uz
Feedback
AAFDA

AAFDA

Kanalga Telegram’da o‘tish
2 699
Obunachilar
+224 soatlar
+357 kunlar
+11930 kunlar
Postlar arxiv
AAFDA
2 701
photo content
+8

AAFDA
2 701
ከ12,900,960 ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ህገ-ወጥ የሺሻ እቃዎችና ኮንትሮባንድ ምርቶች ተወገዱ። 4/11/2018 ዓ.ም የንፋስ ስልክ ምግብና መድኃኒት ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኙ ከፖሊስ፣ ከደንብ ማስከበር አካላት፣ ከአካባቢ ማህበረሰብ እና ከሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር በተቀናጀ ትብብር በተለያዩ ወቅቶች ባከናወነው የቁጥጥር እና የህግ ማስከበር ስራ፣ በህብረተሰቡ ጤናና ደህንነት ላይ አደጋ የሚያስከትሉ በርካታ ህገ-ወጥ የሺሻ እቃዎች እና ኮንትሮባንድ ምርቶችን ማስወገድ ተችሏል። በዚህም 500 ጠርሙሶች፣ 650 ቡሬዎች፣ 900 ገመዶች፣ 50 ሳህኖች፣ 310 የኤሌክትሪክ ሺሻ እቃዎች እና 450 የቡሬ ማስቀመጫዎች በድምሩ 4,110 የሺሻ መጠቀሚያ እቃዎች ተወግደዋል። በተጨማሪም የኮንትሮባንድ እና የማለቂያ ጊዜ (Expiry Date) የሌላቸው 500 ካርቶን ውስጥ 25,000 ምርቶች ተወግደዋል። በአጠቃላይ የተወገዱት ህገ-ወጥ ምርቶች ግምታዊ ዋጋ ከ12,900,960 (አስራ ሁለት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሺ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ብር) የሚደርስ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ ጉዳይ የጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሸበላው እንደገለጹት፣ የህገ-ወጥ የትምባሆ እና ሌሎች ለጤና አደገኛ ምርቶች ዝውውርን ለመግታት ባለስልጣኑ ከአጋር ተቋማት ጋር በመቀናጀት የሚያከናውነው የቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። ህብረተሰቡም ህገ-ወጥ ምርቶችን እና ለጤና አዋኪ ድርጊቶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ፣ እንዲሁም ጥርጣሬ የሚያሳድሩ ህገ ወጥ ድርጊቶችን ሲመለከት ለባለስልጣኑና ለሚመለከታቸው አካላት በወቅቱ እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርበዋል።

AAFDA
2 701
photo content
+5

AAFDA
2 701
photo content
+5

AAFDA
2 701
ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ ለ25‚771 ተቋማት እና ለ23‚940 ጤና ባለሙያዎች በስታንዳርዱ መሰረት ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል የብቃት እድሳት ተግባራትን አከናወነ፡፡ -------------------------- ሐምሌ 4/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ምግብ መድኃኒት ባለስልጣን የብቃት ማረጋገጥ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት በምግብ፣ በጤና እና ጤና ነክ ተቋማት በስታንዳርዱ መሰረት ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አኳያ ዘርፈ ብዙ የብቃት እድሳት ማረጋገጥ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማት በስታንዳርዱ መሰረት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አኳያ ለ1,866 ጤና ተቋማት፣ ለ1‚690 መድሃኒት ችርቻሮ፣ ለ22,104 የምግብና ጤና ነክ አምራች፣አከፋፋይ፣ችርቻሮና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ መሰጠቱን፣ ለ23,940 ጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት መሰጠቱን፣ ለ111 የባህል ህክምና ተቋማት ደግሞ እድሳት መስጠቱን በዝርዝር ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች አቅርቧል፡፡ በበጀት ዓመቱ በጤና ባለሙያዎች ብቃት ማረጋገጥ ለብልሹ አሰራር ምንጭ የሆኑ ሀሰተኛ CPD 69፣ የስራ ልምድ 21፣ COC 1፣ ሙያ ፈቃድ 4፣በድምሩ 95 ሀሰተኛ መረጃች ላይ እርምጃ በመውሰድ ህግ የማስከበር ስራ መስራት ተችሏል። ከነዚህ ውስጥ በህግ አገልግሎት ቀርበው እየታዩ ያሉ 6 ሀሰተኛ መረጃዎች መሆናቸውም ተገልጸዋል፡፡ በባለስልጣኑ የዘርፉ ምክትል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትዕግስት በዳዳ በበጀት ዓመቱ የብቃት አፈፃፀም ጥሩ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ እየተመዘገበ መምጣቱን፣ ክፍተቶችን በማረም ከባለፈው በጀት ዓመት ተምረን በቀጣይ በጀት ዓመት የተሻለ ተግባራትን ለማከናወን መነሳት እንደሚያስፈልግ፣ የ2019 በጀት ዓመት ቅድመ እድሳት ኢንስፔክሽን ስራዎችን በማጠናቀቅ የብቃት እድሳት ተግባራትን ትኩረት ሰጥቶ ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት አክለውም ሁላችንም የ2019 በጀት ዓመት ብቃት እድሳት ተግባራት ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በሰጡት የስራ አቅጣጫ አመላክተዋል፡፡

