uz
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Assaye Derbie analitikasi

Assaye Derbie (@asayede) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 336 obunachidan iborat bo'lib, Bloglar toifasida 2 651-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 347-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 336 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -104 ga, so‘nggi 24 soatda esa -8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 35.99% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 12.61% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 158 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 808 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 30 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Bloglar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 336
Obunachilar
-824 soatlar
-327 kunlar
-10430 kunlar
Postlar arxiv
እቅዳቸው እና መፍትሔው አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬▬ እቅዳቸው ➔በአብዛኛው የአማራ ምድር ላይ የተፈጸመውን ውድመት ከጥቃቱ ለተረፉ አካባቢዎች ማጋራት፤ ➔ልክ እንደ ሰኔ 15ቱ ጥቃት አጥቂ እና ተጠቂን በዞን ሸንሽኖ መላው ሕዝባችንን ከጫማቸው ስር መሸርኮት፤ ➔አማራን ውጥረት ውስጥ ከከተቱ በኋላ መሃል መንገድ ላይ የተቋረጠውን ዘመቻ ግልጽ በሆነ መልኩ ወደ ጠረጴዛ አምጥቶ ‹‹ወራሪው በሠራው ወንጀል አማራው ካሳ ይክፈል›› የሚል ውሳኔ ማስተላለፍ፤ ➔ሕዝብን ከወራሪ ጠላት ሊታደግ የወጣውን ፋኖ አክስሞ ለካድሬ ወንበር የሚያደገድገውን ማደራጀት፤ ይህ የጥፋት ድግስ ዒላማውንም ሆነ ዓላማውን እንዳያሳካ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? ▬▬▬▬▬▬▬▬ ➔‹‹እርስ በእርስ ይጠፋፉበት›› ተብሎ የተሰጠንን ሤራ ወደ ውይይት አምጥተን ችግሩን በንግግር መፍታት፤ ➔ለዞን ክፍፍል የሚዳርገውን እና የተበጣጠሰውን የፋኖ አደረጃጀት በአማራዊ ማዕቀፍ ውስጥ የሚያስተሳስር መዋቅር መዘርጋት፤ ➔ጸረ አማራዎች በየትኛውም ስፍራ በሚኖረው አማራ ላይ ለሚፈጽሙት ጥቃት ዞናዊ እውቅና ሰጥተን እራሳችንን ለጥቃት በመዳረግ ፈንታ በአንድነት ቆመን ያነጣጠረብንን አፈሙዝ መመከት፤ ➔የአማራን አንድነትና ሰላም ከማስከበር ይልቅ ሕዝብን በዞን በመለያየት አማራን ማስበላት የሚሹ ኃይሎችን ከጉያችን ነጥለን ማውጣት፤ ➔ሕዝባችንን ለመጉዳት ሃያ አራት ሰዓት እንቅልፍ አጥተው በሚራወጡ ውጫዊ ሃይሎች ፈንታ፤ ሃያ አራት ሰዓት እንቅልፋቸውን የሚለጥጡና ሕዝባቸውን አሳልፈው የሚሰጡ አመራሮችን እና ፖለቲከኞችን ‹‹ለሚደርሰው ነገር ሁሉ ተጠያቂው እናንተ ናችሁ›› የሚል ሃላፊነት መስጠት፤ ➔በእኛ ድክመት የተሰው ጀግኖችን ፎቶ ለጥፈን ከመነፋረቅ ይልቅ በሕይወት ያሉ ጀግኖችን መጠበቅ እንደሚጠቅም መረዳት፤ Share

ከአብዛኛው የአማራ ዲያስፖራ በሚያገኘው የዶላር እርጥባን እየተንቀሳቀሰ፣ በአገር ሥም የወንበር አገልጋይ ሆኖ፣ ያለምንም ቀይ መስመር በሚጓዙ ደላሎቹ አማካኝነት... የወገንን እልቂት፣ የመንግሥትን ክሕደት እና የአገራችንን ፍርሰት ከሚያለማምደን "የኢሳት ሚዲያ" ይልቅ ግልጽ በሆነ መልኩ ወጥተው የጥፋት ቅስቀሳ የሚያካሂዱብን ሚዲያዎች ምስጉኖች ናቸው።

