Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
Kanalga Telegram’da o‘tish
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
Ko'proq ko'rsatish3 590
Obunachilar
-524 soatlar
+37 kunlar
+3830 kunlar
Postlar arxiv
ማስታወቂያ: ለነባር እና ለአዳዲስ ስራ ተቋራጮች እና ማህበራት በሙሉ ፡-
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከቤት ልማቱ ጎን ለጎን ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚው ተጠቃሚ ሲያደርግ የቆየና እያደረገም ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ በሚኖረው የግንባታ ፕሮጀክቶች በዘርፉ የተሠማሩ ስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን አሳታፊ አድርጎ ለመስራት ያሰበና ለዚህም ይረዳው ዘንድ በከተማችን ያሉትን የስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን በመመዝገብ መረጃዎችን አደራጅቶ መያዝ እና መመልመል አስፈላጊ ሆኖ ማግኘቱን በቅርቡ በተቋሙ ማህበራዊ ድረ-ገጽ አሳውቋል፡፡
በዚህም መሰረት ለነባር እና አዳዲስ ተመዝጋቢዎች ከቀን 13/10/2015 - 27/10/2015 ዓ.ም ድረስ ለለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት online ምዝገባ ማካሄድ እንደሚጀመር እየገለጽን ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) https://www.aahdc.gov.et
በመጫን እና የሚጠይቀውን መረጃ በአግባቡ በማስገባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡-
በነባር፡-
በተቋማችንና በተለያዩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የስራ ትስስር ተደርጎላችሁ ስትሠሩ የነበራችሁ ስራ ተቋራጮችና ማህበራት ነባር በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማድረግ ያለባችሁ ሲሆን፤
በአዲስ፡-
ከዚህ በፊት በተቋማችንም ሆነ በቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ምንም ዓይነት የስራ ትስስር ያልተደረገላችሁ አዲስ በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማካሄድ ትችላላችሁ፡፡
ለምዝገባ አስፈላጊ ማስረጃዎችን በድጋሚ ለማስታወስ ያህል፡-
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- የግበር መክፈያ መለያ ቁጥር( Tax
Identification Number- TIN.)
- የስም ስያሜ ምዝገባ ሰርተፊኬት
- የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት
- የስራ ልምድ ከ1-2 ገፅ በማይበልጥ
በዝርዝር ይጠቀስ
- የስራ ልምድ ክብደት በገንዘብ ሲቀየር
የሚያሳዩ መረጃዎች
- እና ሌሎች ስራ ተቋራጩን እና
ማህበራቱን የሚገልጹ ሰነዶችን ናቸው
ማሳሰቢያ፡-
ከስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ ከሚመለከተው አካል በሚላከው መረጃ መሠረትና በተቋማችን ባለው መረጃ መሠረት ወደ ስራ ሲገባ በነባር መመዝገብ እያለባችሁ በአዲስ ተመዝግባችሁ የተገኛችሁት ላይ እንዲሁም በሁለቱም (በነባርም፣በአዲስም) ተመዝግቦ የሚገኝ ስራ ተቋራጭም ሆነ ማህበራት ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን t.me/unityconsupply
ተቋራጭን ከሳይት ስለማባረር/Expel right/ By: Gubaie A.
--------- --------------- ----
በዚህ ጽሁፍ ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብት ለማን የተሰጠ ነው?በየትኛው ህግ?በምን ሁኔታ?በየትኛው የውል አይነት?በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት?የሚሉትን በአጭሩ ለመጠቆም እንሞክራለን፡፡
*ይህ መብት ያለው የትኛው አካል ነው? የሚለውን በተመለከተ ተቋራጭን ከግንባታ ሳይት/ከግንባታ ስፍራ ለማባረር መብት ያለው አሰሪው ነው፡፡ስለዚህ መብቱ የግንባታው ባለቤት ወይም የአሰሪው ነው፡፡ስለዚህ ይህን መብት ተቋራጮች ሆኑ አሰሪ ያልሆነ ሌላ አካል ተግባራዊ ሊያደርገው አይችልም ማለት ነው፡፡
.
