uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 068
Obunachilar
+424 soatlar
-27 kunlar
+230 kunlar
Postlar arxiv
"የማህበረሰብ አቀፍ ውይይት ለስራ ባህል ግንባታና ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የንቅናቄ ስራዎች ማስጀመሪያ መርሐ ግብር !

የሽሬ ግብርና ቴ/ሙ/ት/ስልጠና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራር አባላትን የያዘ ልዑካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት ካሄደ፡፡ ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ እያሳየ በሚገኘው ከፍተኛ አፈፃፀም ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለትም በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚገኘው የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማችን የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጏል:: ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከተ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ የለውጥ ስራዎችም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረገው ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃ መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ሞዴል ተደርጎ መወሰድ የሚችልበት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ሀሳባቸውን ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡበት ኮሌጅ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

የፋይዳ ዲጂታል ብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ መርሀ-ግብር በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ተካሄደ። ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም እንደ ሀገር የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማስቻልና የዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ እውን ከማድረግ አኳያ ሁሉንም ዜጋ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ በንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል:: በዚህም በዛሬው እለት በኮሌጁ በተዘጋጀው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ መርሃ-ግብር ላይ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች በቦታው በመገኘት ምዝገባቸውን ማከናወንም ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

#ዜና /በአስተዳደሩ የተፈጠሩ የስራ እድሎች ለስራ ባህል ማደግ እና ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት የሚኖረው አበርክቶ ከፍተኛ ነው ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ #DGC ሚያዚያ 30/2017 "የማህበረሰብ አቀፍ ውይይት ለስራ ባህል ግንባታና ምርታማነት" በሚል መሪ ሀሳብ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ ምርታማነት ማረጋገጥ የሚያስችል የንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ በዛሬ እለት አካሂዷል ። በንቅናቄ መድረክም ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ድሬዳዋ ከመስረታዊ ጀምሮ በንግድ እና በኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ የስራ እንቅስቃሴ የነበራት የህዝብም የስራ ባህል ጠንካራ የነበረበት መሆኑን አንስተው አሁንም ወጣቱ መንግስት የሚፈጥራቸው የስራ እድሎች በመጠቀም ራሳቸውን እና ሀገራቸውን መለወጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የአስተዳደሩ መንግስት የማህበረሰብ አቀፍ የምርታማነት ውይይት በትኩረት መተግበር ከተቻለ የሥራ ባህልን በመቀየር እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት በማሳደግ ረገድ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸውም በበኩላቸው መድረኩ በዋናነት ከስራ ባህል ጋር ያሉ ችግሮች (በአመለካከት ልማድ ና አሰራር ) ላይ ያሉ ችግሮች በመቀነስ ከዛሬ ችግር ወይም ደህነት በመላቀቅ ወደ ተሻለ ነገ መሸጋገር የሚያስችል አቅም መፍጠር እንደሆነ ተናግረዋል ። በዚህም የስራ ባህልን ግንባታችን ምን ይመስላል የሚሉትን እና በዋናነት የአካባቢ ጸጋን ለይቶ በመጠቀም ለወጣቶች ምቹ የስራ እድልን ከመፍጠር አንጻር ያሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክር ገልጸዋል። የአካባቢ ልማትና የህብረተሰብ ተሳትፎ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ረሂማ አወል ሲገልጹ በንቅናቄ የሚከወነውን የስራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ወጣቶች ከስራ ማማረጥ አስተሳሰብ ተላቀው መንግስት በሚፈጥርላቸው የስራ እድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ በሁሉም ብሎክ ለሚገኙ ስራ ፈላጊዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው የማድረግ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። በመርሀ ግብሩም የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ኢብራሂም ይሱፍን ጨምሮ ከፍተኛ የአስተዳደሩ አመራሮች የሀይማኖት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ነዋሪዎች ተገኝተዋል ። ©️ DDGC

