uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 084
Obunachilar
+524 soatlar
+107 kunlar
+530 kunlar
Postlar arxiv
ድሬ የሥራና ክህሎት ሀገርህን ዕወቅ ክበብ የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጀ፤ ክበቡ ከተመሠረተ ሶስተኛ አመቱ ላይ የሚገኝ ሲሆን ባለፉት ተከታታይ አመታት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በጋራ በመሆን ከመደበኛ ስራ ጎን ለጎን ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ዕድል የፈጠረ ሆኗል። በዛሬው ዕለትም ክበቡ እንዲመሰረትና ተጠናክሮ የተቋቋመበትን አላማ እንዲያሳካ በቡዙ ያገዙትንና የደገፉትን የቢሮው እና የኮሌጅ አመራሮችን አመስግነዋል። በቀጣይም ካለፉት ጊዜያት በተሻለ የሰራተኛውን መቀራረብና ለተሻለ የተልዕኮ አፈጻጸም መነቃቃትን በሚፈጥር መልኩ እንዲንቀሳቀሱ የክበቡን አባላት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አበረታተዋል። የሥራና ክህሎት ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ድሬ የሥራና ክህሎት ሀገርህን ዕወቅ ክበብ የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጀ፤ ክበቡ ከተመሠረተ ሶስተኛ አመቱ ላይ የሚገኝ ሲሆን ባለፉት ተከታታይ አመታት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በጋራ በመሆን ከመደበኛ ስራ ጎን ለጎን ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ዕድል የፈጠረ ሆኗል። በዛሬው ዕለትም ክበቡ እንዲመሰረትና ተጠናክሮ የተቋቋመበትን አላማ እንዲያሳካ በቡዙ ያገዙትንና የደገፉትን የቢሮው እና የኮሌጅ አመራሮችን በማመስገን በቀጣይ ካለፉት ጊዜያት በተሻለ የሰራተኛውን መቀራረብና ለተሻለ የተልዕኮ አፈጻጸም መነቃቃትን በሚፈጥር መልኩ የክበቡን አባላት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አበረታተዋል። የሥራና ክህሎት ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡ በሥራ
+2
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ደ/ር) የመቁረጫ ነጥቡን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጻ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር ተሻለ በመግለጫቸው የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት መግቢያ ነጥብ እንደሚዘጋጅ ገልጸው በዚህ ዓመትም የ12 ክፍል የማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 526,683 የሚሆኑት ከደረጃ 1 እስከ 5 በመደበኛ ስልጠና ለመሰልጠን ተቋማቱን ይቀላቀላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡ ገበያ ተኮር በሆኑ በአጫጭር ስልጠናዎች ደግሞ ከ3 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ዜጎች በተቋማቱ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ሰልጣኞች በተቋማቱ በቂ ክህሎት ታጥቀው እንዲወጡ በክረምቱ የአሰልጣኞች የአቅም ግንበናታ ስልጠና፣ የማሽነሪዎች ጥገና እና አስፈላጊ የማሰልጠኛ ግብዓቶችን የማሟላት ሥራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ በሀገሪቱ የሚገኙ የመንግስት እና የግል ማሰልጠኛ ተቋማት ይህንን የመቁረጫ ነጥብ መነሻ አድርገው ሰልጣኞችን መቀበል ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለተፈጥሮ ሳይንስ የተቀመጡ የመቁረጫ ነጥቦች ዝርዝር ከታች ይመልከቱ ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥቅምት 11፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols

☝️☝️☝️የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ፤

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠኗቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በጋራ በደማቁ  አስመረቁ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር በምረቃ መርኃግብሩ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት ያስተላለፉ ሲሆን ክቡር ከንቲባ በመልዕክታቸው ተመራቂዎች የነገው ህይወታቸውን ለመቀየር መጪው ዘመን ፉክክርና ተወዳዳሪነት የበዛበት በመሆኑ እራሳቸውን በክህሎት፣ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ በቴክኒክና ሙያ አብቅተው በተለይ በድሬዳዋ አስተዳደር የተፈጠሩ ዕድሎችን በመጠቀም ለአገሪቷ መጻኢ ሁለንተናዊ ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት በ2016 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ 447 ሴት 234 ወንድ በአጠቃላይ 681 ሰልጣኞች ተመራቂ መሆናቸውን ገልጸው መጪው ጊዜ በርካታ የሰለጠነ የሰው ሀይል የሚፈልግ በመሆኑ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ተመራቂዎች የሚኖራቸው ሚና የላቀ እንደሚሆንና በተለይ በሥራ ዕድል ፈጠራው አቅጣጫ አቅም እንዲፈጥሩ ቢሮው እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን "ትምህርትና ዕውቀት ፍለጋ መጨረሻ የሌለው በመሆኑ በኮሌጅ ያዳበራችሁትን ጥረትና ትጋታችሁን አጠናክራችሁ ልትቀጥሉ ይገባል" ብለዋል፤ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ካሪኩለም ሰልጥናችሁ የተመረቃችሁ ከፊታቸው ብዙ ዕድሎች እንደሚጠብቋቸው አስታውሰው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ፈቲህያ አደን፣ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ሮቤል ጌታቸው፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ክብርት ፈጡም ሙስጠፋ፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የዘንድሮ ምረቃ ስነስርዓት ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ በዘርፍ አዲሱ ፖሊሲ መሰረት ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የተመረቁበት ሲሆን ከፍተኛ አካዳሚክ ውጤት ያላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሸላሚም ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙት የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠኗቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በጋራ በደማቁ  አስመረቁ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር በምረቃ መርኃግብሩ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት ያስተላለፉ ሲሆን ክቡር ከንቲባ በመልዕክታቸው ተመራቂዎች የነገው ህይወታቸውን ለመቀየር መጪው ዘመን ፉክክርና ተወዳዳሪነት የበዛበት በመሆኑ እራሳቸውን በክህሎት፣ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ በቴክኒክና ሙያ አብቅተው በተለይ በድሬዳዋ አስተዳደር የተፈጠሩ ዕድሎችን በመጠቀም ለአገሪቷ መጻኢ ሁለንተናዊ ብልጽግና የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት በ2016 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ 447 ሴት 234 ወንድ በአጠቃላይ 681 ሰልጣኞች ተመራቂ መሆናቸውን ገልጸው መጪው ጊዜ በርካታ የሰለጠነ የሰው ሀይል የሚፈልግ በመሆኑ ለሀገር ዕድገትና ብልጽግና ተመራቂዎች የሚኖራቸው ሚና የላቀ እንደሚሆንና በተለይ በሥራ ዕድል ፈጠራው አቅጣጫ አቅም እንዲፈጥሩ ቢሮው እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን "ትምህርትና ዕውቀት ፍለጋ መጨረሻ የሌለው በመሆኑ በኮሌጅ ያዳበራችሁትን ጥረትና ትጋታችሁን አጠናክራችሁ ልትቀጥሉ ይገባል" ብለዋል፤ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ካሪኩለም ሰልጥናችሁ የተመረቃችሁ ከፊታቸው ብዙ ዕድሎች እንደሚጠብቋቸው አስታውሰው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ፈቲህያ አደን፣ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፣ የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን፣ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የዘንድሮ ምረቃ ስነስርዓት ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ በዘርፍ አዲሱ ፖሊሲ መሰረት ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች የተመረቁበት ሲሆን ከፍተኛ አካዳሚክ ውጤት ያላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሸላሚም ሆነዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#አሁን_Happening_Now #የሰልጣኝ_ተማሪዎች_ምረቃ
#አሁን_Happening_Now #የሰልጣኝ_ተማሪዎች_ምረቃ

ከ ሆለታ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት አስፈጻሚ ቡድን አባላት እና የኮሌጁ ማኔጅመንት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥና የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ እና
+6
ከ ሆለታ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት አስፈጻሚ ቡድን   አባላት  እና የኮሌጁ ማኔጅመንት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   የልምድ ልውውጥና የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ጉብኝቱ እና በልምድ ልውውጡ   ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት አፈጸጸም  እንዲሁም የልህቀት ማእከሉ የግንባታ ሂደት  እስካሁን የደረሰበት ደረጃ  የቀረበ ሲሆን በልምድ ልውውጡ ወቅት የተሳተፋ  አካላት ለሚያነሱዋቸው የተለያዩ ጥያቄዎች የኮሌጁ የፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ቡድኑ አባላት ለተሳታፊዎቹ ገለጻ ተደርጓል ። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም  ድሬዳዋ