AAFDA
2 701
photo content
+6

AAFDA
2 701
photo content
+9

AAFDA
2 701
በሀገር ደረጃ የተጀመረው "ተስፋን እንትከል" የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የዜጎችን ከጠባቂነት ወደ አምራችነት የመሻገር ጉዞውን እንቀላቀላለን ***** የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሐምሌ 3/2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ከማዕከል እስከ ክላስተር ያሉትን አመራሮችና ሰራተኞች በማስተባበር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል አስኮ አዲስ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው ፍቅር ጫካ ችግኝ በመትከል ሀገራዊ አሻራውን አስቀምጧል ፡፡ በችግኝ ተከላው ዶክተር ሙሉእመቤትን ጨምሮ ሁሉም የባለስልጣኑ አመራሮችና ባለሙያዎች በጠዋት ተገኝተው በርካታ ችግኝኞችን ተክለዋል፡፡

AAFDA
2 701
photo content
+8

AAFDA
2 701
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከ8.5 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶችና ምግቦች ተወገዱ፡፡ *** ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ቂርቆስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በህብረተሰቡ ጤና ላይ ከፍተኛ አደጋ ሊያደርሱ የሚችሉና የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸውን በርካታ የመድኃኒትና የምግብ ምርቶች ከገበያ በማስወገድ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። በዚህ መጠነ ሰፊ የቁጥጥርና የማስወገድ ዘመቻ በአጠቃላይ ከ8.5 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የሕክምና መገልገያዎች፣ መድኃኒቶችና የተለያዩ የምግብ አይነቶች እንዲወገዱ ተደርጓል። ይህም በክፍለ ከተማው የሚገኘውን ማህበረሰብ ሊያጋጥመው ከሚችል የጤና ቀውስና ያልተገባ የኢኮኖሚ ብክነት የታደገ የቁጥጥር ሥራ መሆኑ ተገልጿል። ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የክፍለ ከተማው ኮሙዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት የዜና ክፍል እንዳገኘው መረጃ ከሆነም በቁጥጥር ዘመቻው ወቅት በዋናነት የመድኃኒት ጥራትንና ደህንነትን ለማረጋገጥ በተደረገው ፍተሻ ከሁለት ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የሚመዝኑና አገልግሎት የማይሰጡ መድኃኒቶች ተሰብስበዋል። እነዚህ ጊዜ ያለፈባቸው መድኃኒቶች የተገኙት በክፍለ ከተማው ሥር ከሚገኙት የመንግሥት ጤና ጣቢያዎች እንዲሁም የግል ፋርማሲና መሰል የሕክምና ተቋማት እንደሆነም ተመላክቷል። የመድኃኒቶቹ አጠቃላይ ግምታዊ ዋጋ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ሦስት መቶ አምሳ አራት ብር መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ምርቶቹ በተቀመጠው የአወጋገድ ስርዓት መሰረት እንዲወገዱ መደረጉም ተገልጿል። ከመድኃኒቶቹ በተጨማሪ በሕዝብ የዕለት ተዕለት የምግብ ፍጆታና ደህንነት ላይ ያነጣጠረ ጥብቅ የክትትል ሥራ ተከናውኗል። በዚህም መሠረት በተለያዩ የንግድ ተቋማትና ሱፐር ማርኬቶች ውስጥ ሲሸጡ የተገኙ ወደ ሰባት ሺህ ኪሎ ግራም የሚጠጉ የተበላሹና የአገልግሎት ዘመናቸው ያበቃ የምግብ ምርቶች ተይዘው ተወግደዋል። በተመሳሳይ ሁኔታ ከሰባት መቶ ሰማኒያ ሊትር በላይ የሚሆኑ የተለያዩ መጠጦች፣ ለስላሳዎችና የታሸጉ ውሃዎች የተወገዱ ሲሆን የእነዚህ ምግቦችና መጠጦች አጠቃላይ ዋጋ ከአንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር በላይ መሆኑ ተጠቅሷል። ጽሕፈት ቤቱ በዚሁ የቁጥጥር ዘመቻው ወቅት በሕገ-ወጥ መንገድ የተከናወነና የጤና ምርመራ እውቅና የሌለው የሦስት በሬዎች እርድ ስጋ መያዙን ይፋ አድርጓል። ይህ ሦስት መቶ ሺህ ብር ግምት ያለውና ደረጃውን ያልጠበቀ ሕገ-ወጥ ሥጋ ወደ ማህበረሰቡ እንዳይሰራጭና የጤና እክል እንዳይፈጥር ወዲያውኑ እንዲወገድ መደረጉም አእንዲዘሁ ተነግሯል። ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የቁጥጥር ተግባር በክፍለ ከተማው ውስጥ የሚገኙ የንግድና የጤና ተቋማት ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንዲሠሩ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ወደፊትም ህብረተሰቡን ጊዜያቸው ካለፈባቸውና ያለጥንቃቄ የሚዘጋጁ ምግብና መጠጦች ምርቶች ለመጠበቅ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል ።

