Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 083
Obunachilar
+924 soatlar
+207 kunlar
+1530 kunlar
Postlar arxiv
Repost from N/a
የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት የ2016ዓ.ም የፕሮጀክቱን አመታዊ አፈፃፀም ሪፖርት ለኮሌጁ ማኔጅመት አቀረበ::
በዕለቱ በቀረበው ሪፖርት አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ)ፕሮጀክት በአመቱ የተሰሩ ስራዎችንና የተመዘገቡ ውጤቶች በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችም ጭምር በፕሮጀክቱ ሀላፊ አማካኝነት ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል::
የማኔጅመንት አባላቱ በመቀጠል በአመቱ የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕርጀክት በሰልጣኝ ተማሪዎቹ የተሰሩ ፕሮጀክቶችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል::
በመጨረሻም አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በዘንድሮ ዓመት በSolar PV Instalation ያሰለጠናቸውን 48 ሰልጣኝ ተማሪዎቹን ነሃሴ 2/2016 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ መሆኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሐምሌ 28/2016 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲና እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጣና ኃላፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣ የባቡር ምህንድስና እና የICT የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ከድሬዳዋ አስተዳደር ስር ከሚገኙ ተቋም ጋር በርከት ያሉ ስራዎችን በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በመስክ ምልከታው ወቅት የተሳተፉ የፖሊስ አባላት እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል እየታየ ያለው ርብርብ በጣም አስደማሚ ነው በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን ይህንን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ከተማችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ነሀሴ 1/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+8
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP እናየ SIFA ፕሮጀክቶችን በምስራቅ አፍሪካ የፕሮጀክቶች አስተባባሪ ከሆነው ከ IUCA እና ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች አመታዊ የስራ አፈጻጸም ግምገማ አከናወኑ፡፡
ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ እና የSIFA ፕሮጀክቶች እንዲሁም አሁን ያሉበትን ሁኔታና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች በአቶ መሳይ ጥላሁን የEASTRIP ፕሮጀክት M&E አማካኝነት ቀርቧል፡፡
ከ IUCA እና ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ ያለው የልህቀት መአከሉን ግነባታ እንዲሁም ከኮሌጁ ጋር ትስስር ባላቸው ኢንዱስትሪዎች ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን
ከሪፖርቶና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም እጅግ እንዳስደመማቸው እና ለፕሮጀክቱ መሳካት እየተሰሩ ያሉ ድጋፎችን አድንቀዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ነሀሴ 1/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የኮሌጁ ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር አካሄደ፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት በስራ ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለጹት ኮሌጁ ባለፉት አመታት ያስመዘገባቸው ስኬቶች በሙሉ እንደ ሃገር ልምድ የሚቀሰምባቸውን ትልልቅ ተግባራትን ያከናወነና በነዚህም ተግባራት ደግሞ በሃገር ደረጃ ስኬትን ማምጣት የቻለ አንጋፋ ኮሌጅ ነው፡፡በኮሌጁ የተገኙ ስኬቶች ደግሞ የአመራሩ ብቻ ሳይሆን የሁሉም የኮሌጁ ሰራተኞች ድርሻ ትልቁን ቦታ የሚወስድ ነው ብለዋል፡፡ በመጨረሻም በቀጣይ የEASTRIP እና SIFA ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደስራ ሲገባ ደግሞ አሁን ከተገኘው ስኬት በላይ የላቀ ስኬቶች ይገኛሉ ለዚህ ደግሞ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊዘጋጁ ይገባል ብለዋል፡፡
ኮሌጃችን በ2016 በጀት አመት ያስመዘገባቸው ስኬቶች በሙሉ የጥቂቶች ብቻ ሳይሆን የሁሉም ባለድርሻ አካላቶች ነው ለነዚህ ባለድርሻ አካለቶች ደግሞ ምስጋናና እውቅና መስጠት ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ናቸው፡፡ አቶ ሳሊም በማስቀጠልም በ2016 በጀት አመት የተመዘገቡ ስኬቶች በ2017 ተጠናክረው መቀጠልና እንደ ሃገር ለሚገኙ ስኬቶች የሚጠበቅብንን ድርሻ መወጣት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ለዚህ መርሃ ግብር መሳካት ትልቁን ድርሻ ለወሰዱት ለኮሌጁ ማኔጅመንት፣ለኮሌጁ ሰራተኞች፣ባለድርሻ አካልት፣ የEASTRIP ፕሮጀክት አባላት እንዲሁም ለኮሚቴ አባላት በኮሌጁ ሰራተኞች ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡
በእለቱ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ እና የንግድ ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት አይናለም ተዘራ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ እና የንግድ ኢንዱስትሪ ጉዳዮች አማካሪ ክቡር አቶ ሽመልስ፣በስራ ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፣የኮሌጁ ማኔጅመንትና እና ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካለት ተገኝተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር አንፃር በቀጣይ በጀት አመት በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለፀ
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የ 2016 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም እና የ 2017 በጀት አመት እቅድ ዙሪያ የቢሮው አመራሮች እና በየደረጃው ያሉ ሰራተኞች ተሳታፊ የሆኑበት የውይይት እና የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አካሂዷል ።
በያዝነው በጀት አመት ከስራ እድል ፈጠራ አንፃር በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረው በተለይም የስራ እድል ፈጠራዎቹ የዜጎችን ህይወት ከመቀየራቸውም በላይ ለሀገራችን ኢኮኖሚ እድገት አይነተኛ አስተዋፆ እንዳላቸውም ነው አቶ ሮቤል ያስታወቁት ።
በገጠር የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በስራ እድል ፈጠራ ተጠቃሚ ከማድረግ ጋር ተያይዞ በቀጣይ በስፋት ከመሰራቱም በላይ ፋሚሊ ቢዝነስ ላይም በርካታ ስራዎችን ለመስራት መታቀዱን የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑት ወ\ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረው በተለይም ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የአርሶ እና አርብቶ አደሩን ኑሮ በቴክኖሎጂ የማሻሻል ስራዎች እንደሚሰራም ነው ወ\ሮ ፈጡም ያስታወቁት ።
በእለቱም በበጀት አመቱ የተሰሩ እንዲሁም ደግሞ በ 2017 በጀት አመት ለመስራት የታቀዱ ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይትም ተደርጓል ።
©️ የድሬዳዋ መንግስት ኮምኒኬሽን
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆች ጋር በ2016 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ የ2017 በጀት አመት ዕቅድን የማናበብ ስራ ተሰራ።
ይህ የዕቅድ ማናበብ በኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ፤ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር እና የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬቶች ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር የዘርፉን ተልዕኮ በቅንጅትና በመናበብ ለማሳካት የሚያስችል ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ዙሮች የሚሰጠው መሠረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመሰጠት ላይ ይገኛል፤
በአስተዳደሩ ቀላል የማይባሉ እድሜያቸው ከ18-25 የሆኑ ወጣቶችን ከስራ ጋር እያስተሳሰረ ሁለተኛ አመት በትግበራ ላይ የሚገኘው "ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ወጣቶች በህይወት ክህሎት እንዲበቁ በማድረግ የተግባቦት አቅማቸውን በማሳደግ ቴክኒካል ክህሎቶችንና የሥራ ባህልን በተግባር እንዲያዳብሩ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል።
በተለይ የሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ሚና በዚህ እረገድ ወሳኝ ሆኖ የሚታይ ሲሆን ሰሞኑን በተከታታይ የሚሰጠውም መሠረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ስልጠና ማሳያ መሆኑን በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ የገለጹ ሲሆን አክለውም ብቃት የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለአምስት ዓመት የሚተገበር መሆኑና ከ70 ሺ በላይ ወጣቶችን ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውሰው እንደ አስተዳደር በመጀመሪያው ዓመት የፕሮግራሙ አፈጻጸም በተሰራው ስራ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተገኙ ውጤቶችን አስጠብቆና አስፍቶ በመስራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ለወጣቶች መሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና መስጠት ተጀመረ፤
እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በ2016 ዓ.ም እየተተገበረ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የ10 ቀን የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድ በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ለሚገኙ ወጣቶች መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
ይህንንም ስልጠና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እየተከታተሉ የሚገኙ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም እያዳበሩ እንደሚገኙ የተናገሩ ሲሆን መሠረታዊ የኮምፒውተር ስልጠናው በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በተመሳሳይ ከነገ ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኑነት
ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
