Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Kanalga Telegram’da o‘tish
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Ko'proq ko'rsatish3 584
Obunachilar
-124 soatlar
-67 kunlar
+5130 kunlar
Postlar arxiv
4.የጥገና ወይም የብልሽት አላፊነት መያዣ (Maintenance or Defect Liability Bond)
የጥገና ዋስትና የተበላሹ የግንባታ ግብዓቶችንና የሥራ አሰራር ግድፈቶችን ለመከላከል በሚል ሥራ ተቋራጩ ለፕሮጀክት ባለቤቱ የሚገባው ዋስትና ነው፡፡ በተለይም ከላይ ስለዋና ገንዘብ መያዣ (retention) ቆይታ እንደተመለከተው ለአንድ ዓመት ጊዜ የሚያዝበት ምክንያት ከጥራት ጉድለት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ለመጠገን ነው፡፡ በሚለቀቅበትም ጊዜ ያለቅድመ ሁኔታ ዋስትና ሥራ ተቋራጩ እንዲያቀርብ የሚደረግበት ምክንያት በህንጻው ግንባታ ላይ የሚታዩ ግድፈቶችን ለመጠገን በሚል ነው፡፡
የጥገና እና ብልሽጽ አላፊነት መያዣ በዋናነት የዋና ገንዘብ መያዣ ቆይታ እንዳበቃ የሚጀምር ነው፡፡ በርግጥ ሥራ ተቋራጩ ለባለቤቱ ለተወሰኑ ዓመታት ዋቢ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ፡-በሲቪል የግንባታ ሥራዎች በተለይም በፍ/ህ/ቁ 3039 እንዲህ የሚል ዐ.ነገር ይነበባል፡-
"ሥራ ተቋራጩ ሥራውን ካስረከበበት ጊዜ ጀምሮ ስለመልካም አሰራር፣ ስለሥራው እና ስለጠንካራነቱ ለ10 (አስር) አመት መድን (guarantee/ warranty) ነው፡፡ በዚህም ጊዜ ውስጥ በሥራው ጉድለት ወይም በተሰራበት መሬት ዓይነት ምክንያት በተሰራው ሥራ ላይ ለሚደርሰው መጥፋት ወይም መበላሸት አላፊ ነው፡፡ ”
በተመሳሳይ መልኩ የመንግስት የግንባታ ውሎችንም በተመለከተ የፍትሐብሔር ሕጉ ከአንቀጽ3277-3282 ላይ የ10 (አስር) አመት የብልሽት መድን ጊዜ ያስቀምጣል፡፡
ሆኖም~ አንድ ሥራ ተቋራጭ በሠራው ህንጻ ላይ የተከሠተ እርግጠኛ የአሰራር ጉድለት በሌለበት ሁኔታ ወደፊት የሚታይና የሚከሰት የአሰራር ጉድለት ሊኖር ይችላል በሚል ምክንያት ሥራ ተቋራጮች ለሰሩት ሥራ የመጨረሻ ክፍያ የማግኘት መብት መከልከል አግባብነት የለውም::
የውጭ ምንዛሪ ተመን ተጀምረው የቆሙ ፕሮጀክቶች ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ስላለው የሚመለተው አካል ቶሎ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል?