*በየትኛው ህግ? ለሚለው ምላሹ በፍትሀብሄር ህጉ እና በጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት ነው፡፡በዝርዝር ሲታይ፡-
-በግንባታ ውሎች በተለይ ጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት መጠቀም የተለመደ ነው፡፡እነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች በራሳቸው ህግ አይደሉም፡፡እዚህ ላይ አንዳንድ የህግ ባለሙያዎች እንደ መመሪያ እና ህግ ስለሚቆጥሩት ይህ የግንዛቤ ክፍተት መታረም ይኖርበታል፡፡የግንባታ ውል ተዋዋዮች በስምምነታቸው እነዚህን ጀኔራል ኮንዲሽኖች የውሉ አካል ሲያደርጓቸው በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1731 መሰረት በተዋዋዮች መካከል እንደ ህግ ሆነው ይቆጠራሉ፡፡እዚህ ላይ ሌላው ጉዳይ ስፔሻል ኮንዲሽን ኦፍ ኮንትራክት ተብለው የሚቀመጡት ከጀኔራል ኮንዲሽኑ ድንጋጌዎች የተፈጻሚነት ቅድሚያ ይኖራቸዋል፡፡ለምሳሌ ከነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች ውስጥ የሲቪል ግንባታ ስራዎች ቋሚ የውል መተዳደሪያ/Standard condition of contract for the construction of civil work projects/ አንዱ ነው፡፡ይህ ጀኔራል ኮንዲሽን በከተማ ልማት ሚኒስቴር በኩል የተዘጋጀ ሲሆን ይዘቱ በዋናነት ከFIDIC 1987 version የተወሰደ ነው፡፡በአብዛኛው MoWUD 1994 ተብሎ ይጠራል፡፡ሆኖም ዋናው ነጥብ ተዋዋዮች ጥቅም ላይ ያዋሉትና የውላቸው አካል ያደረጉት የትኛውን ጀኔራል ኮንዲሽን እንደሆነ መለየትና ማወቅ የግድ ይላል፡፡
-ከዚህ አንጻር MoWUD 1994 ክሎዝ 63 ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብትን አስመልክቶ በዝርዝር አስቀምጦታል፡፡በዚህ ድንጋጌ መሰረት በዋናነት አማካሪ መሀንዲሱ ለአሰሪው የተቋራጩን እንደውሉ ያለመፈጸም ሲያሳውቅ በተለይም ተቋራጩ ስራውን እንደተወው አማካሪው ሲያስታውቅ፣ተቋራጩ በአማካሪ መሀንዲሱ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ለ28ቀናት ስራውን ሳይጀምር ሲቀር፣በመሀንዲሱ ተቀባይነት የላቸውም የተባሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በ28 ቀናት ውስጥ ከሳይት ያላስወጣ እንደሆነ፣በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ስራውን በውሉ አግባብ ለመፈጸም ፈቃደኛ ያልሆነ እንደሆነ፣አማካሪ መሀንዲሱ እየከለከለው የስራውን ክፍል ለሌላ ተቋራጭ አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ ወይም ተቋራጩ የከሰረ እንደሆነ አሰሪው የ14 ቀን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት ማባረር የሚችል ይሆናል፡፡በዚህ ጊዜ ውሉ ይቋረጣል ማለት ነው፡፡/Termination of contract/
በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3288 አና ተከታዮቹ ላይ የተደነገገውም ተቋራጩ የውል ግዴታውን ባልፈጸመ ጊዜ የግንባታ ባለቤት ለሆነው ለአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ስራውን ከተቋራጩ ለመንጠቅ እና ውሉ ሳይቋረጥ ስራው በስራ መሪ ስር ሆኖ እንዲቆይ ለማድረግ መብት ይሰጠዋል፡፡እንዲሁም ውሉ ሊሰረዝ የሚችልበት ፈቃጅ የውል ቃል በግንባታ ውሉ ላይ ያለ እንደሆነ አሰሪው ቀሪውን ስራ ለሌላ ተቋራጭ በጨረታ ወይም በስምምነት በማሰራት እንዲጠናቀቅ ማድረግ ይችላል፡፡/የፍ/ህ/ቁ 3291(1) በዚህም ምክንያት አሰሪው ለተጨማሪ ወጭ/Additional cost/ የተዳረገ እንደሆነ ከተቋራጩ ላይ ለመጠየቅ እንደሚችል የፍ/ህ/ቁ 3291(2) በግልጽ መብት ይሰጠዋል፡፡ሆኖም በውል ህግ ላይ አሰሪው የተቋራጩን ግዴታ በሚያከብድ ሁኔታ ቀሪውን ስራ ማከናወን እንደሌለበት የሚያስገነዝበውን ግዴታውንም ማክበር አለበት፡፡
በየትኛው የውል አይነት? ለሚለው በዋናነት የአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ውሎችን በሚመለከት ሊተገበር የሚችል ነው፡፡ በግል የግንባታ ውሎች/private construction contract/ በተለይ ከፍ/ህ/ቁ 2610 እና ተከታዮቹ እንዲሁም ከፍ/ህ/ቁ 3019 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ውስጥ ተቋራጭን ስለማባበር አስመልክቶ ግልጽ ድንጋጌ አለመኖሩ ይህ መብት ለግለሰቦች ለመተግበር አስቸጋሪ የመሆኑን ሁኔታ ታሳቢ ተደርጐ በህግ አውጭው በማወቅ/ፐርፐዝሊ/ የተተወ ይመስላል፡፡ተዋዋዮች የግንባታ ውል ሲዋዋሉ ጀኔራል ኮንዲሽን ቢጠቀሙና በዚህም ስለተቋራጭ የማባረር መብት ድንጋጌ ቢኖረውስ የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል?ይሄን እንዴት ይተገብረዋል የሚለው ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ውሉ ግን ለተዋዋዮች ህግ ስለሚሆን በተቻለ መጠን ሊተገበር ይገባዋል የሚል እሳቤ አለኝ፡፡
በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት? ለሚለው በዋናነት በ MoWUD 1994 ክሎዝ 63(2) ላይ እንደተቀመጠው በግንባታ ሳይት ላይ የተገኘ ቁሳቁስ በሙሉ በዝርዝር መመዝገብና ዋጋ ወጥቶለት መጠኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡በተቋራጩ የተሰራው ስራ መጠን/level of work done/ በትክክል መታወቅና በዝርዝር መመዝገብ አለበት፡፡ተቋራጩ ያለበት እዳ/ከወሰደው የቅድሚያ ክፍያ ውስጥ ያልመለሰው ማለት ነው/ መታወቅ አለበት፡፡ለተቋራጩ የተከፈለው የስራ ክፍያ ሊታወቅ ይገባል፡፡እነዚህን የሂሳብ ሁኔታዎች አመዛዝኖ እና ዋጋ አስቀምጦ ተቋራጩ የሚከፈለው ገንዘብ ካለ እንዲከፈለው ለአሰሪው የሚመልሰው ገንዘብ ካለም እንዲመልስ ሂሳብ የማስተሳሰብና ሪፖርት የማቅረብ ሀላፊነቱ የአማካሪ መሀንዲሱ ነው፡፡በዚህ ረገድ አማካሪ መሀንዲሶች ብዙ ጊዜ እንደዚህ አይነት ሪፖርት ስለማያቀርቡ የግንባታ ክርክሮች ያልተሸከፉ ይሆኑና ለፍርድ ቤቶች ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ አስቸገሪ ሁኔታ ይፈጥራሉ፡፡
አሰሪው ይህን መብቱን ለመጠቀም ሀይል መጠቀም የሚችልበት ግልጽ ፈቃጅ ህግ ግን የለም፡፡
በመጨረሻም አሰሪና ተቋራጮች ለግንባታ ጥራት በመስራትና ለትክክለኛ እና እውነተኛ ነገር በመተባበር የኮንስትራክሽኑ ዘርፍ እድገት እንዲያሳይ ማገዝና አለመግባባቶችን በስምምነት መፍታት ቢችሉ ጠቀሜታው ለሀገርም ለራሳቸውም ነው፡፡በአሰሪና ተቋራጭ ክርክር ብዙ ትምህርት ቤት እና የጤና ተቋም እንዲሁም ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታቸው ተቋርጦ ማህበረሰቡን ከተጠቃሚነት የሚያዘገይበት ሁኔታ ወደፊት ተቀርፎና ተቃልሎ ማየት የዘወትር ምኞታችን ነው፡፡
እንኳን ለኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! በዓሉ: የሰላም የፍቅር የደስታ የመረዳዳት የመከባበር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!
ድርጅትዎን" እና አገልግሎትዎን" ከ85,000ሺ ቤተሰብ በላይ ባለው ድረ-ገፃችን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ? በቀላሉ ተደራሽነትዎን' ያሥፉ.. .) ያሳውቁ! ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
📞+251-989-999-001 | +251-
707-999-001 | 09-12-815619
ቴሌግራም ላይ ጥያቄ ሆነ ሀሳብ
ካለችሁ በቀጥታ ከስር /ያለውን:
t.me/UnitySupplydbot ☜|]
ለመልዕክት ይጠቀሙ, ይደርሰናል
ዩኒቲ ኮንስትራክሽን ስራ ኦፊሻሎች
http://t.me/unitysupplydb1
በቋሚነት ለተሻለ ለውጥ እንተጋለን
ለርስዎና ለወዳጅ ዘመድዎ' በሙሉ
መልካም በዓል እንዲሆን እንመኛለን!
"ዒድ ሙባረክ!
ዩ ኒ ቲ´ | Official
ማስታወቂያ፦ ለተከበራችሁ የማኅበራችን አባላት!
ከዚህ ቀደም ሲል የ “Claims Management” ሥልጠና በማኅበራችን በኩል ለመስጠት ታስቦ ፍላጎት ያላችሁ አባላት እንድትመዘገቡ ጥሪ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡ በዚሁ ጥሪ መሠረትም የየአባል ድርጅቶቹ ባለቤቶች በእራሳቸው ሥልጠናውን ለመውሰድ በመሻት የተመዘገቡ እንዳሉ ሁሉ በየአባል ድርቶቹ ውስጥ የሚገኙ በተለያየ የሥራ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሙያተኞችም ሥልጠናውን እንዲወስዱ ስማቸው እንደተላለፈልን ይታወቃል፡፡
ይሁንና ይህን ሥልጠና በመጀመሪያ እንዲወስዱ በማኅበራችን በኩል የታቀደው እራሳቸው የየአባል ድርጅቶቹ ባለቤቶችን ሲሆን ይህም ሲታቀድ ተከታታይነት ያለው ሰፊ ሥራ ለመሥራት በማሰብና የሥራ መመሪያ (Working Manual) እንዲዘጋጅ ለማድረግ በማለምም ነው፡፡
ይህም ማኅበሩን ወጪ የሚያስወጣው ሆኖ ስለተገኘ የየአባል ድርጅቶቹ ባለቤቶች አሁን በታቀደው ሥልጠና ላይ እንዲካፈሉ ሆኖ ዓላመውን በተጨባጭ በመረዳት ከዚህ አንፃር ለምናደርገው የሥራ እንቅስቃሴም ማኅበሩን በፋይናንስ እንዲያግዙ አስበን በመሆኑ የየአባል ድርጅቶቹ ባለቤቶች ትመዘገቡ ዘንድ በታላቅ አክብሮትና ትህትና ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር
በአዲስ_አበባ_ቤቶች_ልማትና_አስተዳደር_ቢሮ_የአዲስ_አበባ_ቤቶች_ልማት_ኮርፖሬሽን.pdf9.39 KB
በአዲስ_አበባ_ቤቶች_ልማትና_አስተዳደር_ቢሮ_የአዲስ_አበባ_ቤቶች_ልማት_ኮርፖሬሽን.pdf9.39 KB
ማስታወቂያ: ለነባር እና ለአዳዲስ ስራ ተቋራጮች እና ማህበራት በሙሉ ፡-
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከቤት ልማቱ ጎን ለጎን ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚው ተጠቃሚ ሲያደርግ የቆየና እያደረገም ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ በሚኖረው የግንባታ ፕሮጀክቶች በዘርፉ የተሠማሩ ስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን አሳታፊ አድርጎ ለመስራት ያሰበና ለዚህም ይረዳው ዘንድ በከተማችን ያሉትን የስራ ተቋራጮችንና ማህበራትን በመመዝገብ መረጃዎችን አደራጅቶ መያዝ እና መመልመል አስፈላጊ ሆኖ ማግኘቱን በቅርቡ በተቋሙ ማህበራዊ ድረ-ገጽ አሳውቋል፡፡
በዚህም መሰረት ለነባር እና አዳዲስ ተመዝጋቢዎች ከቀን 13/10/2015 - 27/10/2015 ዓ.ም ድረስ ለለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት online ምዝገባ ማካሄድ እንደሚጀመር እየገለጽን ከዚህ በታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) https://www.aahdc.gov.et
በመጫን እና የሚጠይቀውን መረጃ በአግባቡ በማስገባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡-
በነባር፡-
በተቋማችንና በተለያዩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የስራ ትስስር ተደርጎላችሁ ስትሠሩ የነበራችሁ ስራ ተቋራጮችና ማህበራት ነባር በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማድረግ ያለባችሁ ሲሆን፤
በአዲስ፡-
ከዚህ በፊት በተቋማችንም ሆነ በቅርንጫፍ ፅ/ቤቶቻችን ስር ምንም ዓይነት የስራ ትስስር ያልተደረገላችሁ አዲስ በሚለው ስር ምዝገባችሁን ማካሄድ ትችላላችሁ፡፡
ለምዝገባ አስፈላጊ ማስረጃዎችን በድጋሚ ለማስታወስ ያህል፡-
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- የግበር መክፈያ መለያ ቁጥር( Tax
Identification Number- TIN.)
- የስም ስያሜ ምዝገባ ሰርተፊኬት
- የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት
- የስራ ልምድ ከ1-2 ገፅ በማይበልጥ
በዝርዝር ይጠቀስ
- የስራ ልምድ ክብደት በገንዘብ ሲቀየር
የሚያሳዩ መረጃዎች
- እና ሌሎች ስራ ተቋራጩን እና
ማህበራቱን የሚገልጹ ሰነዶችን ናቸው
ማሳሰቢያ፡-
ከስራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ ከሚመለከተው አካል በሚላከው መረጃ መሠረትና በተቋማችን ባለው መረጃ መሠረት ወደ ስራ ሲገባ በነባር መመዝገብ እያለባችሁ በአዲስ ተመዝግባችሁ የተገኛችሁት ላይ እንዲሁም በሁለቱም (በነባርም፣በአዲስም) ተመዝግቦ የሚገኝ ስራ ተቋራጭም ሆነ ማህበራት ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
INVITATION FOR RETENDERING
IFB No. ECWCT/NCB/PW-128/2015
1. The Ethiopian Construction Works Corporation (ECWC) hereby invites registered eligible bidders for TO SUPPLY AND FIX OF METAL WORKS
2. Interested Potential Bidders are required to present renewed relevant Trade License for the Ethiopian fiscal year, VAT Registration Certificate, Tax Clearance Certificate and Online Supplier list Registration Certificate together with their offer.
3. Bidding document should be prepared in English language.
4. Interested Potential Bidders obtain a complete set of bidding document from the office of Procurement Department against payment of none refundable fee of Birr 300.00 upon presentation of Trade License renewed for the fiscal year.
5. This invitation of bid is open to all interested potential bidders regardless of their nationality and the bid evaluation and award shall be determined in accordance with the provision indicated in bidding document.
6. The deadline for bid Submission shall be on June 28, 2023, at 08:00 (Local Time)
7. Bid must be accompanied with a Bid Security of an amount of Birr Birr 300,000.00 ETB (Three hundred thousand) in the form of certified cheque (CPO) or Bank guarantee. Bid Bond in the form of insurance bond or in any other form shall not be accepted.
8. Bids must be delivered or deposited in the Tender Box situated at the office of the Procurement Department on June 28, 2023, at 08:30 (Local Time). in Ethiopian Construction Works Corporation Procurement Department conference room, in the presence of bidders and/or their representatives who choose to attend.
10. The Ethiopian Construction Works Corporation reserves its rights to reject any or all bids.
11. Bidders may get further information at the following address:
Ethiopian Construction Works Corporation
Address: - Gurd shola behind Athletics Federation Building
In front of Andinet International school
Telephone No.011 8 72 29 58/ 0118 72 30 86/011 896 29 91
ማስታወቂያ: ለኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማኅበር አባላት!
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ከመጪው ሐምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል በመንግሥት የተወሰነውን የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት የተመለከተ የውይይት መርኃ-ግብር አዘጋጅቷል፡፡
በዚሁ መሠረት በመጪው ሰኔ 13 ቀን 2015 ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት በሸራተን አዲስ ሆቴል በሚዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ በዚህ የግዥ ሥርዓት የተመዘገባችሁ አባላትም ሆናችሁ ያልተመዘገባችሁት የማኅበራችን አባላት እንዲሁም መላው የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች በዚሁ የውይይት መርኃ-ግብር ላይ ተካፋይ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል፡፡
በተለይ በዚህ በአዲሱ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት ያልተመዘገባችሁት የማኅበራችን አባላትም ሆናችሁ ያልተመዘገባችሁት መላው ሥራ ተቋራጮች ከሐምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በማንኛውም የመንግሥታዊ ግዥ ሥርዓት ውስጥ ተሳታፊ መሆን የሚችሉት በአዲሱ የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓት ውስጥ የታቀፉ ሥራ ተቋራጮች ብቻ መሆናቸውን ከወዲሁ ተገንዝባችሁ በመርኃ-ግብሩ ላይ ተሳታፊ እንድትሆኑ አጥብቀን እንመክራለን፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