"አንድነት በክህሎት ቀን" ሶስተኛ ቀኑን በያዘው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ሀገራዊ አንድነት በክህሎት የውድድር አደባባይ ብዝሃ ክህሎቶች በአንድነት ደምቀው በኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት ከሁሉም አካባቢዎች የተወጣጡ ልጆቿ እንደ ቤተሰብ አንድ ሆነው የነገዋን ኢትዮጵያ እያሰቡ በመወዳደር ላይ ይገኛሉ። በዛሬው ዕለትም የድሬዳዋ አስተዳደር ሰልጣኝ የክህሎት ተወዳዳሪዎች ቀጥለው በውድድሩ እየተሳተፉ ሲገኝ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር አስተዳደሩን በመወከል የተማሪዎችን የአቴንዳንስ ስርአትን ዲጂታል በሆነ መንገድ ለማሻሻል ታልሞ የተዘጋጀ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በተወዳዳሪ አሰልጣኝ መምህራን ቀርቧል። መልካም ዕድል ለተወዳዳሪዎቻችን! የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬደዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ፕሮጀክቶች ጋር በ2025 የመጀመሪያ ሩብ አመት የሥራ አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ከፌዴራል በመጡ ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዥንና የጉብኝት መረሃ ግብር ተካሄደ፡፡ በዚህም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ጋር በቅንጅት የተሰሩ ስራዎች ከፌደራል በመጡ አመራሮች በአስተዳደሩ ከሚገኙ የፕሮግራም አስተባባሪዎች እና የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በመሆን አፈጻጸሙን የገመገሙ ሲሆን በተጨባጭ የመስክ ጉብኝት በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት  መመልከት ችለዋል፡፡ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ሲኖሩ በዛሬው ዕለት ከቢሮው ጋር ስራዎቻቸውን በዕቅድ አናብበው እየሰሩ የሚገኙና ስራቸው የተገመገመ የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም፣ ጥላ ፕሮግራም፣ ሳፊ ፕሮግራም፣ መስመር ፕሮግራም እና ሲድ ፕሮግራም ናቸው፡፡ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለፁት በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ የአጋር አካላት ሚና ቀላል የማይባል መሆኑንና በቀጣይም ተቀራርቦ እና በየጊዜው በተመሳሳይ መልኩ ስራዎችን አቅዶ እየገመገሙ መሄድ አስፈላጊ በመሆኑን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና | የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አድራ ፕሮጀክት የ 5000 ዋት ሶላር ፒቪ ኢኒስታሌሽን እና ኮሚሽኒንግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ ። #Dire tv አማርኛ ሚያዚያ 28/2017 በድሬዳዋ አስተዳደር በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በአድራ ኢትዮጵያ በቅንጅት እየተሰራ ያለ የኤሌትሪክ ሀይል የሚሰራ በአይነቱ ለየት ያለ ሶፍት ዌር የተገጠመለትን የኮሌጁን የኤሌክትሪክ ዲፖርትመንት ሙሉ ለሙሉ በሶላር ሀይል ኢንዲጠቀሙ የሚያደርግ ፕሮጀክት ከጀርመን ሀገር በመጡ የሶላር ዘዴዎች የተሰራ 5000 ዋት ሶላር ፒቪ ዝርጋታ በትብብር በመስራት በይፋ የርክክብና የምረቃ መርሀ ግብር ተካሂዷል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸዉ በጸሀይ ሀይል የሚሰራ የሀይል ምንጭን መጠቀም ውስጥ የታዳሽ ሀይልን የመጠቀም አዲስ ልምድና አዲስ አቅምን የፈጠረ መሆኑን ገልጸው በተጨባጭ ያለዉን አስተዳደሩ የሚፈልገዉን ቴክኖሎጂ የሞላ የስራ እድልን መፍጠር ላይ ከዚህ በላይ መስራት ይገባናል ብለዋል ።ድርጅቱ ላደረገው ድጋፍም በቢሯቸውና በአስተዳደሩ ስም አመስግነዋል። የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ዳሬክተር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በበኩላቸው ወጣቶች በታዳሽ ሀይል በሶላር ሀይል መሳቢያ ተከላ ሥራ ሰልጥነዉ ህዝባቸዉና ሀገራቸዉን እንዲያገለግሉ ብሎም የራሳቸውን ህይወት እንዲለዉጡ አላማ ይዞ እየሰራ ያለ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዉ ወጣቶችን የክህሎት ባለቤት በማድረግ ወጣቱ ከስራ ፈጠራ ወደ ሀብት ፈጠራ እንዲገባ የሚያነሳሳ ፕሮጀክት ነዉ ሲሉ ተናግረዋል ። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁ እንደ አስተዳደር ከያዝነዉ ድሬዳዋን የዘመነች ከተማ የማድረግ ግንባታ ላይ ትልቅ ሚና የሚጫወት ፕሮጀክት ነዉ ብለዋል ። አድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክቱ ሲጀመር ለ120 ሰልጣኞች የስራ እድል ለመፍጠር የታሰበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ከ46 በላይ ሰልጣኞችን አሰልጥኖ በማስመረቅ ለሁለተኛ ዙር ምዕራፍ እንዲሁ አሰልጥኖ ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል ። አድራ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ላለፉት አርባ ሁለት አመታት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በተለይ የነብስ አድንና ዜጎችን ህይወት መለወጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሰራ የቆየ አሁንም እየሰራ ያለ ድርጅት ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በአጫጭር ስልጠናዎችና በሶላር ፒቪ ሲስተም መስመር ዝርጋታና ጥገና ተማሪዎችንንና መምህራንን የማሰልጠንና የማብቃት ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ከመድረኩ ተገልጿል። ሰላም ይኄይስ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የውይይት መድረክ አካሄዱ። "የመሃሉ ዘመን!" በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የተወያዩ ሲሆን ውይይቱም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባለፉት ተከታታይ 7 አመታት ለውጡን ለማፅናት በተደረጉ ጥረቶች፣ የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ውስጣዊ፣ ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችና የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም አሁናዊ ሀገራዊ ሁኔታና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሆኗል። በውይይቱም የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት የቢሮው ሰራተኞችና አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጠራ ግንዛቤ መያዛቸው እንደሀገር ሊገጥሙ የሚችሉ ፈተናዎችን በሚገባ ለመቀልበስ እንዲሁም የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን በማድረግ ሂደት የማይዝልና የማይታክት አቅም የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። በመድረኩ "የመሃሉ ዘመን!" በሚል መሪ ቃል ለውይይት መነሻነት የሚሆን ሰነድ በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

Ovozli xabar00:04

4ኛው ሀገር ዓቀፍ ክህሎት ቴክኖሎጂ እና ጥናትና ምርምር ውድድር ዛሬ በዲጂታል ተወዳዳሪነት ቀን የተለያዩ የክህሎት እና የቴክኖሎጂ ውድድሮች በመካሄድ ላይ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደርም በአሰልጣኝ በሰልጣኝ እና በኢንተርፕራይዞች ተወክሎ ኢትዮጵያን አሸናፊ ለማድረግ በመወዳደር ላይ ይገኛሉ። ከሚካሄዱ ውድድሮች ጎን ለጎን የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽኖች እና ባዛር በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ግቢ እየተካሄደ ይገኛል። "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