uz
Feedback
💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀

Kanalga Telegram’da o‘tish

« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali 💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 analitikasi

💎🎀የሰለፍያ ሴቶች ከቀይ ወርቅ የበለጠ ውድ ናቸው 💎🎀 (@https_asselefya1) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 280 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 123-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 373-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 280 obunachiga ega bo‘ldi.

03 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -19 ga, so‘nggi 24 soatda esa 3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 16.55% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.82% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 364 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 259 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
« الـنِّـسَـاء الـسَّــلَــفِـيَّـة أَغْـلَى مِـنَ الـذَّهَـبِ الأحْـمَـر» قال العلامة المحدث:مقبل الوادعي رحمه الله ማንኛዉም አስተያየት/እርምት መስጫ ↓↓↓↓↓↓ @Ass_selefyaa_bot @Ass_selefyaa_bot

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 04 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 280
Obunachilar
+324 soatlar
+217 kunlar
-1930 kunlar
Postlar arxiv
እከሌ ልቤ ሰበረኝ ሸወደኝ አታለለኝ....እያላችሁ የምታለቃቅሱ ስንተየ ተመከረ ተዘከረ ለምን አሰሙም አታነቡም ግድ እናንተ ላይ እስኪደርስ ለምን ትጠብቃላችሁ አረ ተዉ እባካችሁ አንብቡ አድምጡ ሁሌ ወቀሳ ሁሌ ለቅሶ አይበቃም ወይ ይህ ነገር ?! =

#አደራ_የባለቤትህን_ልብ_ተንከባከበው በመካከላችሁ ያለውን ፍቅር አጠናክረው፡፡ 1. የህይወትን ነፃነት ስጣት 2. ስጦታ ግዛላት 3. ስሟን አቆላምጠህ ጥራት 4. መልካምን ሰላምታ ተለዋወጣት 5. ወደ
#አደራ_የባለቤትህን_ልብ_ተንከባከበው በመካከላችሁ ያለውን ፍቅር አጠናክረው፡፡ 1. የህይወትን ነፃነት ስጣት 2. ስጦታ ግዛላት 3. ስሟን አቆላምጠህ ጥራት 4. መልካምን ሰላምታ ተለዋወጣት 5. ወደ ቤት ስትገባ ሳማት 6. ድንገተኛ የምትመኘውን እና የምትፈልገውን አድርግላት 7. መግባባትን መርህህ አድርግ 8. የሚያነቃ ልቧን የሚያንጠለጥል ታሪክ አስተምራት 9. ወደ ቤት ስትገባ ስለ ስራህ ሳይሆን ስለ ውሎዋ አዳምጣት 10. ወደ ቤት ስትገባ ሳሎን ቤት በነፃነት ብዙ ተቀመጥ 11. የሰራችውን ምግብ በአድናቆት ተመገብ 12. ልብሱ ያምራል በላት 13. ስታረግዝ ተንከባከባት 14. ስጦታ ስትሰጥህ በጣም በፀጋ ተቀበላት 15. ስታናግራት በልዩ በሚማርክ በመስህብ በመልካም አገላለፅ አናግራት 16. የምትወድልህን ልብስ ልበስላት 17. ከቻልክ ስለ እርሷ ቁንጅና ተክለ ቁመና የሚገልፅ ግጥም ፃፍላት 18. ስትለብስ በጣም እንደሚያምርባት ንገራት 19. በማክበር የፍቅር ቃላቶችን በመጠቀም ልቧን አስደስታት

ዐቅላችን ዐቅል እንዳያስተን ~ ዐቅል አላህ ለሰው ልጅ የሰጠው ትልቅ ስጦታ ነው። የሰው ልጅ በዐቅል ያመዛዝናል፣ ያገናዝባል። ይሁን እንጂ ዐቅል በወሕይ ካልታገዘ ደካማ ነው። ስለዚህ ከዐቅል ይልቅ ቀዳሚው ወሕይ ነው፣ ቁርኣንና ሶሒሕ ሐዲሥ። ዐቅልን ፈራጅ ቀዳጅ ማድረግ እና ከወሕይ በላይ ማንገስ ዐቅልን ጣዖት አድርጎ መያዝ ነው የሚሆነው። ሸሪዐዊ ማስረጃን ገሸሽ በማድረግ "እኔኮ ዐቅል አለኝ፤ ሁሉንም በራሴ ነው የምወስነው" አይነት ልክፍት ከተሰማህ በራስ መኮፈስ፣ ዐቅልን ማምለክ ውስጥ ገብተሃል። ይሄ በዐቂዳ ጉዳይ ላይ ዐቅልን እናስቀድማለን የሚሉት የአሻዒራና የማቱሪዲያ ቡድኖች የወደቁበት ጥፋት ነው። ከዐቅል ጋር አይገጥሙም በሚል ሃሰተኛ ምክንያት ቁርኣንና ሐዲሥን በመግፋት የአላህን ሲፋት ሲያስተባብሉ ይታያሉ። ሌሎች በቀደዱላቸው እየፈሰሱ እንጂ ከዐቅል ጋር የማይሄደው የነሱ ፍልስፍና ነው። በተጨማሪም ዛሬ ዛሬ አካዳሚ ትምህርት ገፋ ያደረጉ አንዳንድ አካላት ዐቅልን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ የሸሪዐ ጉዳዮች ላይ አፈንጋጭ አቋሞችን የሚያራምዱበት ሁኔታ አለ። አንዳንዶች የትምህርት ማእረጋቸው ብቅል ሆኖ ይፈትናቸዋል። አካዳሚ ስለተማሩ ብቻ ያላቅማቸው በየዘርፉ ጥልቅ የሚሉ የ'ርጎ ዝንብ ይሆናሉ። እየውልህማ አባኪያ! 1. ዐቅል በቂ ቢሆን ኖሮ ነብይ አይላክም ነበር። ነብይ የሚላከው ሰዎች የማያውቁትን መለኮታዊ ነገር ለማስተማር ነው። 2. ዐቅል በቂ ቢሆን ኖሮ ቁርኣን ባልወረደ ነበር። በዐቅል ብቻ ሌላው ህዝብ ቀርቶ ነብያችን ﷺ እንኳ የኢማንን ዝርዝር አያውቁም ነበር። አላህ እንዲህ ይላል፦ { وَكَذَ ٰ⁠لِكَ أَوۡحَیۡنَاۤ إِلَیۡكَ رُوحࣰا مِّنۡ أَمۡرِنَاۚ مَا كُنتَ تَدۡرِی مَا ٱلۡكِتَـٰبُ وَلَا ٱلۡإِیمَـٰنُ وَلَـٰكِن جَعَلۡنَـٰهُ نُورࣰا نَّهۡدِی بِهِۦ } "እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲሆን መንፈስን (ቁርኣንን) አወረድን፡፡ መጽሐፉም እምነቱም ምን እንደሆነ የምታውቅ አልነበርክም፡፡ ግን (መንፈሱን) ከባሮቻችን የምንሻውን ሰው በእርሱ የምንመራበት ብርሃን አደረግነው፡፡" [አሹራ፡ 52] 3. ዐቅል ልክ እንደሌሎች የስሜት ህዋሳት ወሰን (limit) አለው። ጆሮ ድምፅ በራቀው ቁጥር መስማቱ እየቀነሰ እየቀነሰ ሄዶ መጨረሻ ላይ ይጠፋበታል። አይን ካጠገቡ ያለ ነገር በራቀ ቁጥር እያነሰ ሄዶ ከነ ጭራሹ ከእይታ ይሰወርበታል። አእምሮም እንደዚያው ነው። ሁሉን ነገር የመረዳት አቅም የለውም። 4. ዐቅል ከስህተትና ከጉድለት ፍፁም አይደለም። "ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት " የሚባለው ያለ ምክንያት አይደለም። ፍፁም የሆነው ማስረጃ ወሕይ ነው፣ መለኮታዊ ራእይ። ዐቅል በኋላ ታሪክ፣ በአስተዳደግ፣ በትምህርት፣ በልማድ፣ በአካባቢ፣ ... ተፅእኖ ስር ይወድቃል። በዚህ የተነሳ ነው አረዳዳችን የሚራራቀው። ይህም እውነታ ዐቅል ወጥ የሆነ መለኪያ እንደሌለው ያሳያል። ወጥ ቢሆን ኖሮ በህንድ ፍልስፍና፣ በግሪክ፣ በሮማ፣ በፋርስ፣ በቻይና፣ እንዲሁም በዛሬው የምእራቡ ዓለም እና በምስራቁ ዓለም ፍልስፍናዎች መካከል ልዩነቶች ባልተንፀባረቁ ነበር። የነዚህ ሃገራት ፈላስፎችም ለተውሒድ በተመሩ ነበር።. 5. ዐቅል አጥጋቢ መለኪያ ቢኖረው ኖሮ ዐቅልን እንከተላለን የሚሉት ጀህሚያዎች፣ ሙዕተዚላዎች፣ አሻዒሪዎችና ማቱሪዲያዎች ባልተለያዩ ነበር። ዐቅል በቂ አጥጋቢ መለኪያ ቢሆን ኖሮ ሌላው ቀርቶ በአንድ ቡድን ውስጥ እንኳ መለያየት ባልኖረ ነበር። አሻዒራን እንውሰድ። ሙፈዊዳ እና ሙአዊላ ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ። ሁለቱ ተቃራኒ መንገዶች ናቸው። በሌላ በኩል የቀደሙት አሻዒራዎች የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ጨምሮ በርካታ የአላህን ሲፋት ያፀድቃሉ። የኋለኞቹ ያስተባብላሉ። ወደ ግለሰብ ዝርዝር ብንገባ ደግሞ ልዩነቱ ይሰፋል። 