓ.ም ሐረር

photo content
+7

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የስድስት ወራት አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ነው ። ቢሮው የ2016 በጀት አመት የ6 ወር የቢሮውን፣ የኮሌጆች እና የወረዳ አንድ ማዕከላት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ በዛሬው ዕለት መካሄድ የጀመረ ሲሆን በነገውም ቀጥሎ የ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የሚደረግበት ይሆናል። የሪፖርት ግምገማ መድረኩን የቢሮው ኃላፊና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታችው እና ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የመሩት ሲሆን በመድረኩም የቢሮውን እና የኮሌጆች በስድስት ወራቶች ውስጥ የሰሩአቸው  ስራዎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። የግምገማ መድረኩ የአስተዳደሩ ከፍተኛና መካከለኛ  አመራሮች፣ የኮሌጅ ዲኖች እንዲሁም የወረዳ አንድ ማዕከላት አመራሮች፣  እንዲሁም የቢሮው አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በነገው ዕለትም ቀጥሎ ሲካሄድ የወረዳ አንድ ማዕከላት ሪፖርት ቀርቦ ውይይትና የስራ አቅጣጫ ከቢሮው ኃላፊዎች የሚሰጥ ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 15/2016 ዓ.ም ሐረር

በህብረተሰብ ውስጥ ያለውን ሀገር በቀል ዕውቀትና ክህሎት ለመለየት፤ ለመጠቀምና ለማስተላለፍ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ተዘጋጀ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ጠቃሚ ሀገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኝ ተማሪዎችና በኮሌጅ ለሚደገፉ ኢንተርፕራይዞች ተሰጥቷል። እደሚታወቀው በሀገራችን የሚገኙ የሀገር በቀል እውቀትና ክህሎቶች በየዘርፉ ማለትም በግብርና ሥራ፣ በህክምና፣ በዕደ ጥበብ፣ ኮንስትራክሽን፣ ፍልስፍና ፣ የጎጆ ኢንዱስትሪ፣ በትምህርት ስርዓት ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና ሌሎች ዘርፎች በመለየት፤ በማደራጀትና የሙያ ደረጃ በመስጠት በቴከኒክና ሙያ ኮሌጆችና በሌሎች ስልጠና ተቋማት ውስጥ ገብተው እንዲደገፉ፤ተሻሽለው ወደ ገበያ እንዲገቡ፣ የተሻለ ጥቅም እንዱሰጡ አልፎም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል አስፈላጊ ነው ፡፡ የአቅም ግንባታ ስልጠናው እንደ ሀገር ያለንን የሀገር በቀል እውቀትና ክህሎት ወጥ በሆነ አሰራር ለመሰብሰብ፣ ለማደራጀት፣ ለመተንተን እና ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማቆራኘት፣ በማጣጣም እና የአሰራር ሥርዓት በመፍጠር ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚያስችል ስራዎችን በቀጣይ ለመስራት አስቻይ እንደሚሆን የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ  የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በSustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project ላይ
+4
ለሁለት ተከታታይ ቀናት በድሬዳዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   በSustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project ላይ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ:: ለ ኮሌጁ ማኔጅመንት ፣ ዲፖርትመንት ተጠሪዎች እና ኬዝ ቲመሮች በ Sustainable Employment through Entrepreneurship & Enterprise Development (Seed) Project ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ   ስልጠና የተሠጠ ሲሆን  እንዲሁም  በኮሌጅ ውስጥ ያለን የሥራ ባህልን ለማሣደግና ለውጥ ለማምጣትም ያለመ ነበር። የስልጠናዉ ተሳታፊዎችም በሥልጠናው ማብቂያ ወቅት የፕሮጀክቱ  ትግበራ እንዲሳካ የሚጠበቅባቸዉን ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸዉን አረጋግጠዋል። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 14/2016 ዓ•ም ድሬዳዋ

የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ከሁሉም ዳይሬክቶሬቶች ለተወጣጡ የቢሮው ሰራተኞች  "Public Enterpreneurship Ecosystem Building Workshop(PEEB)" በሚል ርዕስ Mind Set ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የቢሮው ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት ይህን ስልጠና ከሚወስዱ ሰልጣኞች ብዙ እንደሚጠበቅና ስልጠናውን በተግባር በመቀየር ፈጠራንና ፍጥነትን አክለው በቀጣይ በስራቸው የሚገኙ ሰራተኞችንና ሌሎችንም የማሰልጠን ተግባር ላይ እንዲሳተፉ አፅኖት ሰተው ተናግረዋል። በስልጠናው ላይ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች አቶ ታደለ አሰፋ እና አቶ ተሾመ ሸዋዬ ላለፉት ቀናት በአሰልጣኝነት ሰልጣኞችን ያሰለጠኑ ሲሆን የነበረው ስልጠና በዛሬው እለት ፍፃሜውን ማግኘቱን ተከትሎ ስልጠናውን ወስደው ላጠናቀቁ ተሳታፊዎች የእውቅና ሰርተፊኬት የሚሰጣቸው ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የሁለተኛ ዙር ኮቦ(መመዝገቢያ ሶፍትዌር) ላይ የድርጅቶች አመዘጋገብ እና ቀጣይ አቅጣጫ ዙሪያ ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎች እና አስተባባሪዎች ጋር ውይይት ተደረገ። በዚህም ቀጣይ ወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ የሚያደርጉባቸውን ድርጅቶች በመመልመል ዝግጁ የማድረግ ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 13/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