2 610
Suscriptores
+124 horas
+237 días
+7930 días
Archivo de publicaciones
2 610
የጤና ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ እድሳት በወቅቱ እንዲያድሱ የኮልፌ ቅርንጫፍ ምግብና መድኃኒት ጽ/ቤት ጥሪ አቀረበ።
4/10/2018 ዓ.ም
የኮልፌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት የጤና ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ (Licensing) እድሳት በወቅቱ እንዲከናወኑ እና ተቋማት ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።
የግል ጤና ተቋማት ባለቤቶች፣ የመድኃኒት ቤት ባለቤቶች እና የባህል ህክምና አገልግሎት ሰጪዎች በተገኙበት በተካሄደዉ የምክክር መድረክ ተቋማት ከሐምሌ 1 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2019 ዓ.ም. ድረስ የሚከናወነውን የብቃት ማረጋገጫ እድሳት በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ተቋማት የሚያስፈልጋቸውን ሰነዶች፣ የሰው ኃይል መስፈርቶች እና ሌሎች ስታንዳርዶች በመሟላት ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
ሁሉም የጤና ተቋማት ተገቢውን መስፈርቶች በሟሟላት እድሳታቸውን በተቀመጠዉ ጊዜ ማጠናቀቅ እንዳለባቸው የተገለጸ ሲሆን ፣ ይህም ተቋማት እራሳቸውን ከአላስፈላጊ ቅጣት እንዲጠበቁ ያግዛል ተብሏል።
የቅርንጫፍ ጽ/ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ሙኒራ ነጋሽ እንደገለጹት፣ የጤና ተቋማት ባለቤቶች ተቋማቸውን በተቀመጡ ስታንዳርዶች መሰረት በማስተዳደር፣ የብቃት እድሳትን ባለስልጣኑ ባስጀመረው የኦላይን ሲስተም በወቅቱ በማከናወን፣ ፍቃድ ያላቸውንና ብቁ ባለሙያዎችን በመቅጠር እንዲሁም የአገልግሎት ጥራትን በቀጣይነት በማሻሻል ለህብረተሰቡ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ማቅረብ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
የብቃት ማረጋገጫ እድሳት በወቅቱ መከናወኑ የጤና ተቋማት ህጋዊነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል፣ የታካሚዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ እና በጤናው ዘርፍ የሚደረገውን ቁጥጥር ውጤታማ ለማድረግ ወሳኝ ሚና ያለው በመሆኑም ሁሉም ተቋማት በ 11 ዱም ቅርጫፍ ጽ/ቤት በተወሰነው ጊዜ እድሳታቸውን በማጠናቀቅ ጥራት ላለው የጤና አገልግሎት ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ባለስልጣኑ ጥሪ ያቀርባል።
2 610
ለ2019 በጀት አመት የጤና ተቋማት የብቃት ማረጋገጫቸውን በወቅቱ ለማደስ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ ጥሪ አቀረበ።
27/8/2018 ዓ.ም
ከሀምሌ 1 እስከ ነሀሴ 30 ድረስ ለሚከናወነው የተቋማት ብቃት ማረጋገጫ እድሳት ተቋማት ማድረግ ስለሚገባቸው ቅድመ ዝግጅት
እና የጤና ባለሞያዎች የሙያ ፍቃድ እድሳት መመሪያዎች ዙሪያ ከተቋማት ባለቤቶች ጋር የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሂዷል።
የብቃት ዘርፍ ም/ል ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትግስት በዳዳ ሁሉም የጤና ተቋማት የብቃት እድሳታቸውን ባለስልጣኑ ባስጀመረው የኦንላይን ሲስተም ከሀምሌ 1 እስከ ነሐሴ 30 ድረስ በወቅቱ እንዲያጠናቅቁ ጥሪ አቅርበዋል።
ስራ አስኪያጅዋ አክለውም ተቋማት የተቀመጡ የጥራት መስፈርቶች በመተግበር እና የጤና አገልግሎቱን ደረጃ በማሻሻል በአለም አቀፍ ደረጃ በዘርፉ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ማጠናከር እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
