Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 336 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 651,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 347 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 336 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -104,过去 24 小时变化为 -8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 158 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 336
订阅者
-824 小时
-327 天
-10430 天
帖子存档
14 336
እቅዳቸው እና መፍትሔው
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬▬
እቅዳቸው
➔በአብዛኛው የአማራ ምድር ላይ የተፈጸመውን ውድመት ከጥቃቱ ለተረፉ አካባቢዎች ማጋራት፤
➔ልክ እንደ ሰኔ 15ቱ ጥቃት አጥቂ እና ተጠቂን በዞን ሸንሽኖ መላው ሕዝባችንን ከጫማቸው ስር መሸርኮት፤
➔አማራን ውጥረት ውስጥ ከከተቱ በኋላ መሃል መንገድ ላይ የተቋረጠውን ዘመቻ ግልጽ በሆነ መልኩ ወደ ጠረጴዛ አምጥቶ ‹‹ወራሪው በሠራው ወንጀል አማራው ካሳ ይክፈል›› የሚል ውሳኔ ማስተላለፍ፤
➔ሕዝብን ከወራሪ ጠላት ሊታደግ የወጣውን ፋኖ አክስሞ ለካድሬ ወንበር የሚያደገድገውን ማደራጀት፤
ይህ የጥፋት ድግስ ዒላማውንም ሆነ ዓላማውን እንዳያሳካ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል?
▬▬▬▬▬▬▬▬
➔‹‹እርስ በእርስ ይጠፋፉበት›› ተብሎ የተሰጠንን ሤራ ወደ ውይይት አምጥተን ችግሩን በንግግር መፍታት፤
➔ለዞን ክፍፍል የሚዳርገውን እና የተበጣጠሰውን የፋኖ አደረጃጀት በአማራዊ ማዕቀፍ ውስጥ የሚያስተሳስር መዋቅር መዘርጋት፤
➔ጸረ አማራዎች በየትኛውም ስፍራ በሚኖረው አማራ ላይ ለሚፈጽሙት ጥቃት ዞናዊ እውቅና ሰጥተን እራሳችንን ለጥቃት በመዳረግ ፈንታ በአንድነት ቆመን ያነጣጠረብንን አፈሙዝ መመከት፤
➔የአማራን አንድነትና ሰላም ከማስከበር ይልቅ ሕዝብን በዞን በመለያየት አማራን ማስበላት የሚሹ ኃይሎችን ከጉያችን ነጥለን ማውጣት፤
➔ሕዝባችንን ለመጉዳት ሃያ አራት ሰዓት እንቅልፍ አጥተው በሚራወጡ ውጫዊ ሃይሎች ፈንታ፤ ሃያ አራት ሰዓት እንቅልፋቸውን የሚለጥጡና ሕዝባቸውን አሳልፈው የሚሰጡ አመራሮችን እና ፖለቲከኞችን ‹‹ለሚደርሰው ነገር ሁሉ ተጠያቂው እናንተ ናችሁ›› የሚል ሃላፊነት መስጠት፤
➔በእኛ ድክመት የተሰው ጀግኖችን ፎቶ ለጥፈን ከመነፋረቅ ይልቅ በሕይወት ያሉ ጀግኖችን መጠበቅ እንደሚጠቅም መረዳት፤
Share
14 336
ከአብዛኛው የአማራ ዲያስፖራ በሚያገኘው የዶላር እርጥባን እየተንቀሳቀሰ፣ በአገር ሥም የወንበር አገልጋይ ሆኖ፣ ያለምንም ቀይ መስመር በሚጓዙ ደላሎቹ አማካኝነት... የወገንን እልቂት፣ የመንግሥትን ክሕደት እና የአገራችንን ፍርሰት ከሚያለማምደን "የኢሳት ሚዲያ" ይልቅ ግልጽ በሆነ መልኩ ወጥተው የጥፋት ቅስቀሳ የሚያካሂዱብን ሚዲያዎች ምስጉኖች ናቸው።
14 336
ደጺ ከመንግሥት ጋር እያተደረገ ባለው ቀጥተኛ ያልሆን ንግግር የተወሰነ ውጤት መታየቱን ለቢቢሲ ገልጿል። ይህ ውጤት "አፋርን እንዲወጋ አመቻቹልኝ" ወይም ደግሞ "ኢመደበኛውን ፋኖ አጥፉልኝ" ከሚል ጥያቄ የተገኘ ይሆን? 😁
14 336
እኔ እምለው
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ባሳለፍነው ዘመን
አማራን ከጥቃት ፥ ለማዳን የለፉ፤
በወስላቶች ችሎት
"ስጋቶች" ተብለው ፥ አይተናል ሲጠፉ።
እናም...