AAFDA
2 701

AAFDA
2 701
photo content
+6

AAFDA
2 701
የአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ምግብና መድሃኒት ፅ/ቤት ባካሄደው ክትትልና ቁጥጥር 187 ተቋማት ላይ እርምጃ ወሰደ፡፡ ---------------------- ሰኔ 30/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በህብረተሰቡ ላይ የሚደርሰውን የጤና ችግር ለመከላከል ባካሄደው የክትትልና የቁጥጥር ስራ 187 ተቋማት ላይ እርምጃ በመውሰድ ከ3 ሚሊዬን ብር በላይ የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶችን ማስወገድ ችሏል፡፡ ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ ለ950 ምግብና ጤና ነክ፣ ለ161 ጤና ተቋማት ብቃት እድሳት ማከናወኑን፣ ለ321 ጤና ተቋማት፣ ለ1‚360 ጤና ባለሙያዎችን ክትትልና ቁጥጥር ስራ በማከናወን 187 ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል፡፡ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የህብረተሰቡን ጤና ለማስጠበቅ ግምታዊ ዋጋቸው 3‚193‚370 ብር የሚያወጣ የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምግብና መጠጥ እንዲሁም መድኃኒት በማስወገድ በህብረተሰቡ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የጤና ችግር ቀድሞ የመከላከል ስራ ማከናወን ተችላል፡፡ ጽ/ቤቱም ባካሄደው የቁጥጥርና የክትትል ስራ ጤና ተቋማት ከነበረባቸው ችግር ወጥተው ወደ ስታንዳርድ እንዲመጡ መሆኑ፣ የተቋማት ባለቤቶች የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያመጡ መደረጉን፣ ተቋማት የሚሰጣቸውን ግብረ መልስና አስተያየት ተግባራዊ በማድረግ ከፅ/ቤቱ ጋር ተቀራርበው በመስራት ስታንዳርዱን ጠብቀው አገልግሎት የሚሰጡ ሞዴል ተቋማትን መፍጠር ተችሏል፡፡

