uz
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

Yopiq kanal

Ko'proq ko'rsatish
1 148
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-27 kunlar
-1930 kunlar
Postlar arxiv
photo content

ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ታላቅ የዉይይት መድረክ ከአሠልልጣኞች ጋር ተካሄደ ። "የበቁ አሰልጣኞች ፣ ክህሎት የጨበጠ ወጣት ፤ ለሀገር ብልጽግና"  በሚል መሪ ቃል በሀገራዊ ለውጥና ስኬቶች፣ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ጉዳዮች፣ የከተማችን ያለፉት ዓመታት የልማት እና ተያያዥ ጉዳዮች እንደዚሁም የቴክኒክና ሙያ  ስኬቶች፣ ተግዳሮቶች እና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች የሚዳስስ ጉባኤ ተካሄደ ። በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ በተካሄደዉ በዚህ ዓብይ ጉባኤ ኢትዮጵያ በተለይም ከተማችን አዲስ አበባ ከሪፎርሙ በኋላ  በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ያስመዘገበቻቸዉ ለዉጦች ተዳሰዋል ። አዲስ አበባ ዉስጥ ለሚገኙ ሁሉም የቴ/ሙ ተቋማት እና ኮሌጆች በzoom Meeting ቴክኖሎጅ በመታገዝ የመወያያ ሃሳቦች ያቀረቡት የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ የተከበሩ አቶ ጥራቱ በየነ እንዳሉት ከሃገራዊ ሪፎርሙ በኋላ በትምህርት ፣ በጤና ፣ በከተማ ግብርና ፣ በቴክኖሎጅ ፣ በቱሪዝም ፣  በመሰረተ ልማት ግንባታ ፣ በዲፕሎማሲ እና ሌሎችም ዘርፎች ከፍተኛ እምርታ መታየቱን  ገልጸዋል። የከተማችን የወንዝ ዳር እና የኮሪደር ልማት እንደዚሁም  ከተማችን ላይ እየተሰሩ ያሉ የተለያዪ ሜጋ  ፕሮጀክቶች በተሳካ ሁኔታ እየተከናወኑ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።  በነዚህ ፕሮጀክቶች ላይ  የቴ/ሙያ ተቋማት ፣ አሰልጣኞች እና  ሰልጣኞች በጉልህ የተሳተፉበት እንደሆነም ተናግረዋል። አያይዘዉም ከቴ/ሙያ ተቋማዊ ሪፎርም  አንጻር በቴ/ሙያ ተቋማት የስልጠና ዘርፎቹ ማስፋት  እና የአሰለጣጠን ሂደቱ መሻሻል ፣ ለኢንዱስትሪው እና ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ የቴ/ሙያ ማሕበረሰብ ተኮር ስራዎች ፣ በሰዉ ሀይል አቅም ግንባታ የተሰሩ መልካም ስራዎች  ፣ የቴ/ሙያ ተቋማት ከባቢያቸዉን ውብ ፣ ማራኪና ለስራ ምቹ በማድረግ በኩል  ለቴ/ሙያ ሁለንተናዊ ዕድገት አስተዋጽኦዉ  ከፍተኛ ነዉ ያሉ ሲሆን  በ2017 ዓ.ም በፌደራል ደረጃ በተከናወነ የክህሎት  ዉድድር አዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ አንደኛ ደረጃ  በመዉጣት ማጠናቀቁ እንደ ስኬት የሚነሳ መሆኑን ተናግረዋል። በውስንነት የተነሱት ደግሞ  የአሠልጣኞች የምዘና  ውጤት አናሳ መሆን  ፣ አሰልጣኞች በሙሉ ሰዓታቸዉ በስልጠና ገበታቸዉ ላይ አለመገኘት፣ የአመለካከት እና ቁርጠኝነት ክፍተቶች እንዳሉ ተነስተዋል። በዉይይቱ በአሰልጣኞቹ ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል   ከቤት ባለቤትነት  ፣ ከደመወዝ ጭማሪ፣ የመምህራን የመድህን አገልግሎት ሽፋን፣ ጥቅማጥቅምና ድጎማ ፣  የመምህራን የማበረታቻ ፕሮግራሞች እንደዚሁም ፣  የአመራሩ ቶሎ ቶሎ መቀያየር ተረጋግቶ ከመስራት እና ውጤት ከማስመዝገብ አንጻር የነበሩ ችግሮችን ጨምሮ ውይይት ተደርጎባቸዋል ። ለተነሱ ሃሳብ አስተያየቶች  አወያዮቹ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ዋ/ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ እና የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ም /ሃላፊ አቶ ሀፍታይ መልስ የሰጡባቸዉ ሲሆን አንኳር ጉዳዮችን ለከፍተኛ አመራሮች ለማቅረብ ሃላፊነት ተቀብለዉ ወስደዋል። በመጨረሻም የቴ/ሙያ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቹ   ምዘና ፣ ጥራት ያለዉ ስልጠና ፣ ቴክኖሎጅ እና ምርምር ፣ አለምአቀፉን የትምህርት ጥራት ደረጃ በISO 21001:2018 Educational quality management system"  ማረጋገጥ፣ ለሃገራዊ ለዉጥ የተጋ ዜጋን መፍጠር ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል። በቀጣይ  ክብርት ከንቲባዋ ቀጥሎም ጠ/ሚ በሚመሩት መድረክ ላይ ኮሌጁን ወክለው የሚሳተፉ  አሰልጣኞች ተመርጠዋል። በውይይቱ 251 ወንድ እና 71 ሴት በድምሩ 322 አሠልጣኞች ተሳትፈዋል፡፡           የኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

ሃገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች  አመራሮችና አሰልጣኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃገራዊ ለውጡን ተከተሎ በተመዘገቡ ለውጦችና ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አመራሮችና አሰልጣኞች ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል፡፡ "የበቃ አሰልጣኝ፣ክህሎት የጨበጠ ወጣት፣ለሀገር ብልፅግና!" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው ውይይት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ  ከማዕከል  ገለፃ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በውይይቱ  ለቢሮው ተጠሪ በሆኑ 15 ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት እና አንድ የልህቀት ማዕከል ላይ የሚገኙ  ከ2ሺ919 በላይ አሰልጣኞች ከማዕል በመተላለፍ ላይ  የሚገኘውን ገለፃ በመከታተል ላይ ይገኛሉ።

photo content

ግንቦት 10/2017 የአሰልጣኞች የውይይት መድረክ ዝግጅት በከፊል
+3
ግንቦት 10/2017 የአሰልጣኞች የውይይት መድረክ ዝግጅት በከፊል

photo content

photo content

ግንቦት 6/2017ዓ.ም የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ በትላንትናው ዕለት ተጀምሮ ዛሬ ተጠናቋል። በፊኒሺንግ የሙያ የሰለጠኑ 7 ሰልጣኞች ከደረጃ
+4
ግንቦት 6/2017ዓ.ም የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። የኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ  በትላንትናው ዕለት ተጀምሮ ዛሬ ተጠናቋል። በፊኒሺንግ የሙያ የሰለጠኑ 7 ሰልጣኞች ከደረጃ 2 ወደ ደረጃ 3 እና በተመሳሳይ በፊኒሺንግ የሙያ ዘርፍ 2 ሴት እና  15 ወንድ በድምር 17 ሠልጣኞች ከደረጃ 1 ወደ  ደረጃ 2 ለመሸጋገር ለምዘና ተቀምጠዋል። ምዘናው በትምህርት ክፍሉ ተዘጋጅቶ በስልጠና ዘርፉ ተገምግሞና ጸድቆ የተሠጠ ሲሆን ለምዘና የተቀመጡ 24 ሠልጣኞች ምዘናውን በብቃ አጠናቀዋል /100% በምዘናው ብቁ ሆነው ወደሚቀጥለው ደረጃ መሸጋገራቸውን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዋ ብርቱሰው ከበደ መረጃውን አጋርተውናል።                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ግንቦት/2017ዓ.ም በክህሎት ዉድድር ያሸነፈዉ  የኮሌጃችን ሰልጣኝ ዳዊት ፋንታሁን ማነዉ ? ዳዊት ፋንታሁን ይባላላል። የ21አመት ወጣት ነዉ። ተወልዶ ያደገዉ አዲስ አበባ ነዉ። የመዋእለ ህጻናት እና የመጀመሪያ  ደረጃ ትምህርቱን በቅዱስ ማርቆስ ት/ቤት ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዛማች በላይ ዘለቀ እንዲሁም የመሠናድኦ ትምህርቱን በዳግማዊ ምኒሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትሏል።  