uz
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

Kanalga Telegram’da o‘tish

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Ethiopian Public Service University analitikasi

Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 12 757 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 15 698-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 647-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 12 757 obunachiga ega bo‘ldi.

24 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 100 ga, so‘nggi 24 soatda esa 2 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 31.47% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 14.18% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 013 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 809 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 16 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 25 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

12 757
Obunachilar
+224 soatlar
+187 kunlar
+10030 kunlar
Postlar arxiv
የኢሲሰዩ ካውንስል የ2016 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ ክንውን ግምገማ አካሄደ ------------ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ ክንውን ግምገማ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በስብሰባው መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ዩኒቨርሲቲው ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ተጠሪነቱ ለኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር መሆኑን ተከትሎ በርካታ የሪፎርምና የማሻሻያ ስራዎችን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡ ባደረግነውም ጥረት ከአንጋፋ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በምርምር ዩኒቨርሲቲ ምድብ ስር ለመመደብ የቻልን ቢሆንም ካሉት መስፈርቶችም መካከልም ገና በስፋት ልንሰራባቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ከዕቅዱ ጋር ተካተው እየተተገበሩ መሆናቸውን የምንገመግምበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡ በመቀጠልም አሁን በመተግበር ላይ ባለው አዲስ የመዋቅር ለውጥ ጋር ታያይዞም አመራሩን የማደራጀት፣ ቀጥሎም የዩኒቨርሲቲውን የአካዳሚክ ዘርፍ አመራሮችን የመደልደል እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞችንም በውድድር የመመደብ ሰፊ ስራዎችን ተሰርተዋል፤ የተቀሩትንም ለመመደብ ስራዎች በመሰራት ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ የመዋቅር ለውጡን ተከትሎም የተለያዩ መመሪያዎች፣ ደንቦች እና ፖሊሲዎች ላይ የክለሳና የማሻሻል ስራዎች መሰራታቸውንና ከእነዚህ ክለሳ ከተደረገባቸው መመሪያዎች መካከልም የዩኒቨርሲቲው የሴኔት ሌጅስሌሽን በቅርቡ እንደሚጸድቅ ለካውንስሉ ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ከተማሪዎች የመውጫ ፈተና እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በመተግበር ላይ ካለው ከድህረ ምረቃ የተማሪዎች ቅበላ ፈተናን ከአሁኑ ታሳቢ በማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ለካውንስሉ አሳስበዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲውን የመማር ማስተማር ሥራም በቴክኖሎጂ የተደገፈ በማድረግና ሌሎች ተጓዳኝ ተግባራትም ላይ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ያመላከቱት ፕ/ር ፍቅሬ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ሁለትና ሶስት ዓመታት ውስጥ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን የተቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ዩኒቨርሲቲው ጠንካራ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው፣ ተመራጭ የሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዲኖሩትና ተወዳዳሪ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን፣ በምርምር ዘርፉም ምርታማና ፋይዳ ያላቸው የምርምር ስራዎች የሚሰሩበት ስርዓት እንዲኖር ከወዲሁ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በግምገማው ላይም የአካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ፣ የምርምርና ትብብር ዘርፍ፣ የአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዚደንቶች ዶ/ር ለማ ጉዲሳ፣ ዶ/ር አለማየሁ ደበበ፣ ዶ/ር ታዲዎስ ሜንታ የየዘርፋቸውን የ 2016 ዓ.ም ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የማኔጅመንት ድጋፍ ዘርፍ ሪፖርት ደግሞ በዶ/ር አብርሃም ሐጎስ የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ ቀርቦ ካውንስሉ በስፋት ተወያይቶበታል፡፡ በመጨረሻም ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ በሰጡት ማጠቃለያ አዲስ እየተተገበረ ያለው ሪፎርም ለዩኒቨርሲቲው እጅግ ወሳኝ ከመሆኑ አንጻር ሁሉም የስራ ክፍል የሪፎርም አጀንዳዎቹን በዕቅድ ውስጥ በማካተት ለተግባራዊነቱ መስራት ተገቢ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዩኒቨርስቲ ምድብ ሥር የተካተተ መሆኑን በማስታወስ አንድ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች አንጸር የበለጠ ብቁ ሆኖ መገኘት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው እዚህ ብቃት ላይ እንዲደርስ መስፈርቶቹን መሰረት በማድረግ በበለጠ ትጋትና ኃላፊነት መስራት ፣ ለዚህም ከአሁኑ መነሳት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢሲሰዩ ዘመናዊ መዋዕለ ሕጻናት በማስገንባት ለወሊሰ መስተዳደር አስረከበ ----------------------------------- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ሸዋ ዞን በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን ደረጃውን የጠበቀ ለመዋዕለ ሕጻናት አገልግሎት የሚውል ህንጻ ለከተማ አስተዳደሩ ጥቅምት 17 /2016 ዓ.ም የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዚዳንት፣የቦርድ አባላት፣ የሀገር ሽማግሌ ፣የአካባቢዉ ነዋሪዎች እና የወሊሶ ከተማ አስተደዳር ከንቲባ በተገኙበት ለወሊሶ ከተማ ትምህርት ቢሮ የቁልፍ ርክክብ አደረገ፡፡ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደተናገሩት የዩንቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ የመዋዕለ ህጻናቱን የግንባታ ሂደት ከጅምሩ ጀምሮ በልዩ ሁኔታ እና በአካል ቦታው ላይ በመገኘት ጭምር ሲከታተለው የቆየ ሲሆን በተደረገው ክትትልም የግንባታ ሂደቱ በታቀደው ሁኔታ ተጠናቆ ለዚህች እለት በመድረሳችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲዉ በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቱ የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር ሥራዎችን እየሠራ እና በርካታ የአካባቢው የማህበረሰብ አባላትን ተጠቃሚ እያደረገ ሲሆን ነገር ግን ዩኒቨርሲቲዉ እስከ አሁን ካከናወናቸዉ የማህበረሰብ አገልግሎት ትልቁ እና በአጭር ግዜ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት በመሆኑ በዚህ ፕሮጀክት ለተሳተፋችሁ በሙሉ ኃላፊነታችሁን በአግባቡ ስለተወጣችሁ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲዉ የትምህርት ማዕከሉን መገንባት ብቻ ሳይሆን ለሕጻናቱ የሚያስፈልጉ ግብአቶች ማለትም ወንበር ፣ጠረፔዛ፣ ለመኝታ የሚያገለግል ክፍል ከነቁሳቁሱ ጭምር ያዘጋጀ ሲሆን የተገነቡት ክፍሎች እና ቁሳቁሶች ደረጃቸዉን የጠበቁ ናቸዉ ብለዋል፡፡ወደፊትም ዩንቨርሲቲዉ ከማህበረሰቡ ጎን በመሆን ተቋማዊ ሀላፊቱን እንደሚወጣ ቃል ገብተዋል፡፡ የመስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እንደገለጹት መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤቱ እንደከተማ ብቻም ሳይሆን እንደክልልም በጥራት በአንደኛ ደረጃ የሚቀመጥ መዋዕለ ሕጻናት መሆኑን በመግለጽ ዩኒቨርስቲዉ በትዉልድ ግናባታ ሂደቱ የራሱን አሻራ አስቀምጧል ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም ዩኒቨርስቲዉ ለትምህርት አጋዥ የሆኑ ቁሳቁስ ጭምር በማሟላት ስላስረከበን ምስጋናችን የላቀ ነዉ በማለት ለተደረገላቸዉ ትልቅ እገዛ በመስተዳደሩ ስም አመስግነዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የሀገር ሽማግሌዎች ለተደረገዉ ትልቅ ስራ ምስጋና በማቅረብ ለዘመናት ሲጠየቅ የነበረ ጥያቄ ዩኒቨርሲቲዉ በአጭር ግዜ በመመለሱ ያላቸዉን አክብሮት በምርቃት ገልፀዋል፡፡ በማስከተልም በዚህ ስራ ትልቅ አበርክቶ ላደረጉት ለዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እና የማናጅመንት አባላት የክብር ሽልማት ሸልመዋል፡፡

