Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 084
المشتركون
+524 ساعات
+107 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
#ዜና|በፋብሪካዎች ውስጥ የሚሰሩ የተለያዩ ሞያተኞችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ እንዲሆኑ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የተውጣጡ ባለሙያዎችን በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡
ስልጠናው ለ11 የናሽናል ሲምንቶ መካኒካል ክፍል ባለሙያዎችና 5 የኤሌክትሪካል ክፍል ባለሙያዎች በብየዳ ሙያ በMMAW (manual metal arc welding) Advance welding training module one እንዲሁም በ pneumatic, Electro Pneumatic, Hydraulic & Electro Hydraulic & Advance PLC ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ስልጠናው ሙሉ በሙሉ በከፍተኛ ባለሞያዎች በሆኑ አሰልጣኞች እየተሰጠ ሲሆን በቀጣይም ስልጠናውን አጠናቀው ወደ ተቋማቸው ሲመለሱ በሰለጠኑት ሙያ ለውጥ ማምጣት እንደሚያስችላቸው ሰልጣኞቹ በስልጠናው ወቅት ገልጸዋል፡፡
ይህን ስልጠና የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን ኮሌጁ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር ባለው ትስስር ለተለያዩ ፋብሪካ ባለያዎችን ቀጣይነት ባለው መልኩ አቅማቸውን የማጎልበት ስራዎች የሚሰራ ይሆናል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#ዜና| በኮሌጁ ውስጥ የተሰሩ ተቋማዊ ስራዎችን ለተቋሙ ሰራተኞች እንዲሁም ለባለድርሻ አካላት በየግዜው ማሳወቅ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ የ2017 ዓም የ6 ወር የኮሌጅ መደበኛና የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት በዛሬው እለት በኮሌጁ አዳራሽ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀረበ፡፡
በተያዘው በጀት አመት የመጀመሪያው 6 ወር በኮሌጁ በርከት ያለ ስራ በውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና፤በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር በመምህራንና በአስተዳደር ሰራተኞች ልማት፣የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ስራዎችን በመስራት ውስጠ ገቢን ከማሳደግ አንጻር እንዲሁም ማህበረሰቡን ሊጠቅሙ የሚችሉ የበጎ አድራጎት ስራውችን፤የEASTRIP ፕሮጀክት ስራዎችን በተሻለ ለመስራት አቅዶ የተንቀሳቀሰ እንዳለ የገለጹት የኮሌጁ ም/ዲን እና ውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ሲሆኑ አያይዘውም ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አንጻር ኮሌጁ አመርቂ ስራዎችን በ6 ወር ውስጥ ለመስራት ተችሏል ያሉ ሲሆን፡፡ለቀጣይ 6 ወር እቅድ አፈጻጸም ደግሞ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰቦች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ሆነን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
የኮሌጁን የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም በአቶ ዘየደ ተክሌ በኩል የቀረበ ሲሆን የፕሮጀክቱን አፈጻጸም ደግሞ አቶ በአቶ መሳይ ጥላሁን የፕሮጀክቱ M & E specialist ቀርቧል፡፡ የቀረበውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ የኮሌጁ ማህበረሰብ ለኮሌጁ አመራሮች እና ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ዩኒት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ያቀረቡ ሲሆን የኮሌጁ አመራሮች በቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ መልስ የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከሉን ግንባታ ሂደት በጋራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሮክቶሬት በአስተዳደር ደረጃ የሥራ ገበያ ፍላጎት ጥናት ዝግጀት መጀመሩን አስታወቀ፡፡
ጥናቱ የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ክህሎት መር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በማቅረብ የአምራችና አገልግሎት ኢንዱስትሪውን የሰለጠነ ሰው ኃይል ፍላጎት ቀጣይነት ባለው ሂደት ማሟላት የሚጠበቅበት ሲሆን የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪውን ቀጣይ የመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦት መለየት ላይ አተኩሮ እንደሚዘጋጅ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን አስረድተዋል፡፡