በአሁኑ ሰዓት በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ( Hardware and Networking Service) ት/ክፍል  የ3ኛ አመት ሰልጣኝ  ሲሆን በያዝነዉ ዓመት ስልጠናዉን አጠናቆ ይመረቃል። ተማሪ  ዳዊት ፋንታሁን በ2017 ዓ.ም  ''ብሩህ አዕምሮዎች ፣ በክህሎት የበቁ ዜጐች '' በሚል መሪ ቃል  የስራና ክህሎት ሚኒስተር በአዲስ አበባ ባዘጋጀዉ አራተኛዉ አገር-አቀፍ የተግባራዊ ምርምር ፣ የቴክኖሎጅ እና የክህሎት ዉድድር በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ፣ በሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ( Hardware and Networking Service) ት/ክፍል በተደረገ የክህሎት ዉድድር  3ኛ በመዉጣት የነሀስ ሜዳሊያ ፣ ሶስት መቶ ሺህ ብር (300,000.00 ) እና የምስክር ወረቀት በመሸለም  የተፈሪመኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅን በአገርአቀፍ ደረጃ ማስጠራት የቻለ ባለተሰጥኦ ወጣት ነዉ። ከልጅነቱ ጀምሮ ለኮምፒዩተር ልዩ ፍቅር እንዳለዉ እና በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች ላይ  ተሰጥኦ እንዳለዉ የሚናገረዉ  ዳዊት ፋንታሁን በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ  ትምህርቱ ከፍተኛ ዉጤት የሚያመጣዉ በአይሲቲ (Information Commynication Technology )የትምህርት አይነት እንደሆነ ያስታዉሳል።  ጊዜዉ 2015  ዓ.ም ነበር።ወደ ዩኒቨርስቲ ለመግባት ዉጤት አለማምጣቱ ዳዊትን የሚወደዉን የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት ለመሰልጠን በሩን ከፈተለት። በቀድሞ የኮሌጁ ተማሪዎች ጥቆማ በዝና ወደሚያዉቀዉ  ተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮ ለመምጣት አላቅማማም  በአይሲቲ ት/ዘርፍ ከሚሰጡ ስልጠናዎች መካከል በሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ት/ክፍልን በመምረጥ ተመዘገበ ። የተፈሪ መኮንን የአይሲቲ ት/ዘርፍ የተደራጀ የኮምፒዉተር ማስተማሪያ ክፍል ፣ በቂ ልምድ እና እዉቀት ያላቸዉ አሰልጣኞች መኖራቸዉ የበለጠ የስልጠና ጉጉቱን ጨመረለት።  እንደርሱ ተመሳሳይ ፍላጎት ካላቸዉ ታዳጊ ወጣቶች ጋር ስልጠናዉ ተጀመረ። የእወቀትና ክህሎት አድማሱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና አየሰፋ መጣ።  የኮሌጅን ህይወት እንደጠበቅኩት ነዉ ያገኘሁት ይላል ተማሪ ዳዊት '' የኮሌጅ ህይወት በጥሩ መልኩ ካየነዉ ተጨማሪ እዉቀት እና ክህሎት የሚያስጨብጥ ፣ ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያጠናከር ፣ አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር እድል የሚሰጥ መሆኑን የሚያወሳዉ ዳዊት ከአሰልጣኞቹ እና ከክፍል ተማሪዎች ጋር ጥሩ ግብቡነት እና መረዳዳት እንደነበራቸዉ ይናገራል። ተማሪ ዳዊት ከእርሱ በፊት የነበሩ ሲኒየር ተማሪዎችን ተሞክሮ በመከተል ዘንድሮ በተካሄደዉ 4ኛዉ አገር አቀፍ የክህሎት ዉድድር በሁሉም የሙያ ዘርፍ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል የሰርቨር ቴክኖሎጅ በመስራት የነሀስ ሜዳሊያ ፣ ሶስት መቶ ሺህ ብር (300,000.00 ) እና የምስክር ወረቀት  ማግኘት ችሏል።  