#MesiratEthiopia ድሬዳዋና ሃዋሳ ቢዝነሱን ማሳደግ ለሚፈልግ ⬇️ - በፋይናንስ፣ - በማርኬቲንግ፣ - ችሎታን በማዳበር፣ - በቴክኖሎጂ፣ - በኔትወርኪንግ፣ - የባለሙያ አማካሪዎችን በማግኘት፣ - በፖሊሲ፣ - በአገልግሎት ሰጪነት እና - በአማካሪነት ድጋፍ ለማግኘት https://bit.ly/3BGeH75 ላይ ተመዝገቡ። የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም አባል ይሁኑና ቢዝነስዎ እንዲያድግ አጠቃላይ ድጋፍን ያግኙ። ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ!

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ለምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሪፈራልና ማስተማሪያ ተቋም በሥሩ ለሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በአሰልጣኝነት ለተመደቡ የጤና ባለሙያዎች የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠን ስነ ዘዴ/ TVT Methodology / ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፤ በዚህም ስልጠና ባለሙያዎቹ ውጤትን መሰረት ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር የተደገፈ እንደመሆኑ ስልጠናው በቴ/ሙ/ስ ተቋማት ውስጥ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና የማሰልጠን ሥነ-ዘዴውን በሚገባ ተረድተው በ2017 ዓ.ም ከመላው አገሪቱ የሚመደቡ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን አቅም የሚገነባ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ቢሮው ለምስራቅ ዕዝ መከላከያ ሪፈራልና ማስተማሪያ ተቋም በሥሩ ለሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በአሰልጣኝነት ለተመደቡ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጠው ስልጠና ለ7 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቂያ በሚኖራቸው ምዘና መሰረት ብቁ የሆኑትን ሰርቲፋይ በማድረግ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን የሚሰጡ ዕውቅና ያገኙ አሰልጣኞች ያደርጋቸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

🏆እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM የአሰራር ስርዓቱን ለማሻሻልና እውቅና ለማግኘት ባለፉት
🏆እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM የአሰራር ስርዓቱን ለማሻሻልና እውቅና ለማግኘት ባለፉት ጊዜያት እንደ ተቋም የተለያዩ ስራዎችን  እየሰራ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን ላለፉት 10ቀናት ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በተመደበ የኦዲት ባለሙያ የEXTERNAL OR CERTIFICATION AUDIT ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለትም በተደረገው የCLOSING MEETING ኮሌጃችን የISO 9001 2015 ሰርተፊኬት እውቅና ለማግኘት ብቁ መሆኑንና RECOMMEND መደረጉን በኦዲተሩ በኩል ተረጋግጧል:: ይህ ስኬት በሁሉም የጋራ ጥረትና ድካም የተገኘ በመሆኑ የኮሌጃችን ማህበረሰብ በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አለን::🔥🔥🏆🏆🏆 ©️ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን

🏆እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM የአሰራር ስርዓቱን ለማሻሻልና እውቅና ለማግኘት ባለፉት
🏆እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን🏆 የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በISO 9001 2015 QUALITY MANAGEMENT SYSTEM የአሰራር ስርዓቱን ለማሻሻልና እውቅና ለማግኘት ባለፉት ጊዜያት እንደ ተቋም የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን ላለፉት 10ቀናት ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በተመደበ የኦዲት ባለሙያ የEXTERNAL OR CERTIFICATION AUDIT ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለትም በተደረገው የCLOSING MEETING ኮሌጃችን የISO 9001 2015 ሰርተፊኬት እውቅና ለማግኘት ብቁ መሆኑንና RECOMMEND መደረጉን በኦዲተሩ በኩል ተረጋግጧል:: ይህ ስኬት በሁሉም የጋራ ጥረትና ድካም የተገኘ በመሆኑ የኮሌጃችን ማህበረሰብ በሙሉ በድጋሚ እንኳን ደስ አለን::🔥🔥🏆🏆🏆