cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Amen Gospel Telegram Channel

#ሰዎችን #በክርስቶስ #ለክርስቶስ #ማድረግ #ነው 💥💥💥💥💥💥💥 #WELCOME TO OUR BLESSING CHANNEL 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ለበለጠ መረጃ +251941810160 ደውሉልን To our belssing telegram group https://t.me/+YcqErTQrE6M2NzFk Join as 🙏 https://t.me/helingjesus

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
942
Obunachilar
+224 soatlar
+177 kunlar
+3430 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

እንኳን #አደረሳችሁ!! ከትንሣኤ በኋላ ... እንኳን አደረሳችሁ መባባል ያለብን ስለ በዓል ሳይሆን ስለደረስንበት ዓለም ነው!! ... የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ #ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም #ደርሳችኋል!! ዕብራውያን 12፥²²-²⁴። ከሙታን የተነሳው ኢየሱስ ራሱ #ትንሣኤ ነው!! ከሙታን ወደ ተነሳው ወደ ኢየሱስ #ደርሳችኋል!! እንኳን #አደረሳችሁ!! ትንሣኤ በዓመት አንድ ቀን የሚጠበቅ በዓል ሳይሆን በየዕለቱ የሚያለመልም እና የሚያከብር ሕይወት ነው!! እርሱም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!! ❝ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤❞ ዮሐንስ 11፥25። የትንሣኤን በዓል ሳይሆን ራሱን #ትንሣኤን ማለትም ኢየሱስን እናከብረዋለን!! እርሱን ደግሞ የምናከብረው በበዓል መንፈስ ሳይሆን በውስጣችን ባለው የትንሣኤ መንፈስ ነው!! ከሙታን የተነሳውን እያሰብን እና የትንሣኤውን ኃይል እየተረዳን በመንፈሱ ደስታ እንዋል!! መብላታችን፣ መጠጣታችን እና መልበሳችን እግዚአብሔርን አያስቆጣውም!! ዋናው ነገር የምናደርገውን ሁሉ ለእርሱ ክብር እናድርገው!! ክብር ሁሉ ለክብር አባት ለእግዚአብሔር ይሁን !! #Amen #Gospel
Hammasini ko'rsatish...
አንድ ወዳጅ ከመሞትህ በፊት ልትተዋወቀው የሚገባ አንድ ወዳጅ አለ። ይህ ወዳጅ አንተን መውደድ የጀመረው አንተ ከመወለድህ በፊት ነው። መኖር ሳትጀምር ያወቀህ፥ ሳታውቀው ያኖረህ፥ ሳትጠይቀው የኃጢአትህን ዕዳ የከፈለልህ፥ በነፃ ሕይወትን ሊሰጥህ እየጠበቀህ ያለ አንድ ወዳጅ ኢየሱስ!! ይህን አንድ ወዳጅ ስታውቀው ሰማይ ያውቅሃል። አንድ ኢየሱስን በመቀበል የእግዚአብሔር ስጦታዎችን ሁሉ ማለትም የኃጢአት ይቅርታ፣ ጽድቅ፣ የዘላለም ሕይወት፣ ልጅነት እና ክብር መቀበል ትችላለህ!! ኢየሱስ ይወድሃል!! ✍️messager kaleb
Hammasini ko'rsatish...
ወደ ኋላ የሚመልስ መንገድ የለም!! #ጀልባዎችህን አቃጥል!! የግሪኮች ጥንታዊ የጦር ዘመቻ ... መሪ ቃል "There is no turning back" የሚል ነበር። ወደፊት ለመሄድ ወደኋላ ሊመልሳቸው የሚችለውን ጀልባ ማቃጠል ይኖርባቸዋል። የጦር ሠራዊቱ ባሕር ካቋረጡ በኋላ ... የጦር ጀኔራሉ ... "ጀልባችሁን አቃጥሉ" ብሎ ያዛል። ወታደሮቹም ባሕር ያቋረጡባቸውን ጀልባዎች በገዛ እጃቸው ያቃጥላሉ። አሁን ወደኋላ የሚመልስ መንገድ እንደሌለ ግልፅ ሆነ። ቀጣይ ግባቸው ጦርነቱን ማሸነፍ ወይም መሞት ይሆናል። ይህን ካደረጉት ቄሳሮች ጁልየስ ቄሳር አንዱ ነበር። እኛም እንዲሁ ... የማንነት ለውጥ አድርገናል ማለትም በክርስቶስ በመሆን ከአዳም ታሪክ ተፋትተናል(2ኛ ቆሮ 5፥16-17)፤ መንግሥት ለውጠናል ማለትም ከጨለማው ስልጣን ወደ ሚወደው ልጁ መንግሥት ፈልሰናል(ቆላስ 1፥13-14)፤ በደም የተመረቀ መንገድ ውስጥ ነን፤ መንገዱ ወደኋላ አይመልስም!! ወደ መርከቡ [ወደ #ኢየሱስ] ስትገቡ ያላቃጠላችሁት ጀልባ በውጭ ካላችሁ አቃጥሉት - መርከቡ አስተማማኝ ነው!!! ✍️messager kaleb
Hammasini ko'rsatish...
#እንዳንወሰድ ❝ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት #እንዳንወሰድ፥ ለእርሱ አብልጠን ልንጠነቀቅ ያስፈልገናል።❞ —ዕብራውያን 2፥1። እምነታችን የጀመረው ከሰማነው ሕያው ቃል ነው። (ሮሜ 10፥17) የእምነታችንን ንፅህና መጠበቅ የምንችለው በሰማነው እውነት በመደላደል ነው። የሚጠበቅብን ሌላ መስማት ሳይሆን በሰማነው በክርስቶስ ስር ሰደን መታነጽ ነው። (ቆላስ 2፥7) የዕብራውያን ፀሐፊ ... መጻፍ ሲጀምር ኢየሱስን የመጨረሻው የእግዚአብሔር አንደበት አድርጎ አቅርቦታል። ❝ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤❞ (ዕብራውያን 1፥2) እግዚአብሔር የተናገረን በልጁ ነው፤ እኛም የሰማነው ልጁን ነው። ፀሐፊው የጀመረውን አሳብ ሲጠቀልል ❝ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት #እንዳንወሰድ ...❞ ብሏል። ይህ ማለት ከኢየሱስ እንዳንወሰድ እንጠንቀቅ። አሁን የኛ ሕይወት ልጁ በነገረን ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ከእርሱ ውጭ ላለመስማት መቁረጥ ይኖርብናል። ቅዱሳን ... የዕብራውያን ፀሐፊ ጭብጥ ወደ ፍጻሜ እንሂድ የሚል ነው። ምክንያቱም ከሁሉ የሚልቀው ኢየሱስ ስላለን እና የቀረን ወይም የጎደለን ስለሌለ ነው። #እንዳንወሰድ ... ማለት ትኩረታችን በሌላ ነገር ላይ እንዳይሆን፣ ዓይናችን ከኢየሱስ እንዳይነሳ፣ ሌላ ነገር ቀልባችንን እንዳይወስደው፣ ልባችን በሌላ ነገር እንዳይያዝ፣ ራሳችንን የሌላ ሆነን እንዳናገኘው፣ ተታለን ወይም ስተን እንዳንወድቅ ... አብልጠን እንጠንቀቅ!! ✍️messager kaleb
Hammasini ko'rsatish...
#ከአማኝ #ህይወት #መፅሐፍ #የተወሰደ ❤ ኢየሱስን ትታችሁ የምትሄዱት መንገድ አይኑር፤ እርሱ የሌለበት ነገር ሕይወት ኖሮት አያውቅም!! ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ... ''ኢየሱስን ወደጎን አድርጎ" የራስን ኑሮ ማደላደል ስለቀለላቸው ሰዎች እየሰማሁ ነው። ባለቀው ዓመት ብቻ ሦስት እህቶች በትዳር ምክንያት ወደ ሌላ ሃይማኖት መመለሳቸውን አስታውሳለሁ። በጊዜው የመጣልኝ አሳብ ''ኢየሱስን ትታችሁ የምትሄዱት መንገድ አይኑር፤ እርሱ የሌለበት ነገር ሕይወት ኖሮት አያውቅም" የሚል ነበር። ወገኖች ኢየሱስ ለእኛ ሲል ራሱን ትቷል፤ ራሱን ባዶ አድርጓል። ከእርሱ የሚቀድም ምንም ነገር የለም። ለጊዜው የነገሮች መቃናት ስሜት ይሰጥ ይሆናል፤ ዘግይቶ ግን የሚገባን ''ተራ ምርጫ" እንደ መረጥን ነው። በመጨረሻ ግልፅ ሊሆንልን የሚገባው ... ❝ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።❞ የሚለው ቃል የታመነ እንደሆነ ነው። —2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥13። ማለት እኛ ስለካድነው ... እርሱ ታማኝ መሆኑ አይቀርም! እኛ በእርሱ ላይ ያለን አቋም ቢለዋወጥ እርሱ ለእኛ ያለውን ልብ አይለወጥም!!                      ✍️messager kaleb
Hammasini ko'rsatish...
ማህበራዊ ሚዲያ እጠቃቀማችን መልካም ነው? አብዛኛው ወጣት በዚህ ጊዜ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ነው... ለዚህ ደግሞ ፌስቡክን እና ቴሌግራም መጥቀስ ይቻላል። ነገር ግን እነኚ ነገሮች ምን ያህል ጠቅመውን ይሆን? ምንያህልስ በህይወታችን ላይ መልካም የሚባሉ ተፅዕኖዎችን አሳርፈውብናል? 🕳️ማህበራዊ ሚዲያ እንደ አጠቃቀሙ ይወሰናል፤ ለምሳሌ ያህል በመልካም ከተጠቀምነው መልካም ጉን ይኖረዋል፤በዛው መጠን ደግሞ እኛን የማይጠቅሙ በነገው ህይወታችን ላይ መጥፎ ጠባሳ የሚያደርሱ ነገሮችን ከተጠቀምንበት መልካሙን የህይወት መንገዳችንን አቅጣጫ ሊያስቀይረን ይችላል። ብዙ ወጣቶች አብዛኛውን ጊዜያቸውን ለነገው ህይወታቸው በማይጠቅማቸው እና በማያስፈልጋቸው ነገር ላይ ያጠፍሉ፤ ከዚህ ውስጥም አብዛኛውን ድርሻ የሚወስደው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ነው፤ ስለዚህም ውድ የአባቴ ብሩካን የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማችንን አግባብ ባለው ሁኔታ እና እግዚአብሔር በማያሳዝን መንገድ ብንጠቀም መልካም ነው ብዬ አስባለው። #እወዳቹዋለው #ጌታ_ዘመናቹን_ይባርክ ✍️messager kaleb
Hammasini ko'rsatish...