ኢትዮጵያ የአለም የክህሎት ማህበረሰብን  በሙሉ አባልነት ከተቀበለች  በኋላ የዓለም አቀፉን መመዘኛ/መለኪያዎች መሰረት አድርጎ በተካሄደው በዚህ ታላቅ ውድድር ከመላዉ  የሀገራችን አካባቢዎች የተወጣጡ  ታታሪ ባለተሰጥኦዎች የተሳተፉበት፤  በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ ፣  በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ልህቀት ያሳዩ የሚበረታቱበት እና  የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ ለመቅረጽ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ያለውን ወሳኝ ሚና በሚታይበት መድረክ የኮሌጃችን እንቁ ልጅ ዳዊት ፋንታሁን በልዩ ክህሎቱ ደምቆበታል። ወ/ሮ ዘዉዲቱ ፀጋዬ የአይሲቲ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ስትሆን ስለተማሪ ዳዊት ፋንታሁን ስትናገር  '' ዳዊት የተለየ ተሰጥኦ ያለዉ ፤ ት/ክፍላችን ከሚኮራባቸዉ ሰልጣኞች መካከል አንዱ ነዉ ፣ የዲፓርትመንቱን ሰልጣኞች የሚያግዝ ፣ ከአስተማሪ እና ከተማሪ ጋር የሚግባባ ፣ ጠንካራ፣ ተወዳጅ እና በስነምግባር የታነጸ ሰልጣኝ ነዉ ከዚህ የበለጠ ለአገር የሚጠቅም ቴክኖሎጅ ለመስራት ብቃት አለዉ '' በማለት ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል ። ዳዊት ከሚወደዉ ኮምፒዩተር ለአፍታ ዘወር ሲል የእረፍት ጊዜዉን በሙዚቃ ያሳልፋል። የሚገርመዉ በተፈሪ መኮነን ፖሊ/ቴ/ኮሌጅ በማታዉ መርሃ ግብር በሙዚቃ ት/ክፍል ከበሮ (Drum )ይማራል።  ፋንታሁን እንድሪስ እና ገነት ሃይሌ የዳዊት አባት እና እናት ናቸዉ።  ሁለቱም የመንግስት ሰራተኞች ሲሆኑ ለቤቱ 3ኛ እና የመጨረሻ  ልጅ ዳዊት በትምህርቱ በኩል ልዩ ድጋፍ እና እገዛ ያደርጉለታል። የኮሌጁ መመህራን ልምዳቸዉን ያካፍሉታል ፣ ከትምህርት ሰዓት ዉጭ ቢሆንም እንኳን የሾፕ ቴክኒሻኖች እርሱ ላይ ሾፑን ቆልፈዉ ለመሄድ አይጨክኑበትም።የክፍል ጓደኞቹ ይወዱታል በእራስ መተማመኑን እና ቀናነቱን ያደንቁለታል።  ከሌሎች ኮሌጅ ተማሪዎች እና አስተማሪዋች እንዲሁም የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጋር በመገናኘት ልምድ እቀስማለሁ የሚለዉ ዳዊት የወደፊት ራዕዪ በቴክኖሎጅ ዘርፍ የላቀ ቦታ ላይ ደርሶ አገሩን በዓለም መድረክ ማስጠራት እንደሆነ ይናገራል። ዉድ አንባቢያን ዳዊት  በብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት በበቁና በታታሪ ዜጎቿ  ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማምጣት ደፋ ቀና እያለች ለምትገኘዋ ኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ፈንታ ከሚወስኑ አርዕያ የሆኑ ወጣቶች መካከል አንዱ ሲሆን መሰል እምቅ አቅም ኖሯቸዉ የሚታትሩ ወጣቶችን በማበረታታት ለአገራችን እድገት እንትጋ መልክታችን ነዉ። ሰናይ ጊዜ!!           የኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+2

ግንቦት/2017ዓ.ም በክህሎት ዉድድር ያሸነፈዉ  የኮሌጃችን ሰልጣኝ ዳዊት ፋንታሁን ማነዉ ? ዳዊት ፋንታሁን ይባላላል። የ21አመት ወጣት ነዉ። ተወልዶ ያደገዉ አዲስ አበባ ነዉ። የመዋእለ ህጻናት እና የመጀመሪያ  ደረጃ ትምህርቱን በቅዱስ ማርቆስ ት/ቤት ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዛማች በላይ ዘለቀ እንዲሁም የመሠናድኦ ትምህርቱን በዳግማዊ ምኒሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትሏል።  በአሁኑ ሰዓት በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ( Hardware and Networking Service) ት/ክፍል  የ3ኛ አመት ሰልጣኝ  ሲሆን በያዝነዉ ዓመት ስልጠናዉን አጠናቆ ይመረቃል። ተማሪ  ዳዊት ፋንታሁን በ2017 ዓ.ም  ''ብሩህ አዕምሮዎች ፣ በክህሎት የበቁ ዜጐች '' በሚል መሪ ቃል  የስራና ክህሎት ሚኒስተር በአዲስ አበባ ባዘጋጀዉ አራተኛዉ አገር-አቀፍ የተግባራዊ ምርምር ፣ የቴክኖሎጅ እና የክህሎት ዉድድር በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ፣ በሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ( Hardware and Networking Service) ት/ክፍል በተደረገ የክህሎት ዉድድር  3ኛ በመዉጣት የነሀስ ሜዳሊያ ፣ ሶስት መቶ ሺህ ብር (300,000.00 ) እና የምስክር ወረቀት በመሸለም  የተፈሪመኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅን በአገርአቀፍ ደረጃ ማስጠራት የቻለ ባለተሰጥኦ ወጣት ነዉ። ከልጅነቱ ጀምሮ ለኮምፒዩተር ልዩ ፍቅር እንዳለዉ እና በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች ላይ  ተሰጥኦ እንዳለዉ የሚናገረዉ  ዳዊት ፋንታሁን በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ  ትምህርቱ ከፍተኛ ዉጤት የሚያመጣዉ በአይሲቲ (Information Commynication Technology )የትምህርት አይነት እንደሆነ ያስታዉሳል።  ጊዜዉ 2015  ዓ.ም ነበር።ወደ ዩኒቨርስቲ ለመግባት ዉጤት አለማምጣቱ ዳዊትን የሚወደዉን የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ትምህርት ለመሰልጠን በሩን ከፈተለት። በቀድሞ የኮሌጁ ተማሪዎች ጥቆማ በዝና ወደሚያዉቀዉ  ተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮ ለመምጣት አላቅማማም  በአይሲቲ ት/ዘርፍ ከሚሰጡ ስልጠናዎች መካከል በሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ት/ክፍልን በመምረጥ ተመዘገበ ። የተፈሪ መኮንን የአይሲቲ ት/ዘርፍ የተደራጀ የኮምፒዉተር ማስተማሪያ ክፍል ፣ በቂ ልምድ እና እዉቀት ያላቸዉ አሰልጣኞች መኖራቸዉ የበለጠ የስልጠና ጉጉቱን ጨመረለት።  እንደርሱ ተመሳሳይ ፍላጎት ካላቸዉ ታዳጊ ወጣቶች ጋር ስልጠናዉ ተጀመረ። የእወቀትና ክህሎት አድማሱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና አየሰፋ መጣ።  የኮሌጅን ህይወት እንደጠበቅኩት ነዉ ያገኘሁት ይላል ተማሪ ዳዊት '' የኮሌጅ ህይወት በጥሩ መልኩ ካየነዉ ተጨማሪ እዉቀት እና ክህሎት የሚያስጨብጥ ፣ ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያጠናከር ፣ አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር እድል የሚሰጥ መሆኑን የሚያወሳዉ ዳዊት ከአሰልጣኞቹ እና ከክፍል ተማሪዎች ጋር ጥሩ ግብቡነት እና መረዳዳት እንደነበራቸዉ ይናገራል። ተማሪ ዳዊት ከእርሱ በፊት የነበሩ ሲኒየር ተማሪዎችን ተሞክሮ በመከተል ዘንድሮ በተካሄደዉ 4ኛዉ አገር አቀፍ የክህሎት ዉድድር በሁሉም የሙያ ዘርፍ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል የሰርቨር ቴክኖሎጅ በመስራት የነሀስ ሜዳሊያ ፣ ሶስት መቶ ሺህ ብር (300,000.00 ) እና የምስክር ወረቀት  ማግኘት ችሏል።  ኢትዮጵያ የአለም የክህሎት ማህበረሰብን  በሙሉ አባልነት ከተቀበለች  በኋላ የዓለም አቀፉን መመዘኛ/መለኪያዎች መሰረት አድርጎ በተካሄደው በዚህ ታላቅ ውድድር ከመላዉ  የሀገራችን አካባቢዎች የተወጣጡ  ታታሪ ባለተሰጥኦዎች የተሳተፉበት፤  በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ ፣  በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ልህቀት ያሳዩ የሚበረታቱበት እና  የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታ ለመቅረጽ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ያለውን ወሳኝ ሚና በሚታይበት መድረክ የኮሌጃችን እንቁ ልጅ ዳዊት ፋንታሁን በልዩ ክህሎቱ ደምቆበታል። ወ/ሮ ዘዉዲቱ ፀጋዬ የአይሲቲ ስልጠና ዘርፍ ተጠሪ ስትሆን ስለተማሪ ዳዊት ፋንታሁን ስትናገር  '' ዳዊት የተለየ ተሰጥኦ ያለዉ ፤ ት/ክፍላችን ከሚኮራባቸዉ ሰልጣኞች መካከል አንዱ ነዉ ፣ የዲፓርትመንቱን ሰልጣኞች የሚያግዝ ፣ ከአስተማሪ እና ከተማሪ ጋር የሚግባባ ፣ ጠንካራ፣ ተወዳጅ እና በስነምግባር የታነጸ ሰልጣኝ ነዉ ከዚህ የበለጠ ለአገር የሚጠቅም ቴክኖሎጅ ለመስራት ብቃት አለዉ '' በማለት ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል ። ዳዊት ከሚወደዉ ኮምፒዩተር ለአፍታ ዘወር ሲል የእረፍት ጊዜዉን በሙዚቃ ያሳልፋል። የሚገርመዉ በተፈሪ መኮነን ፖሊ/ቴ/ኮሌጅ በማታዉ መርሃ ግብር በሙዚቃ ት/ክፍል ከበሮ (Drum )ይማራል።  ፋንታሁን እንድሪስ እና ገነት ሃይሌ የዳዊት አባት እና እናት ናቸዉ።  ሁለቱም የመንግስት ሰራተኞች ሲሆኑ ለቤቱ 3ኛ እና የመጨረሻ  ልጅ ዳዊት በትምህርቱ በኩል ልዩ ድጋፍ እና እገዛ ያደርጉለታል። የኮሌጁ መመህራን ልምዳቸዉን ያካፍሉታል ፣ ከትምህርት ሰዓት ዉጭ ቢሆንም እንኳን የሾፕ ቴክኒሻኖች እርሱ ላይ ሾፑን ቆልፈዉ ለመሄድ አይጨክኑበትም።የክፍል ጓደኞቹ ይወዱታል በእራስ መተማመኑን እና ቀናነቱን ያደንቁለታል።  ከሌሎች ኮሌጅ ተማሪዎች እና አስተማሪዋች እንዲሁም የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጋር በመገናኘት ልምድ እቀስማለሁ የሚለዉ ዳዊት የወደፊት ራዕዪ በቴክኖሎጅ ዘርፍ የላቀ ቦታ ላይ ደርሶ አገሩን በዓለም መድረክ ማስጠራት እንደሆነ ይናገራል። ዉድ አንባቢያን ዳዊት  በብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት በበቁና በታታሪ ዜጎቿ  ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማምጣት ደፋ ቀና እያለች ለምትገኘዋ ኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ፈንታ ከሚወስኑ አርዕያ የሆኑ ወጣቶች መካከል አንዱ ሲሆን መሰል እምቅ አቅም ኖሯቸዉ የሚታትሩ ወጣቶችን በማበረታታት ለአገራችን እድገት እንትጋ መልክታችን ነዉ። ሰናይ ጊዜ!!           የኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+2

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content