ቀራንዮ ታዛ
የለንጊኖስን ጦር ፥ በጨበጠ ዳኛ
ሐቀኛው ነውና
ተወግቶ የሚሞት ፥ እንደ ወንጀለኛ፤
ማደኛው ሳይፃፍ፥ ፍርዱ ሳይፈጸም
ፋይሉ ይቅረብና ፥ ፈራጁን እንገምግም።
14 336
ሸኔን በሪፖርት፣ ፋኖን በጥይት አይሆንም!
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
አራዳው ብልጽግና በሥሙ ሲጠሩት ‹‹አቤት›› ባይ አመራር የሌለው የሽብር ድርጅት እውን አድርጎ የንጹሐንን ሐብትና ሕይወት ሲያስወድም ከረመ፡፡
ከሰሞኑም ከጌጃው ብልጽግና ጋር ባደረገው ስብሰባ ፋኖን ከመምታት በፊት ሸኔን ደምስሻለሁ ማለት እንደሚቀድም ተረድቶ በታጣቂው ፈንታ ተጠቂው ላይ በወሰደው እርምጃ የቀማቸውን መሣሪያዎች ሲያሳየን ነበር፡፡ ከእነዚህም መሣሪያዎች መሃከል አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ማንገቻ ያለው ቁመህ ጠብቀኝ ጠመንጃ ቀላቅሎ ‹‹ከሸኔ ያስፈታኋቸው ናቸው›› እያለ ሲነግረን ነበር፡፡ ከዚህ ባለፈም ‹‹21 የሸኔ ታጣቂዎች እጅ ሰጡ›› በሚል ዜና 28 መንገደኞችን የያዘ ፎቶ ለጥፎ ‹‹ሰባቱ እግር የሰጡ ናቸው ወይ?›› የሚል ትችት ሲያስተናግድ ነበር፡፡
ያ ሁሉ ልፋት ታዲያ፣ አሸባሪው ሃይል አፋር ገብቶ ቅልጥ ያለ ትግል እያደረገ ባለበት ሁኔታ ‹‹ድል አድርጌያለሁ›› ብሎ የተመለሰው አካል፣ ፋኖን መትቶ አማራን ለዳግም ጥቃትና ለባርነት ከመዳረግ የሚመነጭ ነው፡፡ ኦነግ በሪፖርት ሲደመሰስ የከረመው የፋኖን ደም በጥይት ለማፍሰስ ነው፡፡ ኢ-መደበኛ ሃይል የተባሉት አሁንም ድረስ ሕያው ሆነው የንጹሐንን ሕይወት በመቅጠፍ ላይ የሚገኙት አሸባሪዎች ሳይሆኑ ‹‹የመጣብህ ጠላት በመደበኛው የጸጥታ ሃይል የሚመከት ስላልሆነ ተነስና ለህልውናህ ታገል›› በሚል የክተት ጥሪ በእራሱ ስንቅና ትጥቅ ሲዋጋ የከረመው ፋኖ ነው፡፡
የሆነው ሆኖ ግን
ፋኖ ላይ ጣትን ከመቀሰር በፊት ድል በሚል ሥም መሃል መንገድ ላይ የተቋረጠውን ትግል መቋጨት ያስፈልጋል፡፡
ለህልውናው የሚታገለውን ፋኖ ለማጥቃት ከማሰብ አስቀድሞም የንጹሐንን ሕልውና ሲነጥቅ ከርሞ በሪፖርት የተደመሰሰው አሻባሪ ላይ ተጨባጭ እርምጃ መውሰድ ግድ ይላል፡፡
ያን ጊዜ ኢመደበኛውም ሆነ መደበኛው ፋኖ እርምጃ ሳትወስዱበት በፊት ነፍጡን ጥሎ ማረሻውን እና ደብተሩን ያነሳል፡፡
ከዚህ ውጭ ግን መላው የአማራ ሕዝብ በወራሪ ጠላት እና በቆማሪ መንግሥት መሃከል ወድቆ እየዋተተ ባለበት ሁኔታ፣ ፋኖ ላይ የሚወሰድ እርምጃ፣ የሥልጣን ስጋት ከመሆን አልፎ ለባለሥልጣናት ምቾት የሚፈጥር ስላልሆነ የክልሉ መንግሥት ችግሩን በውይይት እንዲፈታው እንመክራለን፡፡
14 336
ሰውየው... አሸባሪው ሃይል በአማራና አፋር ክልሎች ላይ ከፈጸመው ውድመት ላይ ከአሜሪካ መንግሥት የ10.2 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ለክልሉ ሸምቶ በኢትዮጵያ ፍርሰት ላይ አዲስ አገረ መንግሥት እየገነባ ነው።
እኔ እምለው ግን...
➔እንዴት አንድ እንኳን ታግሎ የሚያታግል ፓርቲ ጠፋ?
➔አንድ እንኳን የቁርጥ ቀን ልጅ እንዴት አገሩ ላይ ጠፋ?
➔አማካሪውም፣ ሚኒስትሩም፣ ተቃዋሚውም፣ ሙሕሩም፣ ሼህና ቄሶቹም "እኔ ምን አገባኝ" ብለው በአንድ ሰው ውሳኔ ኢትዮጵያ ትፈርስ ዘንድ እንዴት ወሰኑባት?
14 336
ከሄዊ መግለጫ ውስጥ "ፋሽሽቱ ዐቢይ" የሚለው መጠሪያ ተፍቆ በአወል አርባ መተካቱን ስታይ አፋር የተወረረው በመንግሥት እውቅና መሆኑን ትረዳለህ። ዋነኛ እቅዳቸውም ፕሬዝዳንት ሃጂ አወል አርባን በማስወገድ በኦነጋዊ አስተምህሮ የተጠመቀ መሪ ማምጣት ነበር
14 336
ውሳኔ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔በሆዳሞች ፈንታ ልባሞች የሚመሩት...
➔ለቤተሰብ ሳይሆን ለሕዝብ ተጠቃሚነት የሚታገል...
➔ከአማራነት ከፍም ዝቅም የማይል...
➔በድርጅቱ ፈንታ ለሕዝብ አሸናፊነት የሚተጋ...
➔ምክር ቤት ብቻ ሳይሆን ለሕዝብ ሲል እስር ቤትም ሆነ መቃብር ቤት ለመግባት የማያመነታ....
➔ቪላ ሳይሆን ታሪክ ለመሥራት የሚመኝ...
➔ሥልጣን ላይ ያሉትን አሳሞችም ሆነ እኒህኞቹን ሸለመጥማጦች የሚተካ.... ብርቱ የፖለቲካ ድርጅት ያስፈልገናል።
አይመስላችሁም?
መልሳችሁ አዎ ከሆነ Share አድርጉት‼️
14 336
በአገሩ የማይደራደረውንና ጀግናውን የአፋር ሕዝብ "የምድር ድሮኖች" በሚል ድለላ በከባድ መሣሪያ ማስጨፍጨፍ ተገቢነት የለውም። የአፋርን አገራዊ ስሜትና አይበገሬነት ለማዳከም ታስቦ እየተደረገ ያለውን መንግሥታዊ ሸፍጥ እቃወማለሁ!!
14 336
"እነዚህ ሰዎች የሰኔ 15ቱን ጣጣ በድጋሜ ያመጡብናል" የሚል ሥጋት የሚሰማቸው አካላት የሰኔ 15ቱን ግድያ መድገም የሚሹ ናቸው። "ማን ስለሆኑ ነው ይህ ሁሉ ጥበቃ ያስፈለጋቸው?" ብለው የሚበሳጩትም የሚያሳድዷቸው ናቸው።
በተረፈ መጭው ጊዜ የአማራ ሕዝብ የሚፈተንበት እንደመሆኑ መጠን በሁሉም ስፍራ የሚጠብቁንና የምንጠብቃቸው ጀግኖች ማፍራት ግድ ይለናል‼️
14 336
እሚገርም መንግሥት
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
እሚገርም መንግሥት- ቅጥ አንባር የጠፋው
ወንበር ተረክቦ- አገሩ የሰፋው
ሕዝብ ተሸክሞት-ድካም የሚሰማው
ከአንገት በላይ እርግብ- ከአንገት በታች እባብ
‹‹ኑ እንብረር›› እያለ- በሆዱ የሚሳብ
ባሕሪው የአራስ ሴት፣ መልኩ የእስስት ቆዳ
ወገን ሲሉት ጠላት- ዘመድ ሲሉት ባዳ
ደማከሴ ሳለ- አንካሴ እያነሳ- ደጀን የሚጎዳ፡፡
የሚገርም መንግሥት…
ጥርስ ያወጣል ሲሉት- እግሩ ጠና ሲባል
አቅም የቸረውን- በአዚሙ የሚጥል
ወንበሩ ላይ ቆራጥ- አገሩ ላይ ሰነፍ
ድልን አኮላሽቶ- ትግል የሚያስታቅፍ፤
እሚገርም መንግሥት- መላ ቅጥ የሌለው
እንደ ባላንጋራ- ባንድራ የሚያስቆጣው
ምላሱ ኢትዮጵያዊ - ቃላቱ የዜጋ
መዳፉ አገር አጥፊ- ድርጊቱ የመንጋ
ልማት ሲሉት ግጭት- ቀኝ ሲሉት ግራ
ጠላት ተሸክመው- አፋርና አማራ
የአገሬውን ትግል- ድል ብሎ የሚጠራ
ፍትሕን ሊያስከብር- ተሹሞ እንደ ዳኛ፤
ደጺን ሊቆጣጠር-
ጌታቸውን ሊያስር- ባወጣው ማደኛ፤
ምህረት የሚለግስ- ለጦር ወንጀለኛ፡፡
እሚገርም መንግሥት- አመሉ የሚደንቅ
ሕዝብ ኀዘኑን ውጦ-
ሲታገል ሰንብቶ- ለመጨረሻው ሳቅ
በተኩሱ መሃከል- በትግሉ እኩሌታ፤
ድል አርገናል ብሎ-
ለአገሩ የሚጋብዝ- የአቦይን ፈገግታ፡፡
እሚገርም መንግሥት…
14 336
አቢይ መራሹ የሽመልስ አብዲሳ መንግሥት ሲፈልግ እልፍ አእላፍ ንጹሐን የጨፈጨፈ ነፍሰ በላን "እጁን ሰጠ" በሚል ዜና ቤትና መኪና ሲሸልመው ታገኘዋለህ።
በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ታምራት ነገራ አይነት አገር ወዳዶችን በጥብቅ ከሚፈለጉ ወንጀለኞች ተርታ መድቦ ግፍ ሲፈጽምባቸው ታያለህ!
ፍትሕን እንደ እነሱ የቀለደባት አለ እንዴ?
14 336
በመንግሥት አካላት ተገቢነት የሌለው ድርጊት ሲፈጸም የኢሳት እለታዊዎች የተለመደ መርሐ ግብር፦
▬▬▬▬▬▬
በመጀመሪያ ፕሮግራማቸው፦ ጥፋቱን አውግዘው በአንዳንድ የመንግሥት አካላት በተፈጸመው ድርጊት ማዘናቸውን ከገለጹ በኋላ መንግሥት ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ይመክራሉ፤
በቀጣዩ ቀን፦ ጥፋቱን የፈጸሙትን የመንግሥት አካላት መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመንግሥት ጋር ሆኖ ሊታገላቸው እንደሚገባ ያሳስባሉ።
በሦስተኛው ቀን፦ከአንዳንድ አካባቢዎች እየተሰማ ያለው ጩኸት የመንግሥት አካላት ከፈጸሙት ጥፋት መብለጡን ከተናገሩ በኋላ ተጠቂውን አካል አውግዘው ፕሮግራማቸውን ይቋጫሉ። 😁
14 336
የእነ ዲያቆን ዳንኤልን የቁጣ ድምጽ የምትሰማው "ታቦት ወደ መቅደሱ አይገባም" ተብሎ ሲመለስና የምዕመናን ደም ሲፈስስ ሳይሆን "ወደ ቤተ-መንግሥት አትገባም" ተብሎ ከአራት ኪሎ በር ላይ ሲመለስ ብቻ ነው።
14 336
የአማራ ሕዝብ በማያባራ መከራ ውስጥ እንዲኖር የፈረዱበት ብአዴኖችና ከእራሱ ሆድ የወጡ ሆዳሞች እንደሆኑት ሁሉ ቤተክርስቲያኗንም ለዚህ አይነት ግፍ የዳረጋት የእራሷ ሲኖዶስና የእራሷ ሆዳም አገልጋዮች ናቸው።
14 336
የመንግሥት ታጣቂዎች ታቦት በሚያስገቡ ምዕመናን ላይ ያለምንም ምክንያት በተኮሱት ጥይት ቆስለው ወደ አለርት ሆስፒታል ከተወሰዱ አራት ዜጎች መሀከል ሁለቱ አርፈዋል። አምላክ ነፍሳቸውን ይማረው።
14 336
ባሁኑ ሰዓት በፖለቲከኞች ሳይታዘዝ በእራሱ ስሜት ተገፋፍቶ የመጅሊስ አጥር የሚያፈርስም ሆነ ሙስሊሞችን የሚተናኮስ ክርስቲያን...
ወይም ደግሞ...
የቤተ-ክርስቲያን ሕንፃ ላይ እሳት የሚለኩስም ሆነ "ታቦት ወደ ደብሩ አይገባም" ብሎ የሚመልስ ሙስሊም ኢትዮጵያ ውስጥ የለም።
እነዚሁ ሁሉ ድርጊቶች እኩልነትን እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ፈንታ ሕዝብን በእምነት ወይም በማንነት በማበጣበጥ ሥልጣናቸውን ማስቀጠል የሚሹ አምላክ እና አገር አልባ ዋልጌ ፖለቲከኞች የሚያቀነባብሯቸው ናቸው።
14 336
የወሎ አማራን 'ጠላቴ' ብለው ሲገድሉትና ሲያፈናቅሉት በከረሙት አሸባሪዎች ፈንታ ወሎን 'ወገኔ' ብሎ ለተፈናቀለው እህሉን፣ ለተወረረው ፋኖውን ሲልክ በከረመው ሕዝብ ቂም የያዙ ቅጥረኞች... ጀግኖች ነፃ ካወጡት ከተማ ውስጥ ተወዝፈው በፈጠራ ወሬ ባሕር ዳርን ለማተራመስ ያደረጉት ሙከራ ከሽፏል።
ለወደፊቱም ቢሆን እንደየ ሃይማኖቱ ለአምላኩ ከሰገደ በኋላ ቤተ እምነቱን ሊያረክስና ደሙን ሊያፈስስ ከመጣው የጋራ ጠ.ላቱ ጋር በአማራነቱ ተደራጅቶ የሞት ሽረት ትግል ሲያደርግ የከረመውን ፋኖ በፈጠራ ወሬ ቀርቶ በየትኛውም ድርጊት ትጥቁን ማስፈታትም ሆነ አማራን በእምነትና ጎጥ ከፋፍሎ ለጅብ መስጠት የሚሳካ አይደለም።
ምክንያቱም በመከራ ውስጥ ወድቆ የከረመው የአማራ ሕዝብ አጥፊውን እና አዳኙን ለይቶ ከመቸውም ጊዜ በላይ አንድነቱን አጠናክሯል።
ይሄው ነው!
14 336
"በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት የሚደረገው ትግል በድል እያንበሻበሸን ነው" የሚል ዜና በየቀኑ ሲቀርብ "ድሌን አትሻሙኝ" እንጂ "የጋራ ድሉን ለብቻዬ አታሸክሙኝ" ሲባል አልሰማንም።
"አቦይን በቁጥጥር ስር ያዋለ መሪ" የሚል ሙገሳ ሲጎርፍለት ገድሉን ለሚመራቸው ሚኒስትሮች አላከፋፈለም።
"እነ አቦይን እንዴት ትፈታለህ?" የሚል ክስ ሲቀርብበት ግን አንድን ጥፋት በጋራ በመስራት ወደ ልማት መቀየር ይቻል ይመስል ሚኒስትሮቹን ሁሉ የክሱ ተቋዳሽ አደረጋቸው። 😁
14 336
ረ/ፕሮፌሰር በለጠ ሞላ እና ፕሮፌሰር ብርሐኑ "እነ አቦይን እንፍታቸው" ሲባሉ "እምቢየው" ብለው ውሳኔውን ባለማስቀረታቸው እየተወቀሱ ነው😁 ጥፋትህን ለሚኒስትሮች በማከፋፈል እራስሀህን ነፃ ለማውጣት አትሞክር በሉልኝ!
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