ደጺ ከመንግሥት ጋር እያተደረገ ባለው ቀጥተኛ ያልሆን ንግግር የተወሰነ ውጤት መታየቱን ለቢቢሲ ገልጿል። ይህ ውጤት "አፋርን እንዲወጋ አመቻቹልኝ" ወይም ደግሞ "ኢመደበኛውን ፋኖ አጥፉልኝ" ከሚል ጥያቄ የተገኘ ይሆን? 😁

እኔ እምለው አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ባሳለፍነው ዘመን አማራን ከጥቃት ፥ ለማዳን የለፉ፤ በወስላቶች ችሎት "ስጋቶች" ተብለው ፥ አይተናል ሲጠፉ። እናም... ቀራንዮ ታዛ የለንጊኖስን ጦር ፥ በጨበጠ ዳኛ ሐቀኛው ነውና ተወግቶ የሚሞት ፥ እንደ ወንጀለኛ፤ ማደኛው ሳይፃፍ፥ ፍርዱ ሳይፈጸም ፋይሉ ይቅረብና ፥ ፈራጁን እንገምግም።

ሸኔን በሪፖርት፣ ፋኖን በጥይት አይሆንም! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ አራዳው ብልጽግና በሥሙ ሲጠሩት ‹‹አቤት›› ባይ አመራር የሌለው የሽብር ድርጅት እውን አድርጎ የንጹሐንን ሐብትና ሕይወት ሲያስወድም ከረመ፡፡ ከሰሞኑም ከጌጃው ብልጽግና ጋር ባደረገው ስብሰባ ፋኖን ከመምታት በፊት ሸኔን ደምስሻለሁ ማለት እንደሚቀድም ተረድቶ በታጣቂው ፈንታ ተጠቂው ላይ በወሰደው እርምጃ የቀማቸውን መሣሪያዎች ሲያሳየን ነበር፡፡ ከእነዚህም መሣሪያዎች መሃከል አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ማንገቻ ያለው ቁመህ ጠብቀኝ ጠመንጃ ቀላቅሎ ‹‹ከሸኔ ያስፈታኋቸው ናቸው›› እያለ ሲነግረን ነበር፡፡ ከዚህ ባለፈም ‹‹21 የሸኔ ታጣቂዎች እጅ ሰጡ›› በሚል ዜና 28 መንገደኞችን የያዘ ፎቶ ለጥፎ ‹‹ሰባቱ እግር የሰጡ ናቸው ወይ?›› የሚል ትችት ሲያስተናግድ ነበር፡፡ ያ ሁሉ ልፋት ታዲያ፣ አሸባሪው ሃይል አፋር ገብቶ ቅልጥ ያለ ትግል እያደረገ ባለበት ሁኔታ ‹‹ድል አድርጌያለሁ›› ብሎ የተመለሰው አካል፣ ፋኖን መትቶ አማራን ለዳግም ጥቃትና ለባርነት ከመዳረግ የሚመነጭ ነው፡፡ ኦነግ በሪፖርት ሲደመሰስ የከረመው የፋኖን ደም በጥይት ለማፍሰስ ነው፡፡ ኢ-መደበኛ ሃይል የተባሉት አሁንም ድረስ ሕያው ሆነው የንጹሐንን ሕይወት በመቅጠፍ ላይ የሚገኙት አሸባሪዎች ሳይሆኑ ‹‹የመጣብህ ጠላት በመደበኛው የጸጥታ ሃይል የሚመከት ስላልሆነ ተነስና ለህልውናህ ታገል›› በሚል የክተት ጥሪ በእራሱ ስንቅና ትጥቅ ሲዋጋ የከረመው ፋኖ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ግን ፋኖ ላይ ጣትን ከመቀሰር በፊት ድል በሚል ሥም መሃል መንገድ ላይ የተቋረጠውን ትግል መቋጨት ያስፈልጋል፡፡ ለህልውናው የሚታገለውን ፋኖ ለማጥቃት ከማሰብ አስቀድሞም የንጹሐንን ሕልውና ሲነጥቅ ከርሞ በሪፖርት የተደመሰሰው አሻባሪ ላይ ተጨባጭ እርምጃ መውሰድ ግድ ይላል፡፡ ያን ጊዜ ኢመደበኛውም ሆነ መደበኛው ፋኖ እርምጃ ሳትወስዱበት በፊት ነፍጡን ጥሎ ማረሻውን እና ደብተሩን ያነሳል፡፡ ከዚህ ውጭ ግን መላው የአማራ ሕዝብ በወራሪ ጠላት እና በቆማሪ መንግሥት መሃከል ወድቆ እየዋተተ ባለበት ሁኔታ፣ ፋኖ ላይ የሚወሰድ እርምጃ፣ የሥልጣን ስጋት ከመሆን አልፎ ለባለሥልጣናት ምቾት የሚፈጥር ስላልሆነ የክልሉ መንግሥት ችግሩን በውይይት እንዲፈታው እንመክራለን፡፡