በተለይም የጥናቱን ተዓማኒነትና እውነተኛነት ለማረጋገጥ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የጥናት ባለሙያዎችን በመምረጥና በማደራጀት አንድ የጥናት ቡድን በማዋቀር በልምድና በትምህርት ዝግጅታቸው የተሻለ ብቃት ያላቸውን በመምረጥ ጥናቱን እንዲያከናውኑ ማስጀመር መቻሉን አቶ ጀማል ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 14/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በአስተዳደሩ ከአራቱም ክላስተሮች ለተወጣጡ ወጣቶች በ Sanitation Concrete Slab ላይ ስልጠና ተሰጠ::
ስልጠናው በጤና ቢሮ አማካኝነት ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ 20 ሰልጣኞች በMarketing Based Sanitation Concrete Slab Training የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞችም ለሰባት ተከታታይ ቀናት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው አጠናቀዋል::
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች የእውቅና ሰርተፊኬቱን ያበረከቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በእለቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሰልጣኞች እዚህ በኮሌጁ የወሰዱትን ስልጠና መሰረት እድርገው በየአካባቢያቸው የሚስተዋለውን የመፀዳጃ ቤት ችግሮችን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባቸውም ተናግረዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 12/2017 ዓ.ም
በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ለአጠቃላይ ሠራተኛው የ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ስድስት ወር የተከለሰ ዕቅድ በአንድ ዕቅድ በአንድ ሪፖርት መሠረት በመከለስ ወደ ተግባር ማስገቢያ የስልጠና መድረክ ተካሄደ።
በቢሮው ከዚህ በፊት የነበረው የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት በብዙ መልኩ ውስንነቶች የነበሩትና ሁሉም የተቋሙ ፈፃሚ አካላት የሚሰሯቸውን የዕለት ተዕለት ስራዎች ሙሉ በሚባል ደረጃ ያካተተ አለመሆኑና ይህም ስትራቴጂክ ግቦችና ዝርዝር ተግባራትን ለፈፃሚው ለማውረድ አስቸጋሪ ሁኔታዎች የነበሩ መሆኑ በእነዚህ ችግሮች መነሻነት የቢሮውን እቅድ በአግባቡ በመከለስ ፈፃሚው እንዲያውቀውና ግብዓቶችን እንዲያክልበት ለማድረግ የሚያስችል ስልጠና ተሰጥቷል።
በዋናነት የዛሬው መድረክ የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት ከዚህ በፊት የቢሮው አካላት ዕቅዶች ሲታቀዱ የነበረበት መንገድ እና ከአስቀመጡት ግብ አንጻር የሚመዘኑበት እንዲሁም ውጤትን ለመለካት የማያስችል አካሄድን በመሰረታዊነት ሊያሻሽል የሚችል ወጥነት ያለው የአንድ ዕቅድ እና የአንድ ሪፖርት የአሰራር ስርዓት በቀጣይ ስድስት ወራት በመከለስ መዘርጋት የሚያስችል መሆኑን በቢሮው የፕላን እና ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ይታገስ ካሳሁን ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🛑ከህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች ራስዎን ይጠብቁ!🛑
⚠️ 🇨🇦ካናዳና 🇪🇺አውሮፓን ጨምሮ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት እንልካለን የሚሉ ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎች በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡ ይህን አይነቱ ማስታወቂያ፡-
➡️ ላልተፈለገ ወጪና እንግልት ይዳርጎታል፣
➡️ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰንሰለት ለከፋ አደጋም ያጋልጥዎታል፣
🌍 ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈራረመችባቸውና ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሚደረግባቸው ሀገራት የሚከተሉት ብቻ ናቸው 👇
1️⃣ ሳውዲ አረቢያ 🇸🇦
2️⃣ የተባበሩ አረብ ኤሜሬት🇦🇪
3️⃣ ዮርዳኖስ 🇯🇴
4️⃣ ሊባኖስ (በጊዜያዊነት ስምሪት የማይደረግበት)🇱🇧
5️⃣ ኳታር 🇶🇦
🚨 ማሳሰቢያ
❌ከላይ ከተጠቀሱት ውጪ ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሚሰጥባቸው መዳረሻ ሀገር የሉም፣
✅የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሀገራት በተጨማሪ ከተለያዩ ካምፓኒዎች ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፣
✅በዚህም ከላይ ከተጠቀሱት ሀገራት ውጪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ #ብቻ ስምሪት ሊሰጥ ይችላል፣
❌ለዚህ አይነት ስምሪት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ለየትኛውም ሌላ አካል #ፍቃድም ሆነ #ውክልና አልሰጠም፣
✍️ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን👇
✅ወቅታዊና በቂ መረጃ ይኑርዎ!
