uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 064
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-77 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በየመን በደረሰው የጀልባ መስጠም በዜጎቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልፃል፡፡ ለተጎጂ ቤተሰቦችም መጽናናትን ይመኛል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በየመን በደረሰው የጀልባ መስጠም በዜጎቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልፃል፡፡ ለተጎጂ ቤተሰቦችም መጽናናትን ይመኛል፡፡

በነሀሴ ወር ከባድ ዝናብ እንደሚኖር ተገለፀ በነሀሴ ወር በረዶ የቀላቀለና ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ። ኢኒስቲ
በነሀሴ ወር ከባድ ዝናብ እንደሚኖር ተገለፀ በነሀሴ ወር በረዶ የቀላቀለና ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ። ኢኒስቲትዩቱ እ.ኤ.አ ከኦገስት 1 እስከ 31/2025 የሚኖረውን የአየር ጠባይ ሁኔታ አስታውቋል። በነሃሴ ወር ከሚጠናከሩት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ጋር ተያይዞ በተለይም በሰሜን ምስራቅ፣ በሰሜን፣ በመካከለኛዉ፣ በደቡብ ምዕራብና በምዕራብ የሃገሪቱ ቦታዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ተጠቁሟል። በተጨማሪም በፀሐይ ሀይል ታግዘዉ ከሚፈጠሩ የደመና ክምችቶች በመነሳትም በረዶ የቀላቀለ እና ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል ተመላክቷል። በሌላ በኩል በአንዳንድ ቦታዎች ከሚኖረው ተደጋጋሚ የሆነ የእርጥበት መብዛት ጋር ተያይዞ በረባዳማ አካባቢዎች የውሃ በሰብል ላይ መተኛት፣ የመሬት አቀማመጡ ከፍታ ባላቸውና ተዳፋታማ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ የመሬት መንሸራተትና በጎርፍ መጠቃት ሊያጋጥም እንደሚችል ተገልጿል። እርጥበት በሚበዛባቸው አካባቢዎች የሰብል በሽታ እና የአረም መስፋፋት ሊከሰት ስለሚችል አርሶ አደሮችና የሚመለከታቸው አካላት ሰብሎች በጎርፍ እንዳይጠቁ እና በማሳ ላይ ውሃ እንዳይተኛ የጎርፍ መቀልበሻዎችንና ከማሳ ውሰጥ ውሃን ማስወገጃ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚገባ ተጠቁሟል። የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ደግሞ አልፎ አልፎ በሚኖረው ተደጋጋሚ ከባድ ዝናብ ቅጽበታዊ ጎርፍ የማስከተል እድል ይኖረዋል ሲል ተቋሙ ለመገናኛ ብዙሐን የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡ ©️ ኢፕድ

ኢንስቲትዩቱ በበጀት ዓመቱ በሁሉም ተልዕኮዎቹ ቁልፍ ስኬቶችን አስመዝግቧል። (ዶ/ር ብሩክ ከድር -የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬከተር) *ሀምሌ 28/2017**** የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ ተጀመረ። የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር ኢንስቲትዩቱ የተሰጡትን ተልዕኮዎች በበጀት ዓመቱ በልህቀት ለመፈጸም ጀምሮ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ እንደተቻለ ገልጸዋለ። በዓመተ-ልህቀት ፪ በተቋማዊ አቅም ግንባታ ሥራዎች ትኩረት ሰጥተን በመስራታችን ለሥራ የተመቸ ከባቢን በመፍጠር ትልቅ መነቃቃትን አምጥተናል ብለዋል። የስልጠና ጥራት ላይ በበጀት ዓመቱ ልዩ ትኩረት ተደርጎ በመሰራቱ እንደ ተቋምም ጥራት ያለው ስልጠናን ለማረጋገጥ ከሚሰራው ስራ በላይ እንደአገር ያለውን የስልጠና ጥራት ለማሻሻል ተሠርቷል ብለዋል። ጥናትና ምርምር በኢንስቲትዩታችን በባህል ደረጃ እንዲጠናከር፣ ተግባሮቻችን ዓለምአቀፋዊነትን እንዲላበሱ ሰርተናል ውጤትም አስመዝግበናል ብለዋል። በኢንስቲትዩቱ አዲስ የተጀመረው የቴክኖሎጂና ኢንተርፕራይዝ ልማት ሥራ ለኢንስቲትዩቱ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የስልጠና ተቋማት ሞዴል እንድንሆን ያስቻለ ውጤት እየተመዘገበበት እንደሆነ ዶ/ር ብሩክ ጨምረው ገልጸዋል። 2018 በጀት ዓመትን "የጥራት ዓመት" ብለው የሰየሙት ዋና ዳይሬክተሩ ይህም ኢንስቲትዩቱ ባለፉት 2ዓመታት ለጥራት የጀመረው ሥራ ይበልጥ ተጠናክሮ ሁሉም ተልዕኮዎች በጥራት እንዲፈጸሙ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል። በየዓመቱ መጀመሪያ ላይ የምንፈጥረው መግባባት ዓመቱን ሁሉ ለውጥ እንድናመጣ እየረዳን ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በዚህ የውይይት መድረክም 2017 በጀት ዓመትን በዝርዝር ከተልዕኮዎቻችን አኳያ እንገመግማለን ለሚቀጥለው ዓመት ዕቅድ መግባባት እንፈጥራለን ብለዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ኢንስቲትዩቱ ለክልሉም ሆነ ለአገር ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት ብቁ አመራሮችን እና አሠልጣኞችን እያፈራ እንደሆነ ገልጸው በዚህ መድረክ በሚፈጠር መግባባት በቀጣዩ ዓመት ይበልጥ ጥራት ያለው ስራ እንደሚሰራ እምነታቸውን ገልጸዋል። ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ እንደመሪ ተቋም በሚያመጣቸው ውጤቶች እኛም ተቋሞቻችንን ለማሻሻል መነሻ ይሆነናል ብለዋል። ©️ TVTI