AAFDA
2 701
photo content
+3

AAFDA
2 701
photo content
+9

AAFDA
2 701
የየካ ቅርንጫፍ ምግብና መድኃኒት ጽ/ቤት የህብረተሰቡን ጤና ለማስጠበቅ ከ28 ሚሊዬን ብር በላይ የሚገመት የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶችን አስወገደ፡፡ ------------------------- ሰኔ 30/2018ዓ.ም የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን የየካ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የህብረተሰቡን ጤና ለማስጠበቅ ከ 28 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸውን የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምግብ፣ መድሃኒትና ነክ ምርቶች ማስወገድ ተችሏል፡፡ ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ ለ1836 የምግብ እና 280 የጤና ተቋማት ብቃት ማረጋገጥ ስራ ሰርቷል ፡፡ ለ4417 የምግብና ጤና ተቋማት እና ለ1269 ጤና ባለሙያዎች ክትትልና ለቁጥጥር ማካሄድ መቻሉን እና በበጀት ዓመቱ ባካሄው የክትትልና ቁጥጥር ስራም 286 ተቋማት ላይ የፁሁፍ ማስጠንቀቂያና በ13 ተቋማት ደግሞ የእሸጋ እርምጃ መውሰዱን ለባለድርሻ አካላት እና ለንግዱ ማህበረሰብ አሳውቋል፡፡ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የህብረተሰቡን ጤና ለማስጠበቅ ግምታዊ ዋጋቸው 28‚644‚427.47 ብር የሚያወጣ የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምግብና መጠጥ እንዲሁም መድኃኒት ማስወገድ ተችሏል፡፡ የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉ እመቤት ታደሰ ለፀሀይ ተጋላጭ በሆኑ ምርቶች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስተካከል መስራት እንደሚያስፈልግ፣ የምግብ አገልግሎት ሰጪ እና ጤና ተቋማት ሀላፊነት ወስደው ለህብረተሰቡ የተሻለና ጥሩ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው፣ ተቋማት በወቅቱና በጊዜው ኦን ላይን ብቃት እድሳት ማከናወን እንደሚገባቸው በሰጡት የስራ አቅጣጫ አመላክተዋል፡፡ በመጨረሻም የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ለምግብና ጤና ተቋማት ባለቤቶች የእውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡

AAFDA
2 701
photo content

AAFDA
2 701
photo content
+9

AAFDA
2 701
በልደታ ክፍለ ከተማ ከ9,000 በላይ አቅመ ደካሞችን ለማከም የታቀደ የ3 ቀናት ነጻ የህክምና መርሃ ግብር ተጀመረ። 30/11/2018 ዓ.ም የ ልደታ ክፍለ ከተማ ምግብና መድሓኒት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከልደታ ጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የግልና የመንግስት የጤና ተቋማትን በማስተባበር በጋራ ያተዘጋጀው የ3 ቀናት ነጻ የህክምና መርሃ ግብር በልደታ ክፍለ ከተማ ተስፋ ኮከብ የመጀመሪያ ት/ቤት በይፋ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የልደታ ክፍለ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ የክፍለ ከተማው ጤና ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም ሌሎች አመራሮች በተገኙበት መርሃ ግብሩን በይፋ ተጀምሯል። ነጻ የኅክምና መርሀ ግብሩ በክፍለ ከተማው በ 10 ወረዳዎች የሚኖሩና የህክምና ወጪን ለመሸፈን የማይችሉ አቅመ ደካማ ዜጎችን በዋናነት ለማገዝ የታለመ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ 3 ቀናት ከ9,000 በላይ ተጠቃሚዎችን በነጻ ለማከም በእቅድ ተይዟል። በመርሃ ግብሩ 7 የግል ጤና ተቋማትና 8 የመንግስት ጤና ጣቢያዎች በመተባበር የተለያዩ የህክምና አገልግሎቶችን እየሰጡ ይገኛሉ። በነጻ ህክምናው የሚሰጡት አገልግሎቶች የዓይን ህክምና፣ የጥርስ ህክምና፣ የውስጥ ደዌ ህክምና፣ የስኳርና የደም ግፊት ምርመራ፣ የላብራቶሪ ምርመራዎች፣ የኢሜጂንግና የኤክስሬ አገልግሎት፣ የስብ ምርመራ፣ የመድኃኒት አቅርቦት እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ የህክምና አገልግሎቶችን ያካትታሉ። ከዚህ በተጨማሪ ከባድ የጤና ችግር (Critical Cases) ያለባቸው ታካሚዎች ተለይተው ወደ ተገቢው የህክምና ተቋም በማስተላለፍ ቀጣይነት ያለው የህክምና ክትትልና ሕክምና እንደሚያገኙ ተገልጿል። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተናገሩት የልደታ ክፍለ ከተማ ምግብ፣ መድኃኒትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ በላይነህ ገብሩ፣ መርሃ ግብሩ ለአቅመ ደካማ ዜጎች የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግና የህብረተሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላት የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። የመንግስትና የግል ጤና ተቋማት በመቀናጀት የጀመሩት ይህ ተግባር የጤና አገልግሎት ፍትሃዊነትንና ተደራሽነትን በማጠናከር ለማህበረሰቡ ተጨባጭ ጥቅም እንደሚያስገኝ ጠቁመው በዚህ በጎ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላትን አመስግነዋል።

AAFDA
2 701
photo content
+8