ሰውየው... አሸባሪው ሃይል በአማራና አፋር ክልሎች ላይ ከፈጸመው ውድመት ላይ ከአሜሪካ መንግሥት የ10.2 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ለክልሉ ሸምቶ በኢትዮጵያ ፍርሰት ላይ አዲስ አገረ መንግሥት እየገነባ ነው። እኔ እምለው ግን... ➔እንዴት አንድ እንኳን ታግሎ የሚያታግል ፓርቲ ጠፋ? ➔አንድ እንኳን የቁርጥ ቀን ልጅ እንዴት አገሩ ላይ ጠፋ? ➔አማካሪውም፣ ሚኒስትሩም፣ ተቃዋሚውም፣ ሙሕሩም፣ ሼህና ቄሶቹም "እኔ ምን አገባኝ" ብለው በአንድ ሰው ውሳኔ ኢትዮጵያ ትፈርስ ዘንድ እንዴት ወሰኑባት?

ከሄዊ መግለጫ ውስጥ "ፋሽሽቱ ዐቢይ" የሚለው መጠሪያ ተፍቆ በአወል አርባ መተካቱን ስታይ አፋር የተወረረው በመንግሥት እውቅና መሆኑን ትረዳለህ። ዋነኛ እቅዳቸውም ፕሬዝዳንት ሃጂ አወል አርባን በማስወገድ በኦነጋዊ አስተምህሮ የተጠመቀ መሪ ማምጣት ነበር

ውሳኔ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔በሆዳሞች ፈንታ ልባሞች የሚመሩት... ➔ለቤተሰብ ሳይሆን ለሕዝብ ተጠቃሚነት የሚታገል... ➔ከአማራነት ከፍም ዝቅም የማይል... ➔በድርጅቱ ፈንታ ለሕዝብ አሸናፊነት የሚተጋ... ➔ምክር ቤት ብቻ ሳይሆን ለሕዝብ ሲል እስር ቤትም ሆነ መቃብር ቤት ለመግባት የማያመነታ.... ➔ቪላ ሳይሆን ታሪክ ለመሥራት የሚመኝ... ➔ሥልጣን ላይ ያሉትን አሳሞችም ሆነ እኒህኞቹን ሸለመጥማጦች የሚተካ.... ብርቱ የፖለቲካ ድርጅት ያስፈልገናል። አይመስላችሁም? መልሳችሁ አዎ ከሆነ Share አድርጉት‼️

በአገሩ የማይደራደረውንና ጀግናውን የአፋር ሕዝብ "የምድር ድሮኖች" በሚል ድለላ በከባድ መሣሪያ ማስጨፍጨፍ ተገቢነት የለውም። የአፋርን አገራዊ ስሜትና አይበገሬነት ለማዳከም ታስቦ እየተደረገ ያለውን መንግሥታዊ ሸፍጥ እቃወማለሁ!!

