uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 069
Obunachilar
+224 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ከ2014-2017 ዓ.ም በስድስት የተለያዩ አገር በቀል እውቀቶች ላይ የተደረገ የዳሰሳ ጥናት ቀረበ፡፡ በዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ የሙያ አይነቶች •  እደ ጥበብ (የሐረሪ ኮፍያ) •  ባህላዊ ህክምና •  የአሉሚኒየም ውጤቶች •  የንብ ማነብ •  ብረታ ብረት •  ባህላዊ ሽመና በዚሁም መሰረት በ2017 ዓ.ም ላይ የአሰልጣኝና የሰልጣኝ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሰነድ ለማዘጋጀት በሁሉም በአስተዳደሩ ወረዳዎች መጠይቅ በመሙላት የተሰበሰበና የዳሰሳ ጥናቱ የተዘጋጀ መሆኑና በቀጣይም በተለዩት ሙያዎች ለስልጠና የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፤ የስልጠና ቦታና አሰልጣኞችን በማዘጋጀት ለአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊ ዜጎች አማራጭ የስራ ዕድል እንደሚፈጠር የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from E-LMIS - ብቁ
የስራ ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች! የሥራ አይነት፡ ሞግዚት /Nanny/ የሥራ ቦታ፡ ኳታር ብዛት፡ ሰማንያ (80) ጾታ፡ ሴት (ሴ) ሀይማኖት፡ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነች እድሜ፡ ወጣት (18
የስራ ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች! የሥራ አይነት፡ ሞግዚት /Nanny/ የሥራ ቦታ፡ ኳታር ብዛት፡ ሰማንያ (80) ጾታ፡ ሴት (ሴ) ሀይማኖት፡ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነች እድሜ፡ ወጣት (18 እስከ 40) መስፈርት፡ ቢያንስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቀች፣ የአእምሮ እና የጤና እክል የሌለባት፣ ቶሎ ከአካባቢው ጋር መላመድ የምትችል፣ ጥሩ ስነምግባር ያላት፣ ታማኝ እና ቀልጣፋ የሆነች። ተጨማሪ ክህሎት፡ የቋንቋ ችሎታ ዐረቢኛ የቅጥር ሁኔታ፡ የተመረጡ ዜጎች ለ6 ወራት በኳታር የሞግዚት ማሰልጠኛ አካዳሚ /Qatar Nanny Training Academy/ ውስጥ ተከታታይ ስልጠና ይወስዳሉ። በስልጠና ቆይታቸው፤ መጠለያ፣ ምግብ፣ የጤና ኢንሹራንስ፣ አበል፣ እና የቲኬት ወጪ በማሰልጠኛ ተቋሙ የሚሸፈን ሲሆን ከስልጠና በኋላ በማሰልጠኛ ተቋሙ በሚደረግ የቅጥር ምደባ ወደ ስራ የሚገቡ ይሆናል። በስራ ላይ ሆነው ሙሉ የጤና ኢንሹራንስ ቀጣሪው ድርጅት ይሸፍናል ማሳሰቢያ፡ በዚህ የሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ካዛንቺስ በሚገኘው የሥራ ስምሪት ቢሮ ያላችሁን የት/ት ማስረጃ፣ መታወቂያ/ፓስፖርት/መንጃ ፍቃድ እንዲሁም ሌሎችን ማስረጃዎችን በመያዝ፤ በአካል በመምጣት ወይም ይህንን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም (https://forms.gle/KBwUTKYYJBXipGbb6) እስከ ሰኔ 11 2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። በግል የስልክ ቁጥራችሁን በE-LMIS ስርዓት ላይ (lmis.gov.et) የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ተመዝግባችሁ የሰራተኛ መለያ ቁጥር ማግኘት ይጠበቅባችኋል። የሰው ሃይል ጥያቄውን ያቀረቡት ድርጅቶች እራሳቸው በE-LMIS ሲስተም በኩል አወዳድረው ስለሆነ የሚቀጥሩት ከላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች ማሟላት የግድ ይጠበቅባችኋል።

በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የስልጠና አሰጣጥ ትግበራ የምልከታ መድረክ መካሄድ ጀመረ:: ሰኔ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመት በኮሌጅ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ የግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል:: ለግምገማ መድረኩ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት የአውቶሞቲቭ እና የአይ.ሲ.ቲ ዲፓርትመንቶች በ2017 ዓ.ም ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት የማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮምሽን አባላት በተገኙበት ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሰረትም ሰፊ ውይይቶች ተካሂደው ግብረ-መልስ ተሰጥቶባቸዋል:: የግምገማ መድረኩ ዋና አላማ በበጀት አመቱ በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተሻለ ደረጃ የተከናወኑ አፈፃፀሞችን ይበልጥ ተጠናክረው እዲቀጥሉ ለማስቻል እንዲሁም እንደ ክፍተት በተለዩ ችግሮች ላይ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ለማስቻልም እንደሆነ ተገልፇል:: በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶችም ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

በልምድ የተገኘ ክህሎትን በሙያ ምዘና ማረጋገጥ (Recognition of Prior Learning) ምንድን ነው? RPL ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በስራ ልምድ ኢ-መደበኛ በሆነ መንገድ የዳበረ ክህሎት ራስን በማጥናት በታወቀ ተቋም የሚገመገምበት እና የሚረጋገጥበት መደበኛ ሂደት ነው። በተለይ የRPL ሚና በክህሎት ልማት ቀላል የማይባል ሲሆን ከኢ-መደበኛ ወደ መደበኛ ትምህርት ድልድይ በመሆን ከተለመደው ትምህርት ውጭ ለተማሩ የክህሎት ባለቤቶች ትኩረት የሚሰጥ ይሆናል፤ በዚህም ቀደም ሲል በሚያውቁት መሰረት ግለሰቦች የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያግዛቸው ሲሆን ዜጎች በስራው አለም ውጤታማ እንዲሆኑ ለትምህርት ወደ ኋላ መመለስ ሳይጠበቅባቸው የክህሎት እድገታቸውን የሚያሻሽሉበት እድል ይፈጥርላቸዋል። RPL በዋናነት ልምድ ያላቸው ባለሞያ ዜጎች መደበኛ ሥልጠና ያልተከታተሉ ነገር ግን የተግባር ብቃት አላቸውን፤ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራም ወደ ሚቀጥለው ደረጃ ለመሸጋገር የዕውቅና ማረጋገጫ ወይም ለሚፈልጉ ግለሰቦች እንዲሁም ሥራ መቀየር ወይም የችሎታ አቅማቸውን ለማሻሻል ፍላጎት ያላቸውን ተደራሽ የሚያደርግ ይሆናል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ኤጀንሲ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ማለትም በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣  በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ሲገኝ ይህንንም በሌሎች ተጨማሪ ዘርፎች በማስፋት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በልምድ የተገኘ ክህሎትን በሙያ ምዘና ማረጋገጥ (Recognition of Prior Learning) ምንድን ነው? RPL ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በስራ ልምድ ኢ-መደበኛ በሆነ መንገድ የዳበረ ክህሎት ራስን በማጥናት በታወቀ ተቋም የሚገመገምበት እና የሚረጋገጥበት መደበኛ ሂደት ነው። በተለይ የRPL ሚና በክህሎት ልማት ቀላል የማይባል ሲሆን ከኢ-መደበኛ ወደ መደበኛ ትምህርት ድልድይ በመሆን ከተለመደው ትምህርት ውጭ ለተማሩ የክህሎት ባለቤቶች ትኩረት የሚሰጥ ይሆናል፤ በዚህም ቀደም ሲል በሚያውቁት መሰረት ግለሰቦች የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያግዛቸው ሲሆን ዜጎች በስራው አለም ውጤታማ እንዲሆኑ ለትምህርት ወደ ኋላ መመለስ ሳይጠበቅባቸው የክህሎት እድገታቸውን የሚያሻሽሉበት እድል ይፈጥርላቸዋል። RPL በዋናነት ልምድ ያላቸው ባለሞያ ዜጎች መደበኛ ሥልጠና ያልተከታተሉ ነገር ግን የተግባር ብቃት አላቸውን፤ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራም ወደ ሚቀጥለው ደረጃ ለመሸጋገር የዕውቅና ማረጋገጫ ወይም ለሚፈልጉ ግለሰቦች እንዲሁም ሥራ መቀየር ወይም የችሎታ አቅማቸውን ለማሻሻል ፍላጎት ያላቸውን ተደራሽ የሚያደርግ ይሆናል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ኤጀንሲ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ማለትም በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣  በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ሲገኝ ይህንንም በሌሎች ተጨማሪ ዘርፎች በማስፋት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ትግበራ የመጀመሪያ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤      ወጣቶቹ  በዚህ የመጀመሪያ ዙር የአቻ ለአቻ  ውይይት በየጊዜው ያገኙትን ዕውቀት የገጠማቸውን ችግሮች ለይተው የተወያዩበት መድረክ  ሲሆን ይህም ለተከታታይ ሌሎች ዙሮች የሚቀጥል ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁም በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት የሚያገለግሉ ይሆናል፡፡      በአስተዳደሩ የፕሮግራሙ ሶስተኛ ዙር ትግበራ 1200 በላይ ሰልጣኞች  የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 973 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችን በየወሩ ሲወያዩ የሚቆዩ ይሆናል፡፡      በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበር መጀመራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በመጀመሪያው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ጋር የጋራ መድረክ የተፈጠረ ሲሆን በቀጣይ ትኩረት ማድረግ በሚገባቸው ነገሮች ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 8/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች አጠቃላይ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡ መድረኩ በዋናነት በ2017 በጀት ዓመት በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በተደረገ ድጋፍና ክትትል የተሰጡ  ግብረ-መልሶችን መነሻ በማድረግ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የኮሌጅ ዲኖች እና የወረዳ አንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ አድርጓል፡፡ በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ዘርፍ በጥንካሬ የታዩትን ለማስቀጠል እንዲሁም በድክመት በታዩት ስራዎች ላይ ደግሞ የጋራ ውይይት ለማድረግና መግባባት ላይ በመድረስ ለመጪው አዲስ የስራ ዘመን የሚዘጋጁ ዕቅዶች የእነዚህን ተግባራት የአፈፃፀም ውጤት ማላቅን መሰረት ያደረጉና በዚህ ልክ የተቃኙ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል፡፡ በዚህም የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በአገር አቀፍ ብሎም በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ከስራ እድል ፈጠራና ዜጎች በሚፈጠሩ አዳዲስ ስራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ ሂደት ከተወጠነው ዕቅድ አንፃር በመጪው የክረምት ወራት እንደ አንድ የትኩረት መስክ ሆነው በተለየ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶባቸው እንዲሰሩ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም በቢሮው ስር ሆኖ ትኩረት ተሰጥቶት እየተመራ የሚገኘው የአስተዳደሩ የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራን ለማጠናክርና አቅምን ለማሳደግ የሚረዱ  ኮምፒውተሮች በአራቱም ክላስተሮች(ወረዳዎች) ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የዜጎች በልምድ የተገኘ  የስራ እውቀትን በመመዘንእውቅና መስጠት እንደሀገር  በስራው ዘርፍ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ ። በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ቢሮ በልምድ የተገኘ ሙያን ወደ ምዘና ለማስገባት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር    ዜጎች በልምድ ያካበቱትን እውቀት ና ክህሎት እውቅና ሰጥቶ በመመዘን ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ይገኛል። ድሬዳዋ  አስተዳደር   ስራና ክህሎት ቢሮ ከ2009 ጀምሮ  በአራት የሞያ ዘርፎች በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣  በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ይገኛል ።  ይህንንም በማስመልከት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። በመድረኩም የአስተዳደሩ የስራ ና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት  በልምድ እና በእውቀት የሚገኙ የስራ ዘርፎችን እውቅና መስጠት ተወዳዳሪና የበቁ ዜጎች በማፍራትእንደሀገር ምርትና ምርታማነት  ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው ለተግባራዊነቱም ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል ። በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በተጠቀሰው ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ  ከተሳታፊዎች ጋር  ውይይት ተደርጎበታል። በግንዛቤ መድረኩላይም ያነጋገርናቸው የባለድርሻ አካላት በልምድ የተገኙ እውቀቶች እውቅና ተሰጥቶ መመዘናቸው በስራው ዘርፍ ተወዳዳሪ ና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ። ©️ Dire Tv አማርኛ

የዜጎች በልምድ የተገኘ የስራ እውቀትን በመመዘንእውቅና መስጠት እንደሀገር በስራው ዘርፍ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ ። በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ቢሮ በልምድ የተገኘ ሙያን ወደ ምዘና ለማስገባት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል ። የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች በልምድ ያካበቱትን እውቀት ና ክህሎት እውቅና ሰጥቶ በመመዘን ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ይገኛል። ድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ከ2009 ጀምሮ በአራት የሞያ ዘርፎች በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣ በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ይገኛል ። ይህንንም በማስመልከት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። በመድረኩም የአስተዳደሩ የስራ ና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት በልምድ እና በእውቀት የሚገኙ የስራ ዘርፎችን እውቅና መስጠት ተወዳዳሪና የበቁ ዜጎች በማፍራትእንደሀገር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው ለተግባራዊነቱም ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል ። በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በተጠቀሰው ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጎበታል። በግንዛቤ መድረኩላይም ያነጋገርናቸው የባለድርሻ አካላት በልምድ የተገኙ እውቀቶች እውቅና ተሰጥቶ መመዘናቸው በስራው ዘርፍ ተወዳዳሪ ና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ። ©️ Dire Tv አማርኛ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የሥራ ገበያ ፍላጎት ጥናት ማጥናቱን አስታወቀ። የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የስልጠና መነሻ የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎች የመካከለኛ ደረጃ የቴክኒክና ሙያ ቴክኒሺያኖች አቅርቦት በመሆኑ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት የዘርፉን ስልጠና በውጤታማነትና በሰኬት መምራትና መተግበር እንዲቻል የአካባቢውን ኢንዱስትሪዎች የቀጣይ ዓመታት የሰለጠነና የበቃ የሰው ኃይል  አቅርቦትና ፍላጎት በመለየት ስልጠና ማቅረብ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። ጥናቱ የተካሄደው በራስ አቅም በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ ሰፊ ልምድና ችሎታ ባላቸው ምሁራን በመሆኑ ለጥናቱ አስተማማኝነትና ጥራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው  የጥናቱ ሰነድ ለግምገማ በቀረበበት ወቅት ተብራርቷል። የጥናቱ ሰነድ ለግምገማ በቀረበበት ወቅት ጥናቱ ያለፈበትን አጠቃላይ ሂደትና የደረሰበትን ውጤት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደን ሲሆኑ የጥናቱ ውጤት በሚቀጥለው ሳምንት ለባለድርሻና ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚቀርብ አብራርተው ጥናቱን ላጠኑና ላስተባበሩ ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