ተቋማቱ በውስጣቸው የሚቀጥሯቸውን የጤና ባለሙያዎች ሲቀጠሩም ሆነ ስራ ሲለቁ ለባለስልጣኑ በወቅቱ ማሳወቅ እንደሚገባቸው የገለጹ ሲሆን ከ 2 አመት በላይ በስራ ላይ ያልነበሩ ባለሞያዎችን ሙያ ፈቃዳቸውን ሳያስተካክሉ መቅጠር እንደለሌባቸው አሳስበዋል።
ተቋማት ባለሞያዎችን ሲቀጥሩ የትምህርት ዝግጅት፣ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ፣ እና የሥራ ልምድ በአግባቡ በማረጋገጥ እንዲቀጥሩ አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን በተጨማሪም ብቃት ያላቸውን እና የሙያ ፍቃድ ማረጋገጫ ያላቸውን ባለሙያዎች መቅጠር የሚከሰቱ የህክምና ስህተቶችን ለመቀነስ እና የታካሚዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለውም አመላክቷዋል።
በመጨረሻም የጤና ተቋማት ባለቤቶች ተቋማቸውን በስታንዳርድ መሠረት በማስተዳደር፣ የብቃት እድሳትን በወቅቱ በማከናወን፣ ብቁና ፍቃድ ያላቸው ባለሙያዎችን በመቅጠር እና የአገልግሎት ጥራትን በቀጣይነት በማሻሻል ለህብረተሰቡ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት እንዲያቀርቡ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል ።
2 610
የግል ጤና ተቋማት ህብረተሰቡን በነጻ በማከም ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ ነው
================
ግንቦት 22/2018ዓ.ም
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን የቦሌ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከኮርያ አጠቃላይ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ለ500 የማህበረሰብ ክፍሎች ነፃ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን አሳይተዋል፡፡
የኮርያ ሆስፒታል ስራ አስኪያጂ ፕሮፌሰር ሶንግ ጁንግ ኪም ( Song Jung Kim) እንዳሉት በኮርያ ሆስፒታል EPCC የሚባል ነፃ ህክምና አገልግሎት የሚሰጥበት ትልቅ ፕሮግራም መኖሩን ጠቁመው ሆስፒታሉም ነፃ ህክምና አገልግሎት በመስጠቱና ህብረተሰቡን በማገልገላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀው ህክምና አገልግሎቱን እንዲሰጡ ለተባበሩና ምቹ ሁኔታ ለፈጠሩ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ህክምናውም ለ500 ሰዎች አጠቃላይ ህክምና፣ የውስጥ ደዌ ፣ ሰርጄሪ፣ የህፃናት፣ የአይን እና የጥርስ ነፃ ህክምና እንዲሁም መድሃኒት አገልግሎት መዘጋጀቱን በኮርያ ሆስፒታል የሞባይል ክሊኒክ ቡድን መሪ ዶ/ር ጂሬኛ ጫሊ ገልፀዋል፡፡
2 610
የሸማቾች ጤና ለመጠበቅ በምግብ ደህንነት ላይ ስጋት በሆነው ህገ ወጥ የምግብ ክለሳ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
26/8/2018ዓ.ም
ባለስልጣኑ የሸማቾችን ጤና ለመጠበቅ በምግብ ደህንነት ላይ ስጋት በሆነው የምግብ ክለሳን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን አጠናክሮ እየሰራ መሆኑን ገልጻል።
የምግብ ክለሳ የምግብን ጥራት፣ ደህንነት ወይም ንጥረ ይዘት የሚያሳንስ ወይም የሚቀይር ሕገ-ወጥ ድርጊት ነው። ይህም ለትርፍ ሲባል ውሃ፣ ኬሚካል ወይም ሌሎች ያልተፈቀዱ ንጥረ ነገሮችን ወደ ምግብ በመጨመር ወይም የምግቡን ተፈጥሯዊ ይዘት መለወጥ ነው።
የምግብ ክለሳ በወተትና የወተት ተዋጽኦዎች፣ በማር፣ በዘይት፣ በቅመማ ቅመሞች፣ በዱቄት እና በተለያዩ የታሸጉ ምግቦች ላይ በብዛት ይስተዋላል።
የዘርፉ ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ የምግብ ክለሳ የምግብ መመረዝ፣ የሆድና የአንጀት ሕመሞች፣ የጉበትና የኩላሊት ጉዳት እንዲሁም ረጅም ጊዜ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል።