"እነዚህ ሰዎች የሰኔ 15ቱን ጣጣ በድጋሜ ያመጡብናል" የሚል ሥጋት የሚሰማቸው አካላት የሰኔ 15ቱን ግድያ መድገም የሚሹ ናቸው። "ማን ስለሆኑ ነው ይህ ሁሉ ጥበቃ ያስፈለጋቸው?" ብለው የሚበሳጩትም
"እነዚህ ሰዎች የሰኔ 15ቱን ጣጣ በድጋሜ ያመጡብናል" የሚል ሥጋት የሚሰማቸው አካላት የሰኔ 15ቱን ግድያ መድገም የሚሹ ናቸው። "ማን ስለሆኑ ነው ይህ ሁሉ ጥበቃ ያስፈለጋቸው?" ብለው የሚበሳጩትም የሚያሳድዷቸው ናቸው። በተረፈ መጭው ጊዜ የአማራ ሕዝብ የሚፈተንበት እንደመሆኑ መጠን በሁሉም ስፍራ የሚጠብቁንና የምንጠብቃቸው ጀግኖች ማፍራት ግድ ይለናል‼️

እሚገርም መንግሥት አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ እሚገርም መንግሥት- ቅጥ አንባር የጠፋው ወንበር ተረክቦ- አገሩ የሰፋው ሕዝብ ተሸክሞት-ድካም የሚሰማው ከአንገት በላይ እርግብ- ከአንገት በታች እባብ ‹‹ኑ
እሚገርም መንግሥት አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ እሚገርም መንግሥት- ቅጥ አንባር የጠፋው ወንበር ተረክቦ- አገሩ የሰፋው ሕዝብ ተሸክሞት-ድካም የሚሰማው ከአንገት በላይ እርግብ- ከአንገት በታች እባብ ‹‹ኑ እንብረር›› እያለ- በሆዱ የሚሳብ ባሕሪው የአራስ ሴት፣ መልኩ የእስስት ቆዳ ወገን ሲሉት ጠላት- ዘመድ ሲሉት ባዳ ደማከሴ ሳለ- አንካሴ እያነሳ- ደጀን የሚጎዳ፡፡ የሚገርም መንግሥት… ጥርስ ያወጣል ሲሉት- እግሩ ጠና ሲባል አቅም የቸረውን- በአዚሙ የሚጥል ወንበሩ ላይ ቆራጥ- አገሩ ላይ ሰነፍ ድልን አኮላሽቶ- ትግል የሚያስታቅፍ፤ እሚገርም መንግሥት- መላ ቅጥ የሌለው እንደ ባላንጋራ- ባንድራ የሚያስቆጣው ምላሱ ኢትዮጵያዊ - ቃላቱ የዜጋ መዳፉ አገር አጥፊ- ድርጊቱ የመንጋ ልማት ሲሉት ግጭት- ቀኝ ሲሉት ግራ ጠላት ተሸክመው- አፋርና አማራ የአገሬውን ትግል- ድል ብሎ የሚጠራ ፍትሕን ሊያስከብር- ተሹሞ እንደ ዳኛ፤ ደጺን ሊቆጣጠር- ጌታቸውን ሊያስር- ባወጣው ማደኛ፤ ምህረት የሚለግስ- ለጦር ወንጀለኛ፡፡ እሚገርም መንግሥት- አመሉ የሚደንቅ ሕዝብ ኀዘኑን ውጦ- ሲታገል ሰንብቶ- ለመጨረሻው ሳቅ በተኩሱ መሃከል- በትግሉ እኩሌታ፤ ድል አርገናል ብሎ- ለአገሩ የሚጋብዝ- የአቦይን ፈገግታ፡፡ እሚገርም መንግሥት…

