1 068
Подписчики
+424 часа
-27 дней
+230 день
Архив постов
በልምድ የተገኘ ክህሎትን በሙያ ምዘና ማረጋገጥ (Recognition of Prior Learning) ምንድን ነው? RPL ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በስራ ልምድ ኢ-መደበኛ በሆነ መንገድ የዳበረ ክህሎት ራስን በማጥናት በታወቀ ተቋም የሚገመገምበት እና የሚረጋገጥበት መደበኛ ሂደት ነው።
በተለይ የRPL ሚና በክህሎት ልማት ቀላል የማይባል ሲሆን ከኢ-መደበኛ ወደ መደበኛ ትምህርት ድልድይ በመሆን ከተለመደው ትምህርት ውጭ ለተማሩ የክህሎት ባለቤቶች ትኩረት የሚሰጥ ይሆናል፤ በዚህም ቀደም ሲል በሚያውቁት መሰረት ግለሰቦች የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያግዛቸው ሲሆን ዜጎች በስራው አለም ውጤታማ እንዲሆኑ ለትምህርት ወደ ኋላ መመለስ ሳይጠበቅባቸው የክህሎት እድገታቸውን የሚያሻሽሉበት እድል ይፈጥርላቸዋል።
RPL በዋናነት ልምድ ያላቸው ባለሞያ ዜጎች መደበኛ ሥልጠና ያልተከታተሉ ነገር ግን የተግባር ብቃት አላቸውን፤ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራም ወደ ሚቀጥለው ደረጃ ለመሸጋገር የዕውቅና ማረጋገጫ ወይም ለሚፈልጉ ግለሰቦች እንዲሁም ሥራ መቀየር ወይም የችሎታ አቅማቸውን ለማሻሻል ፍላጎት ያላቸውን ተደራሽ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ኤጀንሲ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ማለትም በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣ በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ሲገኝ ይህንንም በሌሎች ተጨማሪ ዘርፎች በማስፋት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በልምድ የተገኘ ክህሎትን በሙያ ምዘና ማረጋገጥ (Recognition of Prior Learning) ምንድን ነው? RPL ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በስራ ልምድ ኢ-መደበኛ በሆነ መንገድ የዳበረ ክህሎት ራስን በማጥናት በታወቀ ተቋም የሚገመገምበት እና የሚረጋገጥበት መደበኛ ሂደት ነው።
በተለይ የRPL ሚና በክህሎት ልማት ቀላል የማይባል ሲሆን ከኢ-መደበኛ ወደ መደበኛ ትምህርት ድልድይ በመሆን ከተለመደው ትምህርት ውጭ ለተማሩ የክህሎት ባለቤቶች ትኩረት የሚሰጥ ይሆናል፤ በዚህም ቀደም ሲል በሚያውቁት መሰረት ግለሰቦች የብቃት ማረጋገጫ እንዲያገኙ የሚያግዛቸው ሲሆን ዜጎች በስራው አለም ውጤታማ እንዲሆኑ ለትምህርት ወደ ኋላ መመለስ ሳይጠበቅባቸው የክህሎት እድገታቸውን የሚያሻሽሉበት እድል ይፈጥርላቸዋል።
RPL በዋናነት ልምድ ያላቸው ባለሞያ ዜጎች መደበኛ ሥልጠና ያልተከታተሉ ነገር ግን የተግባር ብቃት አላቸውን፤ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራም ወደ ሚቀጥለው ደረጃ ለመሸጋገር የዕውቅና ማረጋገጫ ወይም ለሚፈልጉ ግለሰቦች እንዲሁም ሥራ መቀየር ወይም የችሎታ አቅማቸውን ለማሻሻል ፍላጎት ያላቸውን ተደራሽ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ኤጀንሲ በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ማለትም በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣ በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ሲገኝ ይህንንም በሌሎች ተጨማሪ ዘርፎች በማስፋት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሶስተኛ ዙር ትግበራ የመጀመሪያ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤
ወጣቶቹ በዚህ የመጀመሪያ ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት በየጊዜው ያገኙትን ዕውቀት የገጠማቸውን ችግሮች ለይተው የተወያዩበት መድረክ ሲሆን ይህም ለተከታታይ ሌሎች ዙሮች የሚቀጥል ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁም በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት የሚያገለግሉ ይሆናል፡፡
በአስተዳደሩ የፕሮግራሙ ሶስተኛ ዙር ትግበራ 1200 በላይ ሰልጣኞች የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 973 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችን በየወሩ ሲወያዩ የሚቆዩ ይሆናል፡፡
በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበር መጀመራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
በመጀመሪያው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ጋር የጋራ መድረክ የተፈጠረ ሲሆን በቀጣይ ትኩረት ማድረግ በሚገባቸው ነገሮች ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 8/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች አጠቃላይ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡
መድረኩ በዋናነት በ2017 በጀት ዓመት በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በተደረገ ድጋፍና ክትትል የተሰጡ ግብረ-መልሶችን መነሻ በማድረግ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የኮሌጅ ዲኖች እና የወረዳ አንድ ማዕከል አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ አድርጓል፡፡
በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ዘርፍ በጥንካሬ የታዩትን ለማስቀጠል እንዲሁም በድክመት በታዩት ስራዎች ላይ ደግሞ የጋራ ውይይት ለማድረግና መግባባት ላይ በመድረስ ለመጪው አዲስ የስራ ዘመን የሚዘጋጁ ዕቅዶች የእነዚህን ተግባራት የአፈፃፀም ውጤት ማላቅን መሰረት ያደረጉና በዚህ ልክ የተቃኙ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
በዚህም የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በአገር አቀፍ ብሎም በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ከስራ እድል ፈጠራና ዜጎች በሚፈጠሩ አዳዲስ ስራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረግ ሂደት ከተወጠነው ዕቅድ አንፃር በመጪው የክረምት ወራት እንደ አንድ የትኩረት መስክ ሆነው በተለየ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶባቸው እንዲሰሩ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም በቢሮው ስር ሆኖ ትኩረት ተሰጥቶት እየተመራ የሚገኘው የአስተዳደሩ የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራን ለማጠናክርና አቅምን ለማሳደግ የሚረዱ ኮምፒውተሮች በአራቱም ክላስተሮች(ወረዳዎች) ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የዜጎች በልምድ የተገኘ የስራ እውቀትን በመመዘንእውቅና መስጠት እንደሀገር በስራው ዘርፍ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ ። በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ቢሮ በልምድ የተገኘ ሙያን ወደ ምዘና ለማስገባት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች በልምድ ያካበቱትን እውቀት ና ክህሎት እውቅና ሰጥቶ በመመዘን ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ይገኛል።
ድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ከ2009 ጀምሮ በአራት የሞያ ዘርፎች በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣ በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ይገኛል ።
ይህንንም በማስመልከት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። በመድረኩም የአስተዳደሩ የስራ ና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት በልምድ እና በእውቀት የሚገኙ የስራ ዘርፎችን እውቅና መስጠት ተወዳዳሪና የበቁ ዜጎች በማፍራትእንደሀገር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው ለተግባራዊነቱም ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል ።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በተጠቀሰው ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጎበታል።
በግንዛቤ መድረኩላይም ያነጋገርናቸው የባለድርሻ አካላት በልምድ የተገኙ እውቀቶች እውቅና ተሰጥቶ መመዘናቸው በስራው ዘርፍ ተወዳዳሪ ና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ።
©️ Dire Tv አማርኛ
የዜጎች በልምድ የተገኘ የስራ እውቀትን በመመዘንእውቅና መስጠት እንደሀገር በስራው ዘርፍ የበቃ ዜጋን ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ ። በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎት ቢሮ በልምድ የተገኘ ሙያን ወደ ምዘና ለማስገባት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል ።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች በልምድ ያካበቱትን እውቀት ና ክህሎት እውቅና ሰጥቶ በመመዘን ብቁ ዜጋ ለማፍራት እየሰራ ይገኛል።
ድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ከ2009 ጀምሮ በአራት የሞያ ዘርፎች በሆቴልና ቱሪዝም፣ በግንባታ፣ በፅዳት እና ውበት እንዲሁም በግብርና ዘርፎች በልምድ የሚገኙ እውቀቶች እውቅና በመስጠት በመመዘን የበቁ ዜጎች እንዲፈጠሩ እየሰራ ይገኛል ።