photo content
+2

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን መዋዕለ ሕጻናት ርክክብ ሊያደርግ ነው ------------------------------ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ሸዋ ዞን በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን ደረጃውን የጠበቀ ለመዋዕለ ሕጻናት አገልግሎት የሚውል ህንጻ ለከተማ አስተዳደሩ ርክክብ ሊያደርግ ነው። ዩኒቨርሲቲው በወሊሶ ከተማ በማስገንባት ላይ ካለው የወሊሶ ካምፓስ ግንባታ ጎን ለጎን በልዩ ትኩረት በማከናወን ላይ ባለው የማህበረሰብ አገልግሎት መሰረት ለአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች የትምህርት አገልግሎት የሚውል የመዋዕለ ህጻናት ህንጻም ሲያስገነባ ቆይቷል፡፡ የዩንቨርስቲው የሥራ አመራር ቦርድም የመዋዕለ ህጻናቱን የግንባታ ሂደት ከጅምሩ ጀምሮ በልዩ ሁኔታ እና በአካል ቦታው ላይ በመገኘት ጭምር ሲከታተለው የቆየ ሲሆን በተደረገው ክትትልም የግንባታ ሂደቱ በታቀደው ሁኔታ ተጠናቆ ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራው ለማስጀመር ዝግጁ እንዲሆን ተደርጓል። በዚህም ጥቅምት 17/2016 የዩኒቨርስቲው ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ አባላት በተገኙብት ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር ርክክብ ያደርጋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በዋናው ካምፓስም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቱ የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር ሥራዎችን እየሠራ እና በርካታ የአካባቢው የማህበረሰብ አባላትን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል።

photo content

photo content
+2

photo content

photo content

photo content
+3

𝐄𝐂𝐒𝐔 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐢𝐝𝐞𝐧𝐭 𝐃𝐢𝐬𝐜𝐮𝐬𝐬𝐞𝐬 𝐖𝐢𝐭𝐡 𝐒𝐡𝐚𝐧𝐠𝐡𝐚𝐢 𝐀𝐝𝐦𝐢𝐧𝐢𝐬𝐭𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐈𝐧𝐬𝐭𝐢𝐭𝐮𝐭𝐞 𝐃𝐞𝐥𝐞𝐠𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 ------------------ Ethiopian Civil Service University (ECSU) president Professor Fikre Dessalegn held a discussion with Professor Mei Lihong, Vice President of Shanghai Administration Institute in China on August 18, 2023 at ECSU Senate Hall. The discussion focused on how to work together for the benefit of the two institutions and create bilateral relations between ECSU and Shanghai Administration Institute. On the discussion, Professor Fikre Dessalegn welcomed Professor Mei Lihong and her team and said that ECSU has established partnership and strong relations with two Chinese universities and this relations also bring a fruitful collaboration between the two higher institutions. He also indicated that ECSU has unique mission, building the capacity of the public service of the country. He also indicated that as a higher educational institution, ECSU has a strong desire to share experiences and resources, work on the capacity building of the staff, joint masters and PhD programs and collaboration with different universities to make research in different thematic areas and this coolaborations brings a possibility to work together with Shanghai Administration Institute.He also thanked the team for their initatives of working in collaborations with ECSU. On the discussion Dr. Abrham Hagose, Head of the President Office, delivered a brief presentation about the university since its establishment and the progress it has registered in the last three decades. Dr. Abrham in his presentation noted that the university has produced more than fifty thousand graduates serving in the public service sectors of the country in different hierarchies including Ministers. By providing scholarship programs to the neighboring countries, the university also produced more than 448 graduates of public servants in the neighboring countries. It also engaged in short term training programs and trained more than two hundred thousand civil servants in different training topics. According to Dr. Abreham, ECSU has produced more than three hundred researches conducted focusing on the public service issues and issued four scientific journals. He also expressed the university has a ten year strategic plan and based on this strategic plan ECSU has active and current partnership and collaboration with Universities in Europe, Asia and in Africa.He added that strengthening of partnership and collaboration among higer institiutions and reserch centers is one of the focus area of the university’s strategic plan. Professor Mei Lihong on her part thanked the University for the Discussion and expressed her anticipation to learn more about each other and identify collaboration areas and communicate to further strengthen their relationship between the two institutions.