#ዜና | የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሶስተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መካኒክ አሽከርካሪዎችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡ በሀገራችን እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳድር መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ አሽከርካራችን ማፍራት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የሶስተኛ ዙር ስልጠና ያጠናቀቁ አሽከርካሪዎችን በዛሬው እለት ያስመረቀ ሲሆን፡፡ ይህ ስልጠና መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ ዋናው አላማ ነው በተጨማሪም ብቃት ያለውና ተወዳዳሪ አሽከርካሪ በማፍራት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚያግዝ ትልቅ ስልጠና ነው ያሉ የኮሌጁ ም/ዲን አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ሲሆኑ አያይዘውም ለከተማችን ብሎም ለሃገራችን ብቁና ተወዳዳሪ አሽከርካሪዎችን ለማፍራት ቀጣይነት ባለው መልኩ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናዎችን በመስጠት አሽከርካሪዎችን የማብቃት ስራ ኮሌጁ በሰፊው የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ ቁጥጥር ዲቪዥን ባልደረባ የሆኑት ኢ/ር ካሳሁን እንዳሉት ይህ ስልጠና ብቃት ያለው መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በኮሌጁ የተሰጠውን ስልጠና ወስዳችሁ ላጠናቀቃችሁ ባለሙያዎች በቅድሚያ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም የስልጠናውን ውጤት በተግባር በመፈጸም በየእለቱ ልትተገብሩት ይገባል ብለዋል፡፡በስተመጨረሻም ኮሌጁ በቀጣይ ዙሮች በሚሰጠው ስልጠና ላይ ሌሎች ሰልጣኞች ተመዝግበው ስልጠናውን እንዲወስዱ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ መካኒክ አሽከርካሪዎች ስልጠና ይህ የሶስተኛ ዙር ሲሆን በዚህም ስልጠና ከ30 በላይ አሽከርካሪዎች የተሳተፉበት እንደሆነና አራተኛ ዙር ስልጠናም በቀጣይ እንደሚጀመር በእለቱ ተገልጿል ፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሀምሌ 26/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ ስለ ኮሌጁ ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

