Joseph Math Tutor
Kanalga Telegram’da o‘tish
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
Ko'proq ko'rsatish1 857
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+57 kunlar
+2130 kunlar
Postlar arxiv
1 856
#URGENT_Notice
በAASTU (Addis Ababa Science and Technology University) እና በASTU (Adama Science and Technology University) በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ ትምህርት ዘርፍ ለመማር የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ከፈተናው ጋር እንድትተዋወቁ ለማድረግ የDemo Exam ስለተዘጋጀላችሁ ስትሞሉ በመረጣችሁት መፈተኛ ጣቢያ በመሄድ ዛሬ መስከረም 19 ከ9:00 ሰዓት ጀምሮ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርስቲዎቹ ገልጸዋል።
📌AASTU ወይም ASTU ለመግባት
ላሰቡ ተማሪዎች share አድርጉ::
1 856
እንኳን አደረሳችሁ
ዛሬ እንደሚታወቀው የመስቀል በዓልን እያከበርን ነው። እናም ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁንና ሁላችንም በቤታችን እያከበርን ነው ኖረንም አልኖረንም ተሰባስበን እያከበርን ነው። ነገር ግን በዚህ ሰዓት ምንም ደጋፊ የሌላቸው ወገኖቻችን አሉ ምን በላችሁ? ምን ጠጣችሁ? ምን ለበሳችሁ? ብሎ የሚጠይቃቸው ወገን የሌላቸው አሉ እናም ሰሞኑን ያቋቋምነው #Charity ለዚህ ጊዜ የሚሆን ነው። እኛ ካለን ብር አሰባስበን ወስደን ስናግዛቸው የሚሰማቸው ደስታ እና ተስፋ ለካስ ሰው አለኝ የሚል ስሜት አስቡት እስቲ?!
በዚህ ዓመት ከመስከረም 30 ጀምሮ በየወሩ እየሰበሰብን አቅመ ደካማዎችን ልንረዳ ዝግጅታችንን ጨርሰናል እስካሁንም ከ40 በላይ ሰው ተመዝግቧል።
የምንረዳው ለሁሉም ነው እምነት ዘር ቀለም ሳንለይ Charity ውስጥም ሁሉም ሰው መሳተፍ ይችላል።
ለመመዝገብ የሚያስፈልገው ቅን ልብ ብቻ ነው። እኔ መቼ ራሴን ቻልኩና፤ መቼ ከቤተሰብ ተላቀኩና ፤ ከየት አምጥቼ ነው የምረዳው የሚሉ የሰነፍ ሰው ሀሳቦችን አስወግዱ ለመርዳት ከታሰበ ቀላል ነው ደግሞም የሚረዳው በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በሀሳብም ነው።
"ለችግረኛ የሚያስብ ብጹዕ ነው"
መዝ 40÷1
መልካም በዓል
1 856
#ASTU/AASTU
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብታችሁ በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለመማር ለተመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ማክሰኞ መስከረም 20/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
➫ ተፈታኞች ለፈተናው መመዝገባችሁን የሚገልፅ ከሲስተም ላይ በማወረድ ፕሪንት አድርጋችሁ መያዝ ያስፈልጋል፡፡
➫ ተፈታኞች ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያና የአድሚሽን ካርዳችሁን በመያዝ በምዝገባ ወቅት በመረጣችሁት የፈተና ማዕከል ከተጠቀሰው ሰዓት ቀደም ብላችሁ መገኘት አለባችው፡፡
➫ ተፈታኞች ሞባይል ስልክ እና ስማርት ሰዓት ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መምጣት የተከለከለ ነው፡፡
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
