cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

FIDEL POST NEWS

Fast news about Ethiopia

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
14 472
Obunachilar
+6724 soatlar
+3367 kunlar
+2 00030 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

በአዲስ አበባ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ መፀዳጃ  ቤት ውስጥ እርድ ሲከናወን ተገኘ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ከወረዳ እስከ ማዕከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ከ805 በላይ የሚሆኑ ተቋማት ላይ የቁጥጥር ስር መስራቱን አስታውቋል።በዚህም ባለስልጣኑ ባከናወነው የቁጥጥር ስራ ለ251 ተቋማት የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ ሶስት ድርጅቶችን ማሸጉን አስታውቋል። ከታሸጉት  ተቋማት ውስጥ አንዱ  በፆም ወቅት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ህግ እና ደንብ በማይፈቅድ መልኩ መፀዳጃ ቤት ውስጥ በግ እና ፍየል እርድ ሲያከናውን መያዙ ተገልፆል፡፡ በተጨማሪም የባለስልጣኑ የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖራቸው ፅዳቱን ያልጠበቀ ዶሮዎች ለሱፐርማኬት ሲያከፋፍሉ የተገኙ የስጋ ማቀናባበሪያ እና ሱፐር ማርኬት መታሸጋቸው ተገልፆል፡፡ በፍተሻው የተገኙት ምርቶች በአጠቃላይ የተወገዱ ሲሆን በኮልፌ፣በለሚ ኩራ እና በአራዳ ክፍለ ከተሞች ናቸው፡፡ በቀጣይ ቀናቶች የበዓል ወቅት በመሆኑ  ህብረተሰቡ ህገ ወጥ እርድ የሚያከናውኑ ተቆማቶች በሚመለከትበት ጊዜ በነፃ የስልክ መስመር 8864 ላይ በመደወል ለባለስልጣኑ ማሳወቅ እንዳለበት የባለስልጣኑ የምግብና የጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው  ተናግረዋል።
Hammasini ko'rsatish...
👍 4
ትላንት ማታ በአቃቂ የገበያ ማዕከል በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ 16 ሱቆች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል። ሚያዚያ  24 ቀን2016   ዓ.ም ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ  ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ  መዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 ንግድ  ሱቆች  ሙሉ በሙሉና በከፊል ተቃጥለዋል። የእሳት አደጋዉን  ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የዉሀ  ቦቴ  ከ44 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር የተሰማራ ሲሆን እሳቱ ወደገበያ ማዕከሉ ተስፋፍቶ በሰዉና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን አደጋዉን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት ፈጅቷአል። በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሰው  ላይ የደረሰ ጉዳት  የለም ። አቃቂ የገበያ ማዕከል ትንሹ መርካቶ እየተባለ የሚጠራ የገበያ ማዕከል ሲሆን ገበያ ማዕከሉ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ አንዱ ሲሆን በገበያ ማዕከሉ በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመ በንብረት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል። ኮሚሽን መ/ቤቱ ገበያ ማዕከሉ ለአደጋ የተጋለጠባቸዉን ዝርዝር ጉዳዮችን የመፍትሄ ሀሳቦችን አካቶ ለገበያ ማዕከሉ ማህበራትና ለሚመለከታቸዉ አካላት ያቀረበ ቢሆንም የማስተካከያ ዕርምጃዎች አልተወሰዱም። በመሆኑም በቀጣይ መሰል አደጋዎች እንዳያጋጥሙ መፍትሄ እንዲሰጥ ኮሚሽኑ አሳስቧል።
Hammasini ko'rsatish...
👏 1
⚡️በካንሰር የሚሰቃየው አንድ የላኦሺያ ስደተኛ በአሜሪካ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ፓወር ቦል ሎተሪ አሸንፏል። ገንዘቡን ካንሰሩን ለሚያከመው ለአንድ ጥሩ ሐኪም እንደሚያውለው እና ቤተሰቡንም እንደሚረዳ ተናግሯል።
Hammasini ko'rsatish...
👍 13🥰 3🙏 3👏 1
2
በቻይና አንድ የ86 ዓመት አዛውንት የ81 ዓመት አዛውንት የመጀመሪያ ፍቅራቸውን አገቡ ከ60 ዓመታት በፊት ፍቅረኛሞች ነበሩ ። በመጨረሻም የትዳር ጓደኞቻቸው ሲሞቱ ሰሞኑ መጋባታቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
Hammasini ko'rsatish...
🥰 8👍 2
ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እየሄዱ የነበሩ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤትን ጨምሮ የ4 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከል መረጃና ስታቲክስ ክፍል ኃረፊ ኢንስፔክተር ታምራት ደሳለኝ እንደገለፁት በሀዲያ ዞን ሾኔ ከተማ አስተዳደር ማዞሪያ ቀበሌ ሌሊት 11 ሰዓት 40 ከወላይታ ሶዶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ፒካፕ መኪና በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ባለሶስት እግር ባጃጅ ጋር ተጋጭቶ በውስጡ የነበሩ 3 የአንድ ቤተሰብ አባላት እና አንድ ጎረቤት በድምሩ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተናግረዋል። በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው። ከሟቾቹ መካከል ምጥ ይዟት ወደ ሆስፒታል እያመራች የነበረች እናት እንደምትገኝበት ነው ኢንስፔክተር ታምራት የገለጹት። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑንም ኢንፔክተር ታምራት ጠቁመዋል።
Hammasini ko'rsatish...
😱 8👍 4🥱 1
ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት መሪነት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ። በስነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናትና በርካታ ምዕመናን ተገኝተው እንደነበር ከቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘው መረጃ ያሳያል። Photo Credit - TMC
Hammasini ko'rsatish...
👍 15 3🙏 3👎 1
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ ዛሬ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጥታ አካላት መወሰዳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። የሁለቱም አገልጋዮች የመኖሪያ ቤት መፈተሹም ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ሜክሲኮ ፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ይገኛሉ የተባለ ሲሆን የተያዙበት ምክንያት እንዳልታወቀ የቴሌቪዥን ጣቢያው ገልጿል።
Hammasini ko'rsatish...
🥰 1🤔 1
ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር የተቋቋሙ አስተዳደሮች እስከ ሰኔ 30 መፍትሔ እንደሚያገኙ ጄነራል ታደሰ ተናገሩ የትግራይን ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ስር ተጠቅለው የተቋቋሙ አስተዳደራዊ መዋቅሮች እስከ ሰኔ 30/ 2016 ዓ.ም መፍትሔ እንደሚያገኙ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል። ጄነራል ታደሰ ባለፉት ሁለት ቀናት የፕሪቶሪያ ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት አተገባበር በተመለከተ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመከላከያ እና ከፌደራል መንግሥት ባለስልጣናት ጋር ያደረጉትን ውይይት መሰረት በማድረግ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው ይህንን የተናገሩት። የአማራ ክልል ይገባኛል በሚላቸው እና የትግራይን ጦርነት ተከትሎ ክልሉ ጠቅልሎ እንደ አዲስ ያዋቀራቸው የደቡብ ትግራይ እና ጸለምቲ ወረዳዎች መፍትሄ ለማበጀት እስከ ግንቦት 30/2016 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ ስምምነት ላይ መደረሱን ጄነራል ታደሰ ገልጸዋል። በተጨማሪም በአማራ ክልል በኩል ወልቃይት ተብሎ በሚጠራው ምዕራብ ትግራይ እንደ አዲስ የተቋቋመው አስተዳደር እስከ ሰኔ 30 ባለው ጊዜ መፍትሔ ይበጅለታል ብለዋል። በዚህም ውይይት ላይ ትጥቅ መፍታትን አስመልክቶ የትኞቹ አስተዳዳራዊ መዋቅሮች መፍረስ እንዳለባቸው እና የተፈናቀሉ ዜጎች እንደሚመለሱ ዝርዝር እቅድ የወጣ ሲሆን ይህንንም የሚቆጣጠረው እና የሚያረጋግጠው የአፍሪካ ኅብረት የስምምነት ክትትል አረጋጋጭ እና አስከባሪ ኮሚቴ እንደሚሆን ተገልጿል። ኮሚቴው መቀለ ላይ ቢሮ እንዳለው ከዚህ ቀደም ጄነራል ታደሰ መናገራቸው ይታወሳል።
Hammasini ko'rsatish...
😁 11👍 7🔥 6