በከተማዋ በተለይ ወተትን ፣ ማርን ፣ ፣ ቅቤን እና ሌሎች የባልትና ዉጤቶች ከበአድ ነገሮች ጋር መቀላቀል በብዛት እንደሚስተዋል ተገልጻል።
ባለስልጣኑ ችግሩን ለመቆጣጠር መደበኛ ፍተሻ፣ የላቦራቶሪ ምርመራ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና በሕግ ላይ የተመሰረቱ የክትትል እርምጃዎችን እያከናወነ ይገኛል በተጨማሪም በሕገወጥ የምግብ ክለሳ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ሲገኙ ምርቶቻቸውን የማስወገድ ፣ የንግድ ፈቃዳቸውን የማገድ ወይም የመሰረዝ እንዲሁም በሕግ መሠረት ሌሎች እርምጃዎች እንደሚወሰድባቸው የምግብና ጤና ነክ ቁጥጥር ዳሬክቶሬት አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው ገልጸዋል።
ዳሬክተሩ እንደገለፁት ባለስልጣኑ የተለያዩ የቁጥጥር ስራዎችን ቢሰራም በከተማዋ ህግን የሚተላለፉ የንግድ ተቋማት በመኖራቸው ህብረተሰቡ ፣ የምግብ ሽመታ ሲያካሂድ ከሕጋዊ እና ፈቃድ ካላቸው ተቋማት ብቻ እንዲገዛ፣ ጥርጣሬ ያለባቸውን ምርቶች በተቋሙ ነጻ ስልክ መስመር 8864 ጥቆማ በመስጠት የቁጥጥሩ አንድ አካል እንዲሆኑ አሳስበዋል። ለበለጠ መረጃ የባለስልጣኑ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችን ይከታተሉ
ፌስቡክ=https://web.facebook.com/facebook.comAAFDA
ዋትስአፕ=https://whatsapp.com/dl/
ዪቲዪብ=https://www.youtube.com/channel/UC_Oc0F_MUGBV2UcyiKtvijw
ቴሌግራም =https://t.me/AAFMHACA
ኢንስታግረም=addis ababa food and drug authority_aafda instagram
ሊንክዲን=https://www.linkedin.com/in/addis-ababa-food-and-drug-authority-aafda-10b172381?utm_source=share_via&utm_content=profile&utm_medium=member_android
2 610
የሸማቾች ጤና ለመጠበቅ በምግብ ደህንነት ላይ ስጋት በሆነው ህገ ወጥ የምግብ ክለሳ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
26/8/2018ዓ.ም
ባለስልጣኑ የሸማቾችን ጤና ለመጠበቅ በምግብ ደህንነት ላይ ስጋት በሆነው የምግብ ክለሳን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችን አጠናክሮ እየሰራ መሆኑን ገልጻል።
የምግብ ክለሳ የምግብን ጥራት፣ ደህንነት ወይም ንጥረ ይዘት የሚያሳንስ ወይም የሚቀይር ሕገ-ወጥ ድርጊት ነው። ይህም ለትርፍ ሲባል ውሃ፣ ኬሚካል ወይም ሌሎች ያልተፈቀዱ ንጥረ ነገሮችን ወደ ምግብ በመጨመር ወይም የምግቡን ተፈጥሯዊ ይዘት መለወጥ ነው።
የምግብ ክለሳ በወተትና የወተት ተዋጽኦዎች፣ በማር፣ በዘይት፣ በቅመማ ቅመሞች፣ በዱቄት እና በተለያዩ የታሸጉ ምግቦች ላይ በብዛት ይስተዋላል።
የዘርፉ ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ የምግብ ክለሳ የምግብ መመረዝ፣ የሆድና የአንጀት ሕመሞች፣ የጉበትና የኩላሊት ጉዳት እንዲሁም ረጅም ጊዜ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል።
በከተማዋ በተለይ ወተትን ፣ ማርን ፣ ፣ ቅቤን እና ሌሎች የባልትና ዉጤቶች ከበአድ ነገሮች ጋር መቀላቀል በብዛት እንደሚስተዋል ተገልጻል።
ባለስልጣኑ ችግሩን ለመቆጣጠር መደበኛ ፍተሻ፣ የላቦራቶሪ ምርመራ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና በሕግ ላይ የተመሰረቱ የክትትል እርምጃዎችን እያከናወነ ይገኛል በተጨማሪም በሕገወጥ የምግብ ክለሳ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ሲገኙ ምርቶቻቸውን የማስወገድ ፣ የንግድ ፈቃዳቸውን የማገድ ወይም የመሰረዝ እንዲሁም በሕግ መሠረት ሌሎች እርምጃዎች እንደሚወሰድባቸው የምግብና ጤና ነክ ቁጥጥር ዳሬክቶሬት አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው ገልጸዋል።
ዳሬክተሩ እንደገለፁት ባለስልጣኑ የተለያዩ የቁጥጥር ስራዎችን ