cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Bulbula GSS Since 2000 E.C student

ውድ የትምህርት ቤታችን ተማሪዎች እንዲሁም የትምህርት ማህበረሰብ በዚህ ቻናል የሚለቀቁት ጉዳዪች በዋናነት ትምህርትቤቱ ለተማሪዎቹ የሚያስተላልፈው ማስታወቂዎች፤ትኩስናወቅታዊ ትምህርታዊ መረጃዎች እንዲሁም በክፍል ደረጃችሁ ለምትማሩት ትምህርት አጋዥ በሚሆናችሁ ትምህርት መሆኑን እንገልፃለን።

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
2 303
Obunachilar
-724 soatlar
-787 kunlar
+15930 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተማሪዎች እንዲዘጋጁ የትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ። (ቀን ሚያዚያ 23/ 2016 ዓ.ም) የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ በጉዳዩ ዙሪያ በተዘጋጀ የአሰልጣኞች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በኦላይን ለመስጠት ከሁሉም ክልሎች በተመረጡ 25 ከተሞች ዝግጅት እየተደረገ ነው። በወረቀት ከሚሰጠው አገር አቀፍ ፈተና ጎን ለጎን በቴክኖሎጁ ተደግፎ የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር እያደሩ ፈተናውን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸው ሚኒስትር ዴኤታዋ ተናግረዋል። በመሆኑም ፈተናው እንዲሰጥባቸው በተመረጡ ከተሞች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱ የዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከወዲሁ እንዲዘጋጁ ወ/ሮ አየለች አሳስበዋል። በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላትም ከወዲሁ በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ጠቁመዋል። ወላጆች ስለፈተናው የተሻለ አረዳድና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ልጆቻቸውን እንዲደግፉና በራስ መተማመን ወደ ፈተናው ሊገቡ የሚችሉበትን ዕድል ሊፈጥሩ እንደሚገባም አመላክተዋል። ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮም በኦን ላይን የሚሰጠውን ፈተና በተሻለ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው ፈተናን ለተማሪዎች በኦንላይን መስጠት ምቹና ቀላል መሆኑን ጠቅሰው የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል። (መረጃው የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ነው) በዚሁ መሠረት በአዲስ አበባ ያሉ ሁሉም በግልና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ያሉ የ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የሚፈተኑት በኦንላይን መሆኑን እየገለጽን የቡልቡላ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎቻችን አስፈላጊውን ዝግጅታችሁን እንድታዳብሩ እናሳስባለን። የፈተናውን ቴክኒካል ሂደትና የኦንላይን አሰጣጥ መረጃዎች በተመለከተ በቀጣይ መረጃ እንዲኖራችሁ የምናደርግ መሆኑንም እናሳውቃለን።
Hammasini ko'rsatish...
ሚያዝያ 23/08/2016 ዓ.ም ዛሬ በቀን 23/08/2016ዓ.ም በወንዶች መምህራን የእግር ኳስ ጨዋታ ቡልቡላ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 6 ለ0 በሆነ ውጤት አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤትን አሸንፏል:: Waldorgommii kubbaa miillaa barsiisotaa kan dhiiraan har'a gaggeeffameen Manni Barumsaa Waliigalaa Sadarkaa 2ffaa Bulbulaa 6fi 0'n Mana Barumsaa Abuune Goorgiriyoosiin guyyaa har'aa mo'ateera!!!
Hammasini ko'rsatish...
Our be loved students, congratulations to see your efforts!!! Keep it up!!!
Hammasini ko'rsatish...