photo content
+3

በ ኢሲሰዮ  ሲሰጥ የነበረዉ የሁለተኛ  ዙር የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ ____ የ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ   ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ  ዙር የተቀበላቸውን የተፈጥሮ ሳይንስ  የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በማስፈተን  በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ።   ከሐምሌ 25/2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የተፈጥሮ ሣይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተና በዛሬው ዕለት  ሐምሌ 28/2015 ዓ/ም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መልኩ ተጠናቋል፡፡  ተማሪዎችም ወደየቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ። ከሀገሪቱ ከተለያዩ ቦታ የመጡ የፈተና አስፈፃሚዎች በግቢ በነበራቸው ኃላፊነት ግቢ ከገቡበት ቀን ጀምሮ ፈተናው እስከተጠናቀቀበት ድረስ በነበራቸው ቆይታ ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ከፍተኛ አመራሩ ከጎናቸው በመሆን ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ተፈታኞችም  ፍፁም በተረጋጋ እና በሰላማዊ ሁኔታ ፈተናውን የወሰዱ መሆናቸዉን ገልጸዋል። ዮኒቨርስቲው አመራር ፈተናው የተሳካ እንዲሆን  የተሰጣቸውን ሀላፊነት በተሳካ ሁኔታ ለተወጡ የዩኒቨርሲቲው  ሠራተኞች እና በፈተና ሂደቱ  ተሳታፊ ለሆኑ አካላት በሙሉ  ምስጋና አቅርቧል።

                                                                 25/11/2015                  ማስታወቂያ የ2015የክረምት ፕሮግራምን ይመለከታል    ___ _____ ትምህርት ሚኒስትር በተለያዮ ምክንያቶች ላለፉት ዓመታት የተዛነፈውን የትምህርት ካለንደር ከ 2016 ጀምሮ ለማስተካከል እየሠራ ይገኛል።በቀሪው አንድ ወር ውስጥ ብቻ የክረምት ትምህርትን ማስቀጠል የማይቻል በመሆኑ በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት  የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን።                                          የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርሲቲ                                     

የትምህርት ሚኒስቴር  ሚኒስትር  የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ --------------------------- በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ  ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች   ገለጻ (orientation)  ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም የተሰጠ  ሲሆን በዛሬው ዕለት 25/11/2015 ዓ.ም የመጀመሪያ  ቀን ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ። በማስጀመሪያው ዕለት  የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ  ነጋ እና የከፍተኛ ትምህርትና ልማት ዘርፍ ሚኒስትር  ዲኤታ   ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ   በመገኘት አጠቃላይ የፈተናውን ሂደት በተመለከተ  ጉብኝት አድርገዋል። የኢሲሰዮ  ፕሬዚዳንት  ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ  ለሚኒስትሩ አጠቃላይ ሂደቱን በተመለከተ ገለፃ  ያደረጉላቸዉ ሲሆን የፈተናው ሂደት ያለምንም እንከን አየተካሄደ መሆኑን ገልፀውላቸዋል። የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም በዮንቨርስቲው ይሰጣል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ በኢሲሰዩ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ ተሰጠ --------------------------- በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ (orientation) ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ተሰጠ ። ለተፈታኞች የፈተናው ግብረ ሀይል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ፈተናዉ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም ተማሪዎች በግቢዉ ቆይታቸዉ በሚጠበቁባቸዉ ግዴታዎች ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በማጠቃለያዉም ላይ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለተፈታኞች መልካምና የተሳካ ጊዜ እንዲኖራቸው በመመኘት በዮኒቨርሲቲው ቆይታቸዉ አመራሩ ከጎናቸው እንደሆነ ገልጸዋል። ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም ይሰጣል።

photo content
+4