uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 071
Obunachilar
+224 soatlar
+37 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ለአጠቃላይ ሠራተኛው የ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ስድስት ወር የተከለሰ ዕቅድ በአንድ ዕቅድ በአንድ ሪፖርት መሠረት በመከለስ ወደ ተግባር ማስገቢያ የስልጠና መድረክ ተካሄደ። በቢሮው ከዚህ በፊት የነበረው የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት በብዙ መልኩ ውስንነቶች የነበሩትና ሁሉም የተቋሙ ፈፃሚ አካላት የሚሰሯቸውን የዕለት ተዕለት ስራዎች ሙሉ በሚባል ደረጃ ያካተተ አለመሆኑና ይህም ስትራቴጂክ ግቦችና ዝርዝር ተግባራትን ለፈፃሚው ለማውረድ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የነበሩ መሆኑ በእነዚህ ችግሮች መነሻነት የቢሮውን እቅድ በአግባቡ በመከለስ ፈፃሚው እንዲያውቀውና ግብዓቶችን እንዲያክልበት ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና ተሰጥቷል። በዋናነት የዛሬው መድረክ የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ከዚህ በፊት የቢሮው አካላት ዕቅዶች ሲታቀዱ የነበረበት መንገድ እና ከአስቀመጡት ግብ አንጻር የሚመዘኑበት እንዲሁም ውጤትን ለመለካት የማያስችል አካሄድን በመሰረታዊነት ሊያሻሽል የሚችል ወጥነት ያለው የአንድ ዕቅድ እና የአንድ ሪፖርት የአሰራር ስርዓት በቀጣይ ስድስት ወራት በመከለስ መዘርጋት የሚያስችል መሆኑን በቢሮው የፕላን እና ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ይታገስ ካሳሁን ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

🛑ከህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች ራስዎን ይጠብቁ!🛑 ⚠️ 🇨🇦ካናዳና 🇪🇺አውሮፓን ጨምሮ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት እንልካለን የሚሉ ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች በተለያዩ የማህበራዊ ት
🛑ከህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች ራስዎን ይጠብቁ!🛑 ⚠️ 🇨🇦ካናዳና 🇪🇺አውሮፓን ጨምሮ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት እንልካለን የሚሉ ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡ ይህን አይነቱ ማስታወቂያ፡- ➡️ ላልተፈለገ ወጪና እንግልት ይዳርጎታል፣ ➡️ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለት ለከፋ አደጋም ያጋልጥዎታል፣ 🌍 ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረመችባቸውና ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሚደረግባቸው ሀገራት የሚከተሉት ብቻ ናቸው 👇 1️⃣ ሳውዲ አረቢያ 🇸🇦 2️⃣ የተባበሩ አረብ ኤሜሬት🇦🇪 3️⃣ ዮርዳኖስ 🇯🇴 4️⃣ ሊባኖስ (በጊዜያዊነት ስምሪት የማይደረግበት)🇱🇧 5️⃣ ኳታር 🇶🇦 🚨 ማሳሰቢያ ❌ከላይ ከተጠቀሱት ውጪ ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሚሰጥባቸው መዳረሻ ሀገር የሉም፣ ✅የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሀገራት በተጨማሪ ከተለያዩ ካምፓኒዎች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፣ ✅በዚህም ከላይ ከተጠቀሱት ሀገራት ውጪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ #ብቻ ስምሪት ሊሰጥ ይችላል፣ ❌ለዚህ አይነት ስምሪት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ለየትኛውም ሌላ አካል #ፍቃድም ሆነ #ውክልና አልሰጠም፣ ✍️ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን👇 ✅ወቅታዊና በቂ መረጃ ይኑርዎ! ✅አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥሞ በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የህግ አስከባሪ አካላትና በየደረጃው ለሚገኝ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መዋቅር ያሳውቁ! ✅በዘርፉ ላልዎት ማንኛውም ጥያቄና አስተያየት ☎️9138 ነፃ የስልክ መስመርን ይጠቀሙ! ✅በመንግስት ተቋማት በሚሰጠው ስልጠናና የብቃት ምዘና ምንም አይነት ክፍያ አይከፈልም፣ 📢 ይህን መልዕክት ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ♻️ ✅ይህንን መረጃ በማጋራት ሌሎችም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይጋለጡ ያድርጉ❗️

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዋናነት ያሰለጠኗቸውን ሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ እንዲወስዱ ማድረግ ላይ ያተኮረ ሲሆን በተጨማሪም  በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠንና በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል በማስመዘን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትና ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡ በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትና ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አከካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ከመንግስትእና የግል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተወጣጡ አሰልጣኝ መምህራን ሲዘጋጅ የነበረ  የተቋም ውስጥ ምዘና የንድፈ_ሀሳብ_ፈተና( Knoweldege Assessment )፣ የተግባር_ፈተና ( Practical Assessment )፣ የምዘና_ፓኬጅ፣ የተመዛኝ_ፓኬጅ ( Candidate Package )፣ assser package እና ለምዘናው_የሚያስፈልገው_ግብዓት ( Material for assessment package ኤሌክትሪክ፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፋክቸሪንግ ማሽንግና ሜካኒክስ፣ ቢዝነስ አካውንቲግና የሰው ሃብት አስተዳደር፣ በፋሽን ዲዛይን፣ ሚድዋይፈሪ፣ ነርሲንግ፣ ኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን፣ በእንጨት ስራ ቴክኖሎጂ፣ በኮንስትራክሽን እና ካደስተራል ሰርቬይንግ፣ በምግብና መስተንግዶ በጠቅላላ 22 ሙያዎች ተዘጋጅተው በስራ ላይ እንዲውሉ ተደረገ፡፡ ይህም የስልጠናውን ጥራትና የበቃ ባለሞያ ለማፍራት የሚደረገውን ጥራት  ሚያሻሽል ሲሆን ለቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች  የሚሰጡ የስልጠና ፕሮግራሞች በሚፈለገው ደረጃ ለሰልጣኙ አስፈላጊውን እውቀት፣ ችሎታ እና አመለካከት የሚያዳብር ይሆናል፤ ፕሮግራሙን በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች በስራው አለም ውስጥ በተመረቁበት ሙያ በሚጠበቅባቸው ብቃቶች በመሰረታዊነት ለመስራት ብቁ ያደርጋቸዋል፤ በዚህም ይህ የተቋም ውስጥ ምዘና መሳሪያዎች ዝግጅት የሥልጠና ፕሮግራም ዋና ዓላማ ሆነውን ሰልጣኙን በአመለካከት፣ በእውቀትና ክህሎት ማስታጠቅ እንደሆነ በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት  ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

🌎ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት!✈️ በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ የመሆን ፍላጎት አልዎት? እንግዲያውስ ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ብቻ ምርጫዎ ያድርጉ! 📌 አገልግሎቱን ለማግኘት መጀመሪያ ማድረግ ያለብዎ ምንድን ነው?👇 ✅ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (https://lmis.gov.et/) መመዝገብ፣ 🚨 ሕጋዊ አማራጮችን ብቻ ይጠቀሙ! ከዚህ ውጪ ያሉ አማራጮች👇 ✅  ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲሁም ለከፍተኛ አደጋ ያጋልጥዎታል፣ ✅  ከኢትዮጵያም ሆነ ከመድረሻ ሀገራት የመንግስት ሕጋዊ ጥበቃና ከለላ አያገኙም፤ ከተያዙም ወንጀል ነው፣ 💡ህጋዊ መንገዶችን ለምን?👇 ✅ በሄዱበት ሁሉ የሠራተኞች መብት ጥበቃ  ያገኛሉ፣ ✅  በመዳሻ ሀገራት የህግ ጥበቃና ከለላ ያገኛሉ፣ ✅  ሥራ መቀየርም ሆነ ወደ ሀገር ቤት መመለስ ቢፈልጉ ያለምንም መጉላላት መመለስና ሥራዎንም ህጋዊነቱ በተጠበቀ መልኩ መቀየር ይችላሉ፣ ✅  የጉልበት ብዝበዛና እንግልትን ጨምሮ ከበርካታ የህገ-ወጥ ከስደት ስጋቶች ነፃ ይሆናሉ! ✅ በጉዞዎና በሥራ ቆይታዎ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስት ድጋፍና ክትትል የማግኘት ዕድል ያገኛሉ፣ 📢 ደህንነቱ የተረጋገጠና ህጋዊ የሥራ ስምሪት ለማግኘት👇 1️⃣ ህጋዊ ፍቃድ የተሰጣቸውን የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችን ብቻ ይጠቀሙ! ህጋዊ ፈቃድ ያላቸውን የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም (https://mols.gov.et/agencies/) ማግኘት ይችላሉ፣  2️⃣  ስለ ስምሪቱ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ይፋዊ ድረ-ገጽ፣ ማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም ከብሔራዊና ተዓማኒነት ካላቸው መገናኛ ብዙሃን  ተቋማት እንዲሁም በአቅራቢያዎ ከሚገኘውን የአንድ ማእዕል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ብቻ ያግኙ፣ 3️⃣  ህጋዊ ሂደቱን ይከተሉ፣ በ🇪🇹የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ይመዝገቡ፣ ይሰልጥኑ እና ብቃትዎን በምዘና ያረጋግጡ! ✨ልብ ይበሉ!✨ ✅  ህገ-ወጥ አቋራጮችን ያስወግዱ። ህጋዊ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ብቻ ምርጫዎ ያድርጉ❗️ ✅  ይህን መረጃ ለወዳጅ ጓደኛዎ በማጋራት #ከመሄድዎበፊትይሰልጥኑ ይበሏቸው፡፡ #LegalOverseasEmployment #OverseasOpportunities  #ህጋዊአማራጭ  #ደህንነቱየተጠበቀሥራስምሪት  ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ የካቲት 10፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

#ዜና | ወጣቶች በተግባር ተኮር ብቃት የስራ ላይ ልምምድ ተግተው በመስራት እራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን መጥቀም እንደሚገባቸው ተገለፀ። #Diretv አማርኛ የካቲት 7/2017 የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የስራ ልምምድ የሁለተኛ ዙር ማጠቃለያ እና የሶስተኛው ዙር ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሂዷል። በተዘጋጀው መርሃግብር ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሀር እንደገለፁት በተግባር ተኮር ስልጠና ለወሰዱ ሰልጣኞች የስራ እድል ላመቻቹ ቀጣሪ ተቋማትን አመስግነው ሰልጣኞች በሰለጠኑት የሞያ ዘርፍ ሀላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ አደራ ብለዋል። በመድረኩ ላይ በእንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የስራና ክህሎት ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ ባደረጉት ንግግር የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ፕሮጀክት የወጣቱን ተጠቃሚነት የሚያጎሉ ስራዎች ተግባራዊ እየሆነ እንደሚገኝ ገልፀው ለሰልጣኞች በቀጣይ የስራ መስኮች የሚረዱ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስተላልፈዋል። የአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው "ብቃት" የወጣቶች የስራ ልምምድ የወጣቱን ህይወት ከመቀየር ባሻገር ለሀገር እና ለቤተሰብ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል። አክለውም ሰባ በመቶ የሚሆኑት ወጣት ሴቶች መሆናቸውን አብራርተው በአጠቃላይ በነዚህ ስድስት ወራቶች 671 ሰልጣኞች በብቃት መጨረሳቸውን ተናግረው በጥቅሉ በዓመት ውስጥ 2,500 ወጣቶች በስልጠናው እንደሚያልፉ አስረድተዋል። በመርሃግብሩ ላይም በፕሮጀክቱ ሰልጥነው ህወታቸውን የቀየሩ ወጣቶች ተሞክራቸውን ያቀረቡ ሲሆን ለሁለተኛ ዙር አሰልጣኞች እና ቀጣሪ ተቋማት የምስጋና የእውቅና ሰርተፌኬት ተበርክቶላቸዋል። በመርሃግብሩ ላይ ከፌዴራል እና ከአስተዳደሩ የተጋበዙ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ቀጣሪ ተቋማቶች ተገኝተዋል። ©️ ድሬ ቲቪ