#ዜና| ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከመደበኛው ስልጠና በተጨማሪ ትምህርትና ስልጠናው ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን በተለያዩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ሴቶችን በአጫጭር ስልጠናዎች በማሰልጠን እና በማብቃት የእድገቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ34 በላይ ከወረዳ 06 የተውጣጡ ሴት ሰልጣኞችን ከድሬዳዋ አስተዳዳር ስራና ክህሎት ቢሮ፣ከድሬዳዋ አስተዳደር ሴቶችና ህጻናት ቢሮ፣ከወረዳ 06 እና ከሃናን ለችግር የተጋለጡ ሴቶችና ህጻናት መርጃ ማእከል ጋር በመተባበር በጸጉር ስራና በምግብ ሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች በዛሬው እለት አስመረቀ ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎት እና በስነምግባር የታነፀ ተነሳሽነት የተላበሰ አምራች ዜጋን በጥራት እና በብዛት በመፍጠር ረገድ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ እድገት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የገለጹት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም የሃገራችን ብልጽግና እንዲረጋገጥ በሁሉም ስፍራ የሚገኙ ወጣቶችን በተለይ ደግሞ ሴቶችን ያማከለ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ። በቀጣይም በዚህ ስልጠና የተሳተፉ ሴቶችን በማደራጀት እንዲሁም ከኮሌጁ ጋር በመተባበር የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ እንዲሰሩ እንደሚደረግ ገልጸዋል ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለት ያስመረቃቸው ሴቶች 19 በምግብ ስራ፣15 በጸጉር ስራ በተግባርና በንድፈ ሃሳብ የታገዘ ስልጠና ወስደው ማጠናቀቃቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመጨረሻም በስልጠናው የተሳተፉ እንዲሁም በምርቃቱ የተገኙ እንግዶች በጋራ በመሆን ችግኝ ተክለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሀምሌ 26/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ ስለ ኮሌጁ ትኩስና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት Facebook: facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/diredawapolytechniccollege YouTube: youtube.com/diredawapolytechniccollege

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በቢሮው ዳይሬክቶሬቶች እና ክፍሎች ስር ከሚሰሩ ባለሙያዎች ጋር የመግባቢያ መድረክ አካሄደ። በመድረኩም በዋናነት የበጀት አመቱ ዕቅድ በይበልጥ የዳበረና ሊያሰራ በሚችል መልኩ እንዲተገበር ለማድረግ የአስተዳደሩ ፕላን ኮሚሽን ባዘጋጀው የአንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት መተግበሪያ (one-plan one-report platform) መሰረት የተዘጋጀውን ዕቅድ የመገምገምና ሃሳብ አስተያቶችን የመቀበል ስራ ተከናውኗል፡፡ በዚህም መሰረት የ2018 በጀት ዕቅድ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር የተናበበና የፕሮግራም በጀትን መሰረት ያደረገ የመጨረሻ ዕቅድ የማዘጋጀትና የማጠቃለል ስራ ማከናወን ተችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

"ናፍቆት የድሬደዋ ሳምንት መከበር የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን በማጎልበት በኩል ጉልህ ሚና ተጫውቷል".. ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ለአምስት ተከታታይ ቀናት በታላቅ ድምቀት ሲከበር የቆየው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት በበዓሉ የላቀ ተሳትፎ ለነበራቸው ባለድርሻ አካላት ግለሰቦች ና ተቋማት በዛሬው እለት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር በማካሄድ ተጠናቋል። በመርሃ ግብሩም የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ተገኝተው እንደገለጹት ናፍቆት የድሬደዋ ሳምንት መከበር የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን አብሮነቱን በማጎልበት በኩል ጉልህ ሚና ተጫውቷል ብለዋል። ናፍቆት ድሬ አብሮነትን የሚያጠናክሩ የጋራ እሴቶችን ከመገንባት በዘለለ በአስተዳደሩ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ በኩልም አመርቂ ስራ መሠራታቸውን ገልጸዋል። በዚህም የዲያስፖራውን ማህበረሰብ በማስተባበር በጤናው ዘርፍ ለኩላሊት ህሙማን የዲያሌስስ ማሽኖችን ድጋፍ እንዲሁም በትምህርት ቤት የምገባ መርሃ ግብሮች ላይ አመርቂ ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል። ናፍቆት ድሬ በአስተዳደሩ የተጀመረውን የለወጥ ጉዞ ለማስቀጠል ምቹ መደላደል የፈጠረ እና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው በበዓሉ መርሃ ግብር ላይ ጎልህ ድርሻ ለነበራቸው አካላት በሙሉ ከንቲባ ከድር ጁሀር ምስጋና አቅርበዋል። አምባሳደር ፍጹም አረጋ በውጪ ጉዳይ ሚንስትር የዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ኃለፊ እንዳሉት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር በሰጡት አመራር በናፍቆት ድሬ ሳምንት ዘርፈ ብዙ ስራዎች መስራት መቻሉን ገልጸዋል። በቀጣይም በቱሪዝም ዘርፍ የተጀመረውን የማስተዋወቅ ሂደት ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በመርሃ ግብሩም ለባለድርሻ አካላት ተቋማት እና ግለሰቦች የእውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። ©️ DGC

