Bulbula GSS Since 2000 E.C student
Kanalga Telegram’da o‘tish
ውድ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ በዚህ ቻናል የሚለቀቁት ጉዳዪች በዋናነት ትምህርትቤቱ ለተማሪዎቹ የሚያስተላልፈው ማስታወቂዎች፤ትኩስና ወቅታዊ ትምህርታዊ መረጃዎች እንዲሁም በክፍል ደረጃችሁ ለምትማሩት ትምህርት አጋዥ በሚሆናችሁ ትምህርት መሆኑን እንገልፃለን።
Ko'proq ko'rsatish1 673
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-37 kunlar
-3230 kunlar
Postlar arxiv
https://t.me/DailyCashsbot/win?startapp=17585671784954
💥 እኔ 65,000 ብር አሸንፌ ነኝ!
Ani Birr 65,000 mo’ee jira!
🎁 በየቀኑ እስከ 70,000 ብር ያሸንፉ!
Guyyaa guyyaatti hanga Birr 70,000 mo’aa!
💵 አሁን ይመዝገቡ፣ ወዲያውኑ 2,800 ብር ያግኙ!
Amma galmaa’aa, si’a tokkotti Birr 2,800 argadhu!
💰 ጠቅ በሉ → አሁኑኑ ጀምሩ!
Cuqaasi → Ammas jalqabi!
#MoE
በ2018 ዓ.ም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ እንዲደረግላችሁ የምትፈልጉ ተመሳሳይ ጾታ መንትዮች፣ የምታጠቡ እናቶች እንዲሁም የተለያዩ የጤና እክል ያለባችሁ ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት እስኪገለፅ ድረስ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡
የሚያስፈልጉ ሰነዶች፦
1. ለተመሳሳይ ጾታ መንትያ አመልካቾች
➫ የሁለቱም አመልካቾች የልደት ካርድ
➫ ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
2. የሚያጠቡ እናት አመልካቾች
➫ ስድስት (6) ወር ያልሞላው የህጻኑ/የህጻኗ የክትባት ካርድ
➫ ከተማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
3. የተለያዩ የጤና እክል ያለባችሁ አመልካቾች
➫ ከመንግሥት ሆስፒታሎች የቦርድ ወሳኔ የተሰጠበት የህክምና የምስክር ወረቀት
➫ ከሚማሩበት ትምህርት ቤት የድጋፍ ደብዳቤ
@tikvahuniversity
ቀን 04/12/2017 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለ10ኛ-12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ
በትምህርት ቤታችን በ2018 ዓ.ም ከ10ኛ-12ኛ ለምትማሩት ተማሪዎች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል ።ነገር ግን እስካሁን ትምህርታችሁን ያልጀመራችሁ ተማሪዎች ከነገ 05/12/2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 ጀምራችሁ ትምህርት ገበታችሁ ላይ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን ።
ት/ቤቱ
ውድ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች እንደምን ቆያችሁ?ሁሉ ሰላም ነው?መልካም! በመደበኛ ትምህርታችሁ ጎን ለጎን እዚህ ፔጅ ላይ የተለጠፈውን ሊንክ በመጠቀም የኢትዮ ኮደርስ ኦንላይን ስልጠና በነፃ በመውሰድ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችላችሁ ሰርትፍኬት እንድታገኙ እያሳወቅን ስልጠናውን የጀመራችሁ ተማሪዎች ሰኞ በ25/09/2017 ዓ.ም ቢሮ ቁጥር 11 በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉልን እናሳስባለን ።https://ethiocoders.et/
ዛሬ ማለትም 02/09/2017ዓ.ም በቡልቡላ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2ኛ ሴሚስተር የማጠናከሪያ ትምህርት የመጨረሻ ወይም የ8ኛ ሳምንት በጥሩ ሁኔታ ተጠናቅቋል::
============================
Guyyaa har'aa jechuun 02/09/2017 Mana Barumsaa Waliigalaa Sadarkaa Lammaffaa Bulbulaatti barnootni dabalataa kan saamisteera 2ffaa kan sagantaa xumuraa barnoota addaa yookaan torbee 8ffaa haala gaariin xumurameera.
============================
The 2nd semester of the final program or schedule for Supplementary (Tutorial) class at Bulbula General Secondary School has been successfully completed today (02/09/2017E.C).
የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት መርሃ ግብር ተገለጸ፡፡
ፈተናው ከሰኔ 23/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም የሚሰጥ ሲሆን በወረቀት የሚፈተኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 21 እና 22/2017 ዓ/ም እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 29 እና 30/2017 ዓ/ም ወደሚፈተኑበት ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ይሆናል፡፡ በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተፈታኞች ከመኖሪያ ቤታቸው በየቀኑ እየተመላለሱ በተመደቡበት መፈተኛ ማዕከል የሚፈተኑ ሲሆን ዝርዝር መርሃ ግብሩ በሚከተለው ሠንጠረዥ ተገልጿል፡፡
የፈተናው ይዘት በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያተኮረ በመሆኑ እያንዳንዱ ተፈታኝ በትምህርት ቤቱ የተማረበትን የተማሪ መጽሐፍ መሠረት አድርጎ ተገቢ የሆኑ አጋዥ መጽሐፍትን ለበለጠ እውቀትና መረዳት በመጠቀም እንዲዘጋጅ እናበረታታለን፡፡ በፈተና ወቅት ለፈተና ስርቆትና ኩረጃ የሚውሉ ማንኛውንም ቁሳቁሶች መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ዝርዝሩ በቀጣይ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ግንቦት 01/2017 ዓ/ም
የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈታና ተፈታኝ ተማሪዎች ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ለፈተና በቂ ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችሉ ትምህርቶችን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
https://examinfo.moe.gov.et/guides
(ሚያዝያ 29/2017 ዓ.ም)
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
