Ethiopian Public Service University
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Public Service University
تُعد قناة Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 734 مشتركاً، محتلاً المرتبة 15 729 في فئة التعليم والمرتبة 2 648 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 734 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.81%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.95% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 434 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
12 734
المشتركون
+124 ساعات
+187 أيام
+11930 أيام
أرشيف المشاركات
የኢሲሰዩ ዘመናዊ መዋዕለ ሕጻናት በማስገንባት ለወሊሰ መስተዳደር አስረከበ
-----------------------------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ሸዋ ዞን በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን ደረጃውን የጠበቀ ለመዋዕለ ሕጻናት አገልግሎት የሚውል ህንጻ ለከተማ አስተዳደሩ ጥቅምት 17 /2016 ዓ.ም የዩኒቨርስቲዉ ፕሬዚዳንት፣የቦርድ አባላት፣ የሀገር ሽማግሌ ፣የአካባቢዉ ነዋሪዎች እና የወሊሶ ከተማ አስተደዳር ከንቲባ በተገኙበት ለወሊሶ ከተማ ትምህርት ቢሮ የቁልፍ ርክክብ አደረገ፡፡
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እንደተናገሩት የዩንቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ የመዋዕለ ህጻናቱን የግንባታ ሂደት ከጅምሩ ጀምሮ በልዩ ሁኔታ እና በአካል ቦታው ላይ በመገኘት ጭምር ሲከታተለው የቆየ ሲሆን በተደረገው ክትትልም የግንባታ ሂደቱ በታቀደው ሁኔታ ተጠናቆ ለዚህች እለት በመድረሳችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲዉ በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቱ የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር ሥራዎችን እየሠራ እና በርካታ የአካባቢው የማህበረሰብ አባላትን ተጠቃሚ እያደረገ ሲሆን ነገር ግን ዩኒቨርሲቲዉ እስከ አሁን ካከናወናቸዉ የማህበረሰብ አገልግሎት ትልቁ እና በአጭር ግዜ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት በመሆኑ በዚህ ፕሮጀክት ለተሳተፋችሁ በሙሉ ኃላፊነታችሁን በአግባቡ ስለተወጣችሁ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲዉ የትምህርት ማዕከሉን መገንባት ብቻ ሳይሆን ለሕጻናቱ የሚያስፈልጉ ግብአቶች ማለትም ወንበር ፣ጠረፔዛ፣ ለመኝታ የሚያገለግል ክፍል ከነቁሳቁሱ ጭምር ያዘጋጀ ሲሆን የተገነቡት ክፍሎች እና ቁሳቁሶች ደረጃቸዉን የጠበቁ ናቸዉ ብለዋል፡፡ወደፊትም ዩንቨርሲቲዉ ከማህበረሰቡ ጎን በመሆን ተቋማዊ ሀላፊቱን እንደሚወጣ ቃል ገብተዋል፡፡
የመስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እንደገለጹት መዋዕለ ሕጻናት ት/ቤቱ እንደከተማ ብቻም ሳይሆን እንደክልልም በጥራት በአንደኛ ደረጃ የሚቀመጥ መዋዕለ ሕጻናት መሆኑን በመግለጽ ዩኒቨርስቲዉ በትዉልድ ግናባታ ሂደቱ የራሱን አሻራ አስቀምጧል ብለዋል ፡፡ በተጨማሪም ዩኒቨርስቲዉ ለትምህርት አጋዥ የሆኑ ቁሳቁስ ጭምር በማሟላት ስላስረከበን ምስጋናችን የላቀ ነዉ በማለት ለተደረገላቸዉ ትልቅ እገዛ በመስተዳደሩ ስም አመስግነዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የሀገር ሽማግሌዎች ለተደረገዉ ትልቅ ስራ ምስጋና በማቅረብ ለዘመናት ሲጠየቅ የነበረ ጥያቄ ዩኒቨርሲቲዉ በአጭር ግዜ በመመለሱ ያላቸዉን አክብሮት በምርቃት ገልፀዋል፡፡ በማስከተልም በዚህ ስራ ትልቅ አበርክቶ ላደረጉት ለዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ እና የማናጅመንት አባላት የክብር ሽልማት ሸልመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን መዋዕለ ሕጻናት ርክክብ ሊያደርግ ነው
------------------------------
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል በምእራብ ሸዋ ዞን በወሊሶ ካምፓስ ያስገነባዉን ደረጃውን የጠበቀ ለመዋዕለ ሕጻናት አገልግሎት የሚውል ህንጻ ለከተማ አስተዳደሩ ርክክብ ሊያደርግ ነው።
ዩኒቨርሲቲው በወሊሶ ከተማ በማስገንባት ላይ ካለው የወሊሶ ካምፓስ ግንባታ ጎን ለጎን በልዩ ትኩረት በማከናወን ላይ ባለው የማህበረሰብ አገልግሎት መሰረት ለአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች የትምህርት አገልግሎት የሚውል የመዋዕለ ህጻናት ህንጻም ሲያስገነባ ቆይቷል፡፡ የዩንቨርስቲው የሥራ አመራር ቦርድም የመዋዕለ ህጻናቱን የግንባታ ሂደት ከጅምሩ ጀምሮ በልዩ ሁኔታ እና በአካል ቦታው ላይ በመገኘት ጭምር ሲከታተለው የቆየ ሲሆን በተደረገው ክትትልም የግንባታ ሂደቱ በታቀደው ሁኔታ ተጠናቆ ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራው ለማስጀመር ዝግጁ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም ጥቅምት 17/2016 የዩኒቨርስቲው ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ አባላት በተገኙብት ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር ርክክብ ያደርጋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በዋናው ካምፓስም በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቱ የተለያዩ ማህበረሰብ ተኮር ሥራዎችን እየሠራ እና በርካታ የአካባቢው የማህበረሰብ አባላትን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል።
𝐄𝐂𝐒𝐔 𝐏𝐫𝐞𝐬𝐢𝐝𝐞𝐧𝐭 𝐃𝐢𝐬𝐜𝐮𝐬𝐬𝐞𝐬 𝐖𝐢𝐭𝐡 𝐒𝐡𝐚𝐧𝐠𝐡𝐚𝐢 𝐀𝐝𝐦𝐢𝐧𝐢𝐬𝐭𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐈𝐧𝐬𝐭𝐢𝐭𝐮𝐭𝐞 𝐃𝐞𝐥𝐞𝐠𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧
------------------
Ethiopian Civil Service University (ECSU) president Professor Fikre Dessalegn held a discussion with Professor Mei Lihong, Vice President of Shanghai Administration Institute in China on August 18, 2023 at ECSU Senate Hall. The discussion focused on how to work together for the benefit of the two institutions and create bilateral relations between ECSU and Shanghai Administration Institute.
On the discussion, Professor Fikre Dessalegn welcomed Professor Mei Lihong and her team and said that ECSU has established partnership and strong relations with two Chinese universities and this relations also bring a fruitful collaboration between the two higher institutions. He also indicated that ECSU has unique mission, building the capacity of the public service of the country. He also indicated that as a higher educational institution, ECSU has a strong desire to share experiences and resources, work on the capacity building of the staff, joint masters and PhD programs and collaboration with different universities to make research in different thematic areas and this coolaborations brings a possibility to work together with Shanghai Administration Institute.He also thanked the team for their initatives of working in collaborations with ECSU.
On the discussion Dr. Abrham Hagose, Head of the President Office, delivered a brief presentation about the university since its establishment and the progress it has registered in the last three decades. Dr. Abrham in his presentation noted that the university has produced more than fifty thousand graduates serving in the public service sectors of the country in different hierarchies including Ministers. By providing scholarship programs to the neighboring countries, the university also produced more than 448 graduates of public servants in the neighboring countries. It also engaged in short term training programs and trained more than two hundred thousand civil servants in different training topics. According to Dr. Abreham, ECSU has produced more than three hundred researches conducted focusing on the public service issues and issued four scientific journals. He also expressed the university has a ten year strategic plan and based on this strategic plan ECSU has active and current partnership and collaboration with Universities in Europe, Asia and in Africa.He added that strengthening of partnership and collaboration among higer institiutions and reserch centers is one of the focus area of the university’s strategic plan.
Professor Mei Lihong on her part thanked the University for the Discussion and expressed her anticipation to learn more about each other and identify collaboration areas and communicate to further strengthen their relationship between the two institutions.
በ ኢሲሰዮ ሲሰጥ የነበረዉ የሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ
____
የ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ ዙር የተቀበላቸውን የተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በማስፈተን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ።
ከሐምሌ 25/2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የተፈጥሮ ሣይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተና በዛሬው ዕለት ሐምሌ 28/2015 ዓ/ም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መልኩ ተጠናቋል፡፡ ተማሪዎችም ወደየቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ ይገኛሉ።
ከሀገሪቱ ከተለያዩ ቦታ የመጡ የፈተና አስፈፃሚዎች በግቢ በነበራቸው ኃላፊነት ግቢ ከገቡበት ቀን ጀምሮ ፈተናው እስከተጠናቀቀበት ድረስ በነበራቸው ቆይታ ደስተኛ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ከፍተኛ አመራሩ ከጎናቸው በመሆን ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ተፈታኞችም ፍፁም በተረጋጋ እና በሰላማዊ ሁኔታ ፈተናውን የወሰዱ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
ዮኒቨርስቲው አመራር ፈተናው የተሳካ እንዲሆን የተሰጣቸውን ሀላፊነት በተሳካ ሁኔታ ለተወጡ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች እና በፈተና ሂደቱ ተሳታፊ ለሆኑ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርቧል።
25/11/2015
ማስታወቂያ
የ2015የክረምት ፕሮግራምን ይመለከታል
___ _____
ትምህርት ሚኒስትር በተለያዮ ምክንያቶች ላለፉት ዓመታት የተዛነፈውን የትምህርት ካለንደር ከ 2016 ጀምሮ ለማስተካከል እየሠራ ይገኛል።በቀሪው አንድ ወር ውስጥ ብቻ የክረምት ትምህርትን ማስቀጠል የማይቻል በመሆኑ በትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን።
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዮኒቨርሲቲ
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ
---------------------------
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ (orientation) ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም የተሰጠ ሲሆን በዛሬው ዕለት 25/11/2015 ዓ.ም የመጀመሪያ ቀን ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ።
በማስጀመሪያው ዕለት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እና የከፍተኛ ትምህርትና ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት አጠቃላይ የፈተናውን ሂደት በተመለከተ ጉብኝት አድርገዋል።
የኢሲሰዮ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለሚኒስትሩ አጠቃላይ ሂደቱን በተመለከተ ገለፃ ያደረጉላቸዉ ሲሆን የፈተናው ሂደት ያለምንም እንከን አየተካሄደ መሆኑን ገልፀውላቸዋል።
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም በዮንቨርስቲው ይሰጣል፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ በኢሲሰዩ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ ተሰጠ
---------------------------
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ለመዉሰድ ለተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ገለጻ (orientation) ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም ተሰጠ ።
ለተፈታኞች የፈተናው ግብረ ሀይል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ፈተናዉ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም ተማሪዎች በግቢዉ ቆይታቸዉ በሚጠበቁባቸዉ ግዴታዎች ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል።
በማጠቃለያዉም ላይ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ ለተፈታኞች መልካምና የተሳካ ጊዜ እንዲኖራቸው በመመኘት በዮኒቨርሲቲው ቆይታቸዉ አመራሩ ከጎናቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 25 እስከ 28/2015 ዓ.ም ይሰጣል።
በ ኢሲሰዮ ሲሰጥ የነበረዉ የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ
____
የ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዙር የተቀበላቸውን የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በማስፈተን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ።ከሐምሌ 19/2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የማህበራዊ ሣይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተና ሐምሌ 21/2015 ዓ/ም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መልኩ ተጠናቋል፡፡
ተፈታኝ ተማሪዎች እና ከሀገሪቱ ከተለያዩ ቦታ የመጡ የፈተና አስፈፃሚዎች በግቢ በነበራቸው ኃላፊነት ግቢ ከገቡበት ቀን ጀምሮ ፈተናው እስከተጠናቀቀበት ድረስ በነበራቸው ቆይታ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። ተፈታኞችም ፍፁም በተረጋጋ እና በሰላማዊ ሁኔታ ፈተናውን መውሰዳቸውን አሳውቀዋል።
በተመሳሳይ ቀጣይ የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዳጠናቀቁ ገልፀዋል፡፡