በሳዑዲ አረቢያ ኢ_ሰብዓዊ ድርጊት የተፈጸመባት መካ መሀመድ የሞራል ካሳ ማግኘቷን የሳዑዲ ኢምባሲ አስታወቀ ከ4 ወር በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሪያድ ለሥራ ያቀናችው መካ መሀመድ አረጋው ለሁለት ዓመታት የሚያቆያትን ኮንትራት ተስማምታ ነበር፡፡ በሳዑዲ ለ4 ወራት ከሰራች በኋላ ወደ ቤተሰቧ እንዲመልሷት አሰሪዎቿን ብትጠይቅም አሰሪዎች ግን አሻፈረኝ በማለታቸው ይህ አለመግባባት እየሰፋ በመሄዱ ወደ አልታወቀ ስፍራ ሊወስዷት እየጎተቱ ሲያንገላቷት መካ መሀመድ የድረሱልኝ ጩሀት ታሰማለች፡፡ በዚህም ሁለት ሴቶች እየጎተቷት ወደ መኪና ለማስገባት ትግል ሲያደርጉ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ በርካቶችን አስቆጥቷል፡፡ ጉዳዮን የተመለከተው በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሰዎቹን እና የመኪናውን ታርጋ የያዘ ምስል በማዘጋጀት፣ የክስ ማመልከቻ አዘጋጅቶ ለሳዑዲ አረቢያ የጸጥታ አካላት ማስገባቱን በኢትዮጵያ ኢምባሲ የቆንስላ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ተማም አሊይ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል፡፡ ኤምባሲው ያቀረበውን ክስ መሰረት አድርጎ የሳዑዲ አረቢያ የጸጥታ አካላት ክትትል በማድረግ ሁለቱን ሴቶች በቁጥጥር ሥር በማዋል ተበዳይ መካ መሀመድን ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ ኢምባሲ ቅጥር ጊቢ እንድትመለስ ማድረግ ችሏል፡፡ በሂደቱም የመካ መሀመድ አሰሪዎች የፈጸሙትን ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በማመናቸው እና በመፅፅታቸው በቤተሰብ ደረጃ በድርድር እንዲያልቅ ለኢምባሲው ተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ መካ መሀመድ ጉዳዩ በሽምግልና እንዲያልቅ ተጠይቃ በመፍቀዷ 20 ሺህ የሳዑዲ ሪያል የሞራል ካሳ እንዲከፈላት በማድረግ እርቅ ማውረድ መቻሉን ኃላፊው አቶ ተማም አሊይ ጎዱ ተናረግረዋል፡፡ መካ መሀመድ አረጋው አሁን ትኬት ተቆርጦላት ወደ አገር ቤት ቤተሰቦቿ ጋር እንድትመለስ እንደሚደረግ ኢምባሲው ገልጿል፡፡ አዲስ የወጣው የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ በሁለቱም ወገኖች መብትና ግዴታቸውን ግልጽ በሆነ መልኩ ስለሚያስቀምጥ የሰራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር ምቹ ዕድል በመፍጠሩ በህጋዊ መንገድ የሄዱ ሰራተኞችን ደኅንነት ለመከታተል አጋዥ ሆኗል ብለዋል፡፡ በእንደዚህ አይነት መንገድ ዜጎች ለሥራ ወደውጭ ሃገር ሲሄዱ የሰራተኛውን ሙሉ አድርሻ ኢምባሲው ጋር ስለሚደርስ ለክትትልና ለአሰራር ምቹ አድርጎታል ማለታቸውን ጠቅሶ የዘገበው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ነው፡፡

ከትላንት ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የሚቃኝ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ሽግግር እያረጉ የሚገኙት ከሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች በዛሬው ዕለትም ቀጥለው በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ምልከታ አድርገዋል። በዚህም በኮሌጁ በመገኘት አጠቃላይ የክህሎት ልማቱ ከስራ ዕድል ፈጠራው ጋር ያለው መስተጋብር ምን እንደሚመስል በቢሮው አመራሮች እንዲሁም በኮሌጁ ዲን ገለጻ ተደርጎላቸዋል። ‎ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሀምሌ 25/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያ በ7ኛ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ በአንድ ጀምበር 714.7 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ከዕቅዷ በላይ አሳክታለች! #GreenLegacy #7
+1
ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያ በ7ኛ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ በአንድ ጀምበር 714.7 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ከዕቅዷ በላይ አሳክታለች! #GreenLegacy #700MillionTrees #PlantForEthiopia #MyTreeMyFuture #አረንጓዴዐሻራ