+5
ሴራሚክ ቴራዞ መግዛት ስትፈልጉ ጥሩ አቅም ያላቸው ደንበኞች አቅራቢዎች ስላሉን አድራሻቸውን ልንሰጣችሁ እንችላለን
📞+251-908280208 | +251- 707999001 ይደውሉልኝ ቴሌግራም/ጥያቄም ሆነ ሀሳብ ካለችሁ በቀጥታ ከስር /ያለውን: t.me/UnitySupplydbot ☜|] ለመልዕክት ይጠቀሙ, ይደርሰናል
3.የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና (Advance Payment Guarantee)
የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና ሲባል ሥራ ተቋራጩ ጨረታውን አሸንፎ ውል ተፈርሞ ወደ ሥራው ሊገባ ሲል የፕሮጀክቱ ባለቤት ለሥራ ተቋራጩ የተወሰነ የቅድሚያ ገንዘብ በመስጠቱ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ በአንጻሩ ለወሰደው ገንዝብ የሚያቀርበው ዋስትና ነው፡፡
በመሰረቱ በኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ጅማሮ የቅድሚያ ክፍያ መኖር በአንድ በኩል ሥራ ተቋራጩ ያለምንም የገንዘብ ችግር ለሥራው የሚያስፈልጉትን ግብዓቶች መግዣ ይሆነዋል፡፡ ወይም ደግሞ ሥራ ተቋራጩ ሥራውን ከፍሎ ለንዑስ ተቋራጮች በሚሰጥበት ጊዜ እንደ ሥራ ማስጀመሪያ (mobilization commission) ይሆናቸዋል፡፡
ስለ ቅድሚያ ክፍያ አስፈላጊነት ታዋቂው የኮንስትራክሽን ክሌም ጸሀፊ ጆን ስካይስ እ.ኤ.አ 1999 በወጣው መጽሀፋቸው እንዳብራሩት ቅድሚያ ክፍያ መኖር ለሥራ ተቋራጮች ከመጥቀሙ ባሻገር የጨረታ ወጥ መለኪያ (tender standardization) ተድርጎ ስለሚወሰድ ጭምር ነው፡፡
የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና መኖረን አስመልክቶ የመንግስት ግዥ አዋጅ ቁ.649/2001 በአንቀጽ 48 እንደተመለከተው የቅድመ ክፍያ ሊፈጸም የሚችለው ሥራ ተቋራጩ በቅድሚያ ክፍያ መልክ ከሚወስደው ገንዘብ መጠን ጋር እኩል የሆነ ዋስትና ሲያቀርብ እንደሆነ ይናገራል፡፡
የመንግስት የኮንስትራክሽን ውሎችን የቅድሚያ ክፍያ መጠንን በተመለከተ እኤአ በ2010 የወጣው የገ/ኢ/ል/ሚ የግዥ መመሪያ አንቀጽ 16.26 ላይ የቅድመ ክፍያ መጠን የውሉን 30(ሰላሣ) ፐርሰንት መብለጥ የለበትም፡፡ ሆኖም ግን በአገር በቀል የሥራ ተቋራጮች የሚሰራ የመንገድ ግንባታ ሲሆን ግን የቅድሚያ ክፍያ ገንዘቡ እስከ 50(ሃምሳ) ፐርሰንት ይደርሳል፡፡
ዝርዝር ሁኔታው በእያንዳንዱ ጨረታ ይገለጻል፡፡
በሥራ ተቋራጩ የሚቀርበው የቅድሚያ ክፍያ ዋስትናው መጠን የተከፈለውን የቅድሚያ ክፍያ ገንዘብ ጋር እኩል መሆን አለበት፡፡ የዋትናው አቀራረብም በቼክ፣ ያል ቅደመ ሁኔታ የሚቀርብ የባንክ ዋስትና ወይም በቅድመ ሁኔታ የሚዘጋጅ የመድን ዋስትና ሊሆን ይችላል፡፡
ሌላው የቅድሚያ ክፍያ ገንዘቡ ለምን ዓላማ መዋል እንደለበትና በምን አግባብ ሊሰጥ እንደሚችል መመሪያው በአንቀጽ 16.26.7 ተመልክቶታል፡፡ በተለይም የመንገድ እና ህንጻ ግንባታ የሚሰሩ ሥራ ተቋራጮች በቅድሚያ ክፍያው ገንዘብ ስለሚገዙት የማሽነሪ ዝርዝር በመመሪያው መሰረት ብቻ ይሆናል፡፡
በበርካታ የግንባታ ቦታዎች የውጭ የግንባታ ተቋራጮችን የምንመለከተው የአገር ውስጥ ተቋራጮች የት ሄደው ነው ?!
የኢትዮጵያ የአገር ውስጥ የግንባታ ተቋራጮች ማህበርና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴርን አነጋግሬያለሁ።
አለምአቀፋዊ ጨረታ የሚወጣው ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆነ ፕሮጀክት ነው። ማህበሩ ወደ 2 ቢሊዮን ማደግ አለበት የሚል ጥያቄ ለመንግሥት አቅርቧል.. .
Via~ኤርሚያስ
ማስታወቂያ:- ለ7ተኛ ዙር ሰልጣኞች በሙሉ!🚧የሰባተኛ ዙር የHealth and Safety in Construction እንዲሁም Ethics in Construction (Code of Conduct for Members of CCAE) ስልጠና ከ CMI ጋር በመነጋገር የሚሰጥበትን ቀን የወሰንን ሲሆን ስልጠናው ከነሐሴ 15 እስከ ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ለሦስት ሙሉ ቀናት ቦሌ ሜጋ ህንፃ ፊት ለፊት በሚገኘው ሀንሰም ህንፃ ላይ በሚገኘው የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት 8ተኛ ፎቅ ላይ ባለው የስልጠና አዳራሽ ይሰጣል፡፡ ስልጠናውን ለመውሰድ የማኅበራችን አባል መሆን ስለሚያስፈልግ የሰልጣኞች የመጨረሻ ስም ዝርዝር የሚገለጸው የማኅበራችን አባል የሆኑት ድርጅቶች ብቻ ይሆናል፡፡ አባል ያልሆናችሁ ድርጅቶች የ7ኛ ዙር ስልጠናውን ለማከናወን እስከ ሰኞ ነሐሴ 13 ቀን 2016ዓ/ም ጠዋት ድረስ ባንቢስ ኃይለገብርኤል ህንጻ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የማህበሩ ፅ/ቤት በአካል በመምጣት የአባልነት ምዝገባችሁን እንድትጨርሱ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያማኅበራችን ስልጠናውን ለማስተባበር ለሚያወጣቸው ወጪዎች 2,500.00 ብር ክፍያ እንደሚጠይቅ ከወዲሁ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ 🏗👷"Think safety, work safely."ደህንነትን አስብ ፤ በጥንቃቄ ስራ" የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማኅበር
✨ https://addiscostestimator.com/
አስደሳች ዜና በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ ለተሰማራችሁ ባለሙያዎች፡፡ አዲስ ኮስት ኤስቲሜተር ይባላል፡፡
ዌብ ሳይቱ ይግንባታዎትን መረጃ ከእርስዎ በመዉሰድ ጥንቅቅ BOQ በኤክሴል አዘጋጅቶ ይሠጥዎታል፡፡
አጠቃቀሙ በጣም ቀላል ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጋችሁ፣ የኢሜል አድራሻ ብቻ ነዉ፡፡
አሁኑኑ በነጻ ይሞክሩት፡፡
✨ጥቅሞቹ
📌የተሟላ የዋጋ ዝርዝር
📌ፈጣን እና ቀላል
📌ቶሎ ቶሎ የሚሻሻል የገበያ ዋጋ
💥ስራዎትን በጥራት እና በፍጥነት በማጠናቀቅ ደንበኛዎትን ያስደስቱ፡፡https://youtu.be/llCVWy7fWTE?si=mVhMe81grc1Uc31f
For more information call 0909068750
✨ https://addiscostestimator.com/
አስደሳች ዜና በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ ለተሰማራችሁ ባለሙያዎች፡፡ አዲስ ኮስት ኤስቲሜተር ይባላል፡፡
ዌብ ሳይቱ ይግንባታዎትን መረጃ ከእርስዎ በመዉሰድ ጥንቅቅ BOQ በኤክሴል አዘጋጅቶ ይሠጥዎታል፡፡
አጠቃቀሙ በጣም ቀላል ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጋችሁ፣ የኢሜል አድራሻ ብቻ ነዉ፡፡
አሁኑኑ በነጻ ይሞክሩት፡፡
✨ጥቅሞቹ
📌የተሟላ የዋጋ ዝርዝር
📌ፈጣን እና ቀላል
📌ቶሎ ቶሎ የሚሻሻል የገበያ ዋጋ
💥ስራዎትን በጥራት እና በፍጥነት በማጠናቀቅ ደንበኛዎትን ያስደስቱ፡፡https://youtu.be/llCVWy7fWTE?si=mVhMe81grc1Uc31f
For more information call 0909068750
በዚህ ድረ-ገፅ ለሚቀርቡ ወይም ይጥቅማል የምትሉት ሃሳብ ካለ በቀጥታ ከስር ባለው ማስፈጠሪያ ቦቱ ሊንክ ያጋሩን:
t.me/UnitySupplydbot ☜|] መልዕክቶን ይላኩልን, ይደርሰናል
የኮንስትራክሽን ዋስትና አይነቶች:-የቀጠለ.. .) 2.የውል ማስከበሪያ ዋስትና (Contract security/ Performance የውል ማስከበሪያ ዋስትና (contract security) ወይም የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና (performance bond) የሚባለው አንድም ግራ ቀኙ ለገቡት ውል መልካም አፈጻጸም ሲባል በአንድ ሦስተኛ ወገን የሚሰጥ ዋስትና ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜም ሥራ ተቋራጮች ለፕሮጀክት ባለቤቶች ወይም ንዑስ ተቋራጮች ለዋናው ሥራ ተቋራጭ ውል ለመፈጸም ብለው ከአንድ የፍይናንስ ተቋም ወይም ሌላ ሦስተኛ ወገን አማካኝነት የሚቀርብ ዋስትና ነው፡፡ ሁኖም ግን ቀደም ሲል እንደተገለጸው የውል ማስከበሪያ ዋስትና ተፈጻሚ የሚሆነው ዋናው ባለዕዳ(ለምሳሌ፡-ሥራ ተቋራጭ) ግዴታውን ባይወጣ ነው፡፡ "ከመንግስት አስተዳደር መ/ቤት ጋር የሥራ ውል ያደረገ ወገን እንደውሉ መፈጸም ባልቻለ ጊዜ የአስተዳደር መ/ቤቱ ተዋዋዩ የውል ማስከበሪያ (contract security) በሚል ካስያዘው ገንዘብ ላይ ውል ባለመፈጸሙ የደረሰበትን የጉዳት ኪሣራ መቀነስ ይችላል፡፡ ” በፌደራል የመንግስት የግዥ እና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁ.649/2001 አንቀጽ 47 ላይ በግልጽ እንደተመለከው በተለይም የመንግስት ግንባታ ውሎች ላይ አቅራቢ (ውል ተቀባይ) ሆኖ የሚቀርብ ወገን ግዴታውን ባለመፈጸሙ ምክንያት በውል ሰጪው መንግስት መ/ቤት ላይ ለሚደርስ ጉዳት ማካካሻ የሚሆን የውል ማስከበሪያ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ መጠኑን በተመለከተም የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡ እኤአ በ ሰኔ ወር 2010 የወጣው የገ/ኢ/ል/ሚ መመሪያ አንቀጽ 16.25 ላይ እንደተመለከው አሸናፊው ሥራ ተቋራጭ ጨረታውን አሸንፎ ውል በተዋዋለ በ 15 ቀናት ውስጥ ቢያንስ የውሉን 10ፐርሰንት እንደ ውል ማስከበሪያ(Performance security) ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ የዋስትናው መክፈያ መንገድም በመመሪያው አንቀጽ 16.16.4 በተመለከተው መሰረት በተጫራቹ ምርጫ በጥሬ ገንዘብ፣ በቼክ፣ የባንክ ዋስትና ሰነድ፣ ክሬዲት ወይም በቅድመ ሁኔታ በሚዘገጅ የመድን ቦንድ ሊሆን ይችላል፡፡ በተጨማሪም መመሪያው በአንቀጽ 16.25.3 ላይ ውል ሰጪው የመንግስት መ/ቤት አቅራቢው (ሥራ ተቋራጩ) በውሉ በተቀመጠው መሰረት ግዴታውን መወጣት ካልቻለ የያዘውን ውል ማስከበሪያ ገንዘብ እንደነገሩ ሁኔታ መጠቀም ወይም መውረስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ሥራ ተቋራጩ ውሉን በተወጣ ጊዜ ያስያዘው ገንዘብ ይመለስለታል፡፡ /የመመሪያው አንቀጽ 16.25.7 ይመለከተዋል፡፡ ሌላው ጉዳይ #የመልካም_ሥራ_አፈጻጸም ዋስትና (Performance bond) በመድን ድርጅቶች መውጣታቸው የዋሱን እና ባለገንዘቡን ግዴታ የሚገዛውን የሕግ ማዕቀፍ ይቀይራል ወይስ አይቀይርም? የሚለው ነጥብ ነው፡፡ ሲጠቃለልም የውል ማስከበሪያ ዋስትና ስለፕሮጀክቱ መልካም አፈጻጸም ውል ተቀባዩ ከአንድ ከሌላ ሦስተኛ ወገን ጋር በሚደርገው ግንኙነት ሊቋቋም ይችላል
የኮንስትራክሽን ዋስትና አይነቶች1.ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) ጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማለት ጨረታ ተወዳድሮ ያሸነፈ ተጫራች ለምሳሌ ሥራ ተቋራጩ በአሸነፈው መሰረት ውሉ ቢሰጠው ግዴታውን ስለመፈጸሙ የሚያቀርበው ዋስትና ነው፡፡ በሌላ አባባል ይህ ዋስትና ሥራ ተቋራጩ ለአሰሪው ጨረታውን በማሸነፉ ወደ ውሉ እገባለሁ ሲል የሚገባው የዋስትና ግዴታ ነው፡፡ ይህም ጉዳይ በመንግስት ግዥ አዋጅ ላይ በአንቀጽ 40 በስፋት ተመልክቷል፡፡ የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያሰሩት ግንባታ በሚያዘጋጁት የጨረታ ሰነድ ተጫራቾች ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር የጨረታ ማስከበሪያ የማቅረብ ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም መያዣ ተጫራቹ ጨረታው አየር ላይ እያለ ከውድድሩ ከወጣ ወይም ከአሸነፈ በኋላ ውሉን ለመፈጸም ፈቃደኛ ካልሆነ የጨረታ መያዣ ገንዘቡ ሊወረስ ይችላል፡፡ በሌላ አባባል የጨረታ ማስከበሪያ በሚል የሚያዝ ገንዘብ ጨረታውን ባዘጋጀው አካል ሊወሰድ የሚችለው ተወዳዳሪው ጨረታውን ባሸነፈው መጠን ሆኖ በጨረታው መሠረት መፈጸም ካልቻለ ወይም አስቀድሞ ከወጣ ነው፡፡ የጨረታ ዋስትናው መጠኑን በተመለከተም እኤአ በ2010ዓ.ም በወጣው የገ/ኢ/ል/ሚ የግዥ መመሪያ አንቀጽ 16.16.2 ላይ እንደተገለጸው የጨረታ ዋስትና የውሉን አጠቃላይ ግምት ወስጥ 0.5 (ግማሽ) እሰከ 2(ሁለት) ፐርሰንት ሊደርስ ይችላል፡፡ ነገር ግን የተባለው የመንግስት መ/ቤት የጨረታ ዋስትናውን መጠን በሚወስንበት ጊዜ ከ500,000.00 (አምስት መቶ ሺ) ብር መብለጥ የለበትም፡፡ የጨረታው አካሄድ ሚዛናዊ እንዲሆን መመሪያው እንደሚለው የመንግስት የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ለማከናወን የሚወጣ ጨረታ ቢያንስ የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ በግዥ የሚሰራው ሥራ የዋጋ አስተማማኝነት ግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡ ሁለተኛ በጨረታው በቂ ቁጥር ያላቸው ተጫራቾች እንዲኖሩ ግድ ይላል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘቡ ተጫራቾችን እንዳይሳተፋ አስቀድሞ የሚከለክል መሆን የለበትም፡፡ ሌላው #የጨረታ_ማስከበሪያ ገንዘቡ አጫራቹ የመንግስት መ/ቤት በጨረታው አሸናፊ የሆነው ተጫራች ጨረታውን ባለመፈጸሙ ምክንያት ሊደርስበት የሚችልን ጉዳት መሸፈን ይኖርበታል፡፡
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