✅አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥሞ በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የህግ አስከባሪ አካላትና በየደረጃው ለሚገኝ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መዋቅር ያሳውቁ!
✅በዘርፉ ላልዎት ማንኛውም ጥያቄና አስተያየት ☎️9138 ነፃ የስልክ መስመርን ይጠቀሙ!
✅በመንግስት ተቋማት በሚሰጠው ስልጠናና የብቃት ምዘና ምንም አይነት ክፍያ አይከፈልም፣
📢 ይህን መልዕክት ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ♻️
✅ይህንን መረጃ በማጋራት ሌሎችም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይጋለጡ ያድርጉ❗️
አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዋናነት ያሰለጠኗቸውን ሰልጣኞች የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ እንዲወስዱ ማድረግ ላይ ያተኮረ ሲሆን በተጨማሪም በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠንና በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል በማስመዘን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትና ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የትምህርትና ስልጠናዉን የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎትና ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የተሰጠው ይህ ስልጠና የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በሰልጣኝ መረጃ አያያዝ፤ በሰልጣኝ መረጃ ሪፖርት አቀራረብ እንዲሁም በማሰልጠኛ መሳሪዎች ዝግጅት በአጠቃላይ በአሰልጣኝ እና በማሰልጠኛ ተቋማት አቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ ሆኗል፡፡
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ልክ መደበኛ ስልጠናዎች ሁሉ አጫጭር ስልጠናዎችም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው የተቋማቱን አቅም መገንባት አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ የአስተዳደሩ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፣ የግል ማሰልጠኛ ተቋማት እንዲሁም ከቢሮው የሚመለከታቸው አከካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ከመንግስትእና የግል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተወጣጡ አሰልጣኝ መምህራን ሲዘጋጅ የነበረ የተቋም ውስጥ ምዘና የንድፈ_ሀሳብ_ፈተና( Knoweldege Assessment )፣ የተግባር_ፈተና ( Practical Assessment )፣ የምዘና_ፓኬጅ፣ የተመዛኝ_ፓኬጅ ( Candidate Package )፣ assser package እና ለምዘናው_የሚያስፈልገው_ግብዓት ( Material for assessment package ኤሌክትሪክ፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፋክቸሪንግ ማሽንግና ሜካኒክስ፣ ቢዝነስ አካውንቲግና የሰው ሃብት አስተዳደር፣ በፋሽን ዲዛይን፣ ሚድዋይፈሪ፣ ነርሲንግ፣ ኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽን፣ በእንጨት ስራ ቴክኖሎጂ፣ በኮንስትራክሽን እና ካደስተራል ሰርቬይንግ፣ በምግብና መስተንግዶ በጠቅላላ 22 ሙያዎች ተዘጋጅተው በስራ ላይ እንዲውሉ ተደረገ፡፡
ይህም የስልጠናውን ጥራትና የበቃ ባለሞያ ለማፍራት የሚደረገውን ጥራት ሚያሻሽል ሲሆን ለቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የሚሰጡ የስልጠና ፕሮግራሞች በሚፈለገው ደረጃ ለሰልጣኙ አስፈላጊውን እውቀት፣ ችሎታ እና አመለካከት የሚያዳብር ይሆናል፤ ፕሮግራሙን በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች በስራው አለም ውስጥ በተመረቁበት ሙያ በሚጠበቅባቸው ብቃቶች በመሰረታዊነት ለመስራት ብቁ ያደርጋቸዋል፤ በዚህም ይህ የተቋም ውስጥ ምዘና መሳሪያዎች ዝግጅት የሥልጠና ፕሮግራም ዋና ዓላማ ሆነውን ሰልጣኙን በአመለካከት፣ በእውቀትና ክህሎት ማስታጠቅ እንደሆነ በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