አቢይ መራሹ የሽመልስ አብዲሳ መንግሥት ሲፈልግ እልፍ አእላፍ ንጹሐን የጨፈጨፈ ነፍሰ በላን "እጁን ሰጠ" በሚል ዜና ቤትና መኪና ሲሸልመው ታገኘዋለህ። በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ታምራት ነገራ አይነት
አቢይ መራሹ የሽመልስ አብዲሳ መንግሥት ሲፈልግ እልፍ አእላፍ ንጹሐን የጨፈጨፈ ነፍሰ በላን "እጁን ሰጠ" በሚል ዜና ቤትና መኪና ሲሸልመው ታገኘዋለህ። በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ታምራት ነገራ አይነት አገር ወዳዶችን በጥብቅ ከሚፈለጉ ወንጀለኞች ተርታ መድቦ ግፍ ሲፈጽምባቸው ታያለህ! ፍትሕን እንደ እነሱ የቀለደባት አለ እንዴ?

በመንግሥት አካላት ተገቢነት የሌለው ድርጊት ሲፈጸም የኢሳት እለታዊዎች የተለመደ መርሐ ግብር፦ ▬▬▬▬▬▬ በመጀመሪያ ፕሮግራማቸው፦ ጥፋቱን አውግዘው በአንዳንድ የመንግሥት አካላት በተፈጸመው ድርጊት
በመንግሥት አካላት ተገቢነት የሌለው ድርጊት ሲፈጸም የኢሳት እለታዊዎች የተለመደ መርሐ ግብር፦ ▬▬▬▬▬▬ በመጀመሪያ ፕሮግራማቸው፦ ጥፋቱን አውግዘው በአንዳንድ የመንግሥት አካላት በተፈጸመው ድርጊት ማዘናቸውን ከገለጹ በኋላ መንግሥት ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ይመክራሉ፤ በቀጣዩ ቀን፦ ጥፋቱን የፈጸሙትን የመንግሥት አካላት መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመንግሥት ጋር ሆኖ ሊታገላቸው እንደሚገባ ያሳስባሉ። በሦስተኛው ቀን፦ከአንዳንድ አካባቢዎች እየተሰማ ያለው ጩኸት የመንግሥት አካላት ከፈጸሙት ጥፋት መብለጡን ከተናገሩ በኋላ ተጠቂውን አካል አውግዘው ፕሮግራማቸውን ይቋጫሉ። 😁

የእነ ዲያቆን ዳንኤልን የቁጣ ድምጽ የምትሰማው "ታቦት ወደ መቅደሱ አይገባም" ተብሎ ሲመለስና የምዕመናን ደም ሲፈስስ ሳይሆን "ወደ ቤተ-መንግሥት አትገባም" ተብሎ ከአራት ኪሎ በር ላይ ሲመለስ ብቻ ነው።

የአማራ ሕዝብ በማያባራ መከራ ውስጥ እንዲኖር የፈረዱበት ብአዴኖችና ከእራሱ ሆድ የወጡ ሆዳሞች እንደሆኑት ሁሉ ቤተክርስቲያኗንም ለዚህ አይነት ግፍ የዳረጋት የእራሷ ሲኖዶስና የእራሷ ሆዳም አገልጋዮች ናቸው።

የመንግሥት ታጣቂዎች ታቦት በሚያስገቡ ምዕመናን ላይ ያለምንም ምክንያት በተኮሱት ጥይት ቆስለው ወደ አለርት ሆስፒታል ከተወሰዱ አራት ዜጎች መሀከል ሁለቱ አርፈዋል። አምላክ ነፍሳቸውን ይማረው።

ባሁኑ ሰዓት በፖለቲከኞች ሳይታዘዝ በእራሱ ስሜት ተገፋፍቶ የመጅሊስ አጥር የሚያፈርስም ሆነ ሙስሊሞችን የሚተናኮስ ክርስቲያን... ወይም ደግሞ... የቤተ-ክርስቲያን ሕንፃ ላይ እሳት የሚለኩስም ሆነ "ታቦት ወደ ደብሩ አይገባም" ብሎ የሚመልስ ሙስሊም ኢትዮጵያ ውስጥ የለም። እነዚሁ ሁሉ ድርጊቶች እኩልነትን እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ፈንታ ሕዝብን በእምነት ወይም በማንነት በማበጣበጥ ሥልጣናቸውን ማስቀጠል የሚሹ አምላክ እና አገር አልባ ዋልጌ ፖለቲከኞች የሚያቀነባብሯቸው ናቸው።

የወሎ አማራን 'ጠላቴ' ብለው ሲገድሉትና ሲያፈናቅሉት በከረሙት አሸባሪዎች ፈንታ ወሎን 'ወገኔ' ብሎ ለተፈናቀለው እህሉን፣ ለተወረረው ፋኖውን ሲልክ በከረመው ሕዝብ ቂም የያዙ ቅጥረኞች... ጀግኖች
+5
የወሎ አማራን 'ጠላቴ' ብለው ሲገድሉትና ሲያፈናቅሉት በከረሙት አሸባሪዎች ፈንታ ወሎን 'ወገኔ' ብሎ ለተፈናቀለው እህሉን፣ ለተወረረው ፋኖውን ሲልክ በከረመው ሕዝብ ቂም የያዙ ቅጥረኞች... ጀግኖች ነፃ ካወጡት ከተማ ውስጥ ተወዝፈው በፈጠራ ወሬ ባሕር ዳርን ለማተራመስ ያደረጉት ሙከራ ከሽፏል። ለወደፊቱም ቢሆን እንደየ ሃይማኖቱ ለአምላኩ ከሰገደ በኋላ ቤተ እምነቱን ሊያረክስና ደሙን ሊያፈስስ ከመጣው የጋራ ጠ.ላቱ ጋር በአማራነቱ ተደራጅቶ የሞት ሽረት ትግል ሲያደርግ የከረመውን ፋኖ በፈጠራ ወሬ ቀርቶ በየትኛውም ድርጊት ትጥቁን ማስፈታትም ሆነ አማራን በእምነትና ጎጥ ከፋፍሎ ለጅብ መስጠት የሚሳካ አይደለም። ምክንያቱም በመከራ ውስጥ ወድቆ የከረመው የአማራ ሕዝብ አጥፊውን እና አዳኙን ለይቶ ከመቸውም ጊዜ በላይ አንድነቱን አጠናክሯል። ይሄው ነው!

"በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት የሚደረገው ትግል በድል እያንበሻበሸን ነው" የሚል ዜና በየቀኑ ሲቀርብ "ድሌን አትሻሙኝ" እንጂ "የጋራ ድሉን ለብቻዬ አታሸክሙኝ" ሲባል አልሰማንም። "አቦይን በቁጥጥር ስር ያዋለ መሪ" የሚል ሙገሳ ሲጎርፍለት ገድሉን ለሚመራቸው ሚኒስትሮች አላከፋፈለም። "እነ አቦይን እንዴት ትፈታለህ?" የሚል ክስ ሲቀርብበት ግን አንድን ጥፋት በጋራ በመስራት ወደ ልማት መቀየር ይቻል ይመስል ሚኒስትሮቹን ሁሉ የክሱ ተቋዳሽ አደረጋቸው። 😁

ረ/ፕሮፌሰር በለጠ ሞላ እና ፕሮፌሰር ብርሐኑ "እነ አቦይን እንፍታቸው" ሲባሉ "እምቢየው" ብለው ውሳኔውን ባለማስቀረታቸው እየተወቀሱ ነው😁 ጥፋትህን ለሚኒስትሮች በማከፋፈል እራስሀህን ነፃ ለማውጣት አትሞክር በሉልኝ!