6. ዐቅል አስተማማኝ መለኪያ ቢሆን ኖሮ ግለሰቦች ከአንድ አቋም ወደ ሌላ ባልተገላበጡ ወይም በተለያዩ ከታቦቻቸው ላይ የተለያዩ አቋሞችን ባላንፀባረቁ ነበር። ኢብኑል ጀውዚን ምሳሌ መውሰድ ይቻላል። አንዴ ተእዊል፣ አንዴ ኢሥባት፣ ሌላ ጊዜ ተፍዊድ ላይ ተወዛውዘዋል። 7. ዐቅል በቂ መለኪያ ቢሆን ኖሮ በዐለም አቀፍ ደረጃ ፖለቲከኞች እና ኢኮኖሚስቶች ወጥና የጋራ መስመር መንደፍ በቻሉ ነበር። እውነታው ግን ሌላ ነው። የካፒታሊዝምና የሶሻሊዝም ፍጥጫ ለዚህ ሁነኛ ማሳያ ነው። በሀገራችንም በ1960ዎቹ እና ሰባዎቹ እንደ አሸን የፈሉ የፖለቲካ ቡድኖች ሁሉም ለማለት በሚቀርብ ሶሻሊስቶች ነበሩ። ነገር ግን መማራቸውም ዐቅላቸውም ያላግባባቸው የሚጠፋፉ ቡድኖች ነበሩ። ስለዚህ በዐቅል እያመሀኙ ከቁርኣንና ሐዲሥ ማስረጃዎች መራቅ ከራሱ ከዐቅል ጭምር መራቅ እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል። ሲጀመር ጤነኛ ዐቅል ከትክክለኛ ወሕይ ጋር አይጋጭም። ስለሆነም ለወሕይ እጅ ለመስጠት መድረቅረቅ አይገባም። በዚህ ረገድ የኢማን የስኬት ማማ ላይ የደረሱትን የሰለፎችን አቋም እንመልከት፦ 1. ዑመር ብኑል ኸጣብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦ ‏إياكم وأصحاب الرأي، فإنهم أعداء السنن، أعيتهم الأحاديث أن يحفظوها فقالوا بالرأي، فضلوا وأضلوا “ከአስተያየት ባለቤቶች ተጠንቀቁ። ምክንያቱም እነሱ የሱና ጠላቶች ናቸው። ሐዲሦችን መያዝ ስለተሳናቸው በራሳቸው አስተያየት ወሰኑ፣ በመሆኑም እነሱም ጠመሙ፣ ሌሎችንም አጠመሙ።” [ኡሱል አል-ኢዕቲቃድ፣ አላለካኢይ፡ 57] 2. ዐሊይ ብኑ አቢ ጣሊብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦ لو كان الدينُ بالرأي لكان أسفلُ الخفِّ أولَى بالمسحِ من أعلاهُ ، وقد رأيتُ رسولَ اللهِ صلَّى اللهُ عليه وسلم يمسحُ على ظاهرِ خفَّيهِ “ሃይማኖት በራስ አስተያየት የሚመራ ቢሆን ኖሮ፣ የጫማ ታችኛው ክፍል ከላይኛው ክፍል ይልቅ ለማበስ ቅድሚያ ይኖረው ነበር። ነገር ግን የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የጫማቸውን የላይኛው ክፍል ሲያብሱ ነው ያየሁት።” [አቡ ዳውድ፡ 162] ስለዚህ የመፍትሄው ቁልፍ አቅምን ማወቅ ነው። ነፍሲያን መርገጥ። (ኢብኑ ሙነወር፣ ሶፈር 22/1447) = የቴሌግራም አድራሻ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ أفْضَلُ الأعمالِ إِدخالُ السرورِ على المؤمِن؛ كسوتَ عورَتَه، وأَشبعتَ جوعتَهُ، أو قَضَيْتَ له حاجة
የአላህ መልእክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ أفْضَلُ الأعمالِ إِدخالُ السرورِ على المؤمِن؛ كسوتَ عورَتَه، وأَشبعتَ جوعتَهُ، أو قَضَيْتَ له حاجةً “ከስራዎች ሁሉ በላጩ አንድን አማኝ ማስደሰት ነው። ይህም ነውሩን በመሸፈን፣ ረሃቡን በማብላት ወይም ጉዳዩን በመፈፀም ነው።” አልባኒይ ሶሒሕ ነው ብለውታል። [አት-ተርጊብ፡ 2090] = የቴሌግራም አድራሻ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

መተዉ ስንጀምር  መኖር እንጀምራለን ‼️ =

«ስንቱ ተዋርዶ በሚያድርበት ምሺት ተሰትሮ ማደርን ያክል ፀጋ የለም።አሁንም ሲትራህ ያ ረሕማን ! = t.me/https_Asselefya1

አንዳንድ ጊዜ alarm ሲጮህ ስናደድ ለሚያየኝ ሰዉ እኔ የሞላሁት አልመስለም እኮ🖐 መልካም አዳር ይሁንላችሁ 🌸 =

ቆንጆ ቆንጆ የምፀፉበት ልልክላችሁ ነዉ አላችሁ 🖐

«በወንጀል» ላይ ሆነህ የደበቀህ ጌታ «በተዉበት» ላይ ሆነህ  አያዋርድህም። #አላህ = t.me/https_Asselefya1

ይቅር  ማለት እኮ ቀላል ነዉ  ነገር ግን እንደበፊቱ መሆን «በጣም »ከባድ ነዉ። = t.me/https_Asselefya1

ውዷ
ጠንካራ መሆን ከፈለግሽ የሚመጡብሽን ነገሮች በሙሉ በትግስት እለፊ ያኔ አንች ጀግና ነሽ https://t.me/qdemiy_letwuhide

«መልካም ስነ ምግባር መላበስ ማለት: ትርፍ ነገር ማስገኘት አይደለም። በተለይ ወደ ተውሒድ፣ ወደ ሱና ቀረብን ብለን ስናስብ - አንዳንዴ - ለመልካም ስነ ምግባር የምንሰጠው ዋጋ ሊያንስ ይችላል። ይሄ በጣም የግንዛቤ ክፍተት ነው።» አርበዒን ሐዲሥ (18:5’) ኡስታዝ  ኢብኑ  ሙነወር