ይህንንም በማስመልከት በአስተዳደሩ ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል። በመድረኩም የአስተዳደሩ የስራ ና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለፁት በልምድ እና በእውቀት የሚገኙ የስራ ዘርፎችን እውቅና መስጠት ተወዳዳሪና የበቁ ዜጎች በማፍራትእንደሀገር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው ለተግባራዊነቱም ሁሉም በጋራ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል ።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ በተጠቀሰው ርእሰ ጉዳይ ዙሪያ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጎበታል።
በግንዛቤ መድረኩላይም ያነጋገርናቸው የባለድርሻ አካላት በልምድ የተገኙ እውቀቶች እውቅና ተሰጥቶ መመዘናቸው በስራው ዘርፍ ተወዳዳሪ ና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ።
©️ Dire Tv አማርኛ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የሥራ ገበያ ፍላጎት ጥናት ማጥናቱን አስታወቀ።
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የስልጠና መነሻ የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎች የመካከለኛ ደረጃ የቴክኒክና ሙያ ቴክኒሺያኖች አቅርቦት በመሆኑ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት የዘርፉን ስልጠና በውጤታማነትና በሰኬት መምራትና መተግበር እንዲቻል የአካባቢውን ኢንዱስትሪዎች የቀጣይ ዓመታት የሰለጠነና የበቃ የሰው ኃይል አቅርቦትና ፍላጎት በመለየት ስልጠና ማቅረብ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ጥናቱ የተካሄደው በራስ አቅም በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ ሰፊ ልምድና ችሎታ ባላቸው ምሁራን በመሆኑ ለጥናቱ አስተማማኝነትና ጥራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው የጥናቱ ሰነድ ለግምገማ በቀረበበት ወቅት ተብራርቷል።
የጥናቱ ሰነድ ለግምገማ በቀረበበት ወቅት ጥናቱ ያለፈበትን አጠቃላይ ሂደትና የደረሰበትን ውጤት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደን ሲሆኑ የጥናቱ ውጤት በሚቀጥለው ሳምንት ለባለድርሻና ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚቀርብ አብራርተው ጥናቱን ላጠኑና ላስተባበሩ ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 5/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ለውጭ ሀገር የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች አዲስ የሥራ ፈቃድ ፣ የእድሳት፣ የክሊራንስና የጠፋና የተበላሸ ሥራ ፈቃድ ምትክ አገልግሎት በሥራ ገበያ መረጃ ድረገፅ www.lmis.gov.et አማካኝነት በቀጥታ እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
አሁን ደግሞ ተጠቃሚዎች የአገልግሎት ክፍያቸውን በቴሌብር አማካኝነት መፈፀም፣ የሚላክላቸውን IMV ቁጥር ተጠቅመው የሥራ ፈቃዳቸውን በድረ ገፁ ላይ ማግኘትና ወደ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መ/ቤት መምጣት ሳይጠበቅባቸው አትመው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ከዚህም በተጨማሪ አገልግሎቱን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በኩል ማግኘት እንደሚችሉም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
For All Foreign Work Permit Applicants
The Ministry of Labor and Skills now provides all foreign work permit services—including new applications, renewals, clearances, and replacements—online via www.lmis.gov.et.
Applicants can pay service fees through Telebirr, use the provided IMV number, and print their permits directly from the website—eliminating the need to visit the Ministry in person.
Services are also available at the Mesob One-Stop Service Center.
Ministry of Labor and Skills
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የገጠሩን ማህበረሰብ የሚጠቅሙ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
ከዚህም ውስጥ በኮሌጁ ማኑፋችቸሪንግ ትምህርት ክፍል መምህራን የተሰራው የዶሮ መኖ መፍጫና የከብት መኖ ቾፕ ማሽን አንዱ ነው፡፡
ይህ ማሽን በዋነኝነት ከውጪ የሚመጣ ሲሆን የኮሌጁ መምህራን ግን ሙሉ ማሽኑን በራስ አቅም መስራት የቻሉ ሲሆን በተጨማሪም ማሽኑ ላይ የተለያዩ ማሻሻያዎችን በማድረግ ዝግጁ እንዲሆን አድርገውታል፡፡ በዚህም ሃገራችን ማሽኑን ለማስገባት ታለው የነበረውን የውጪ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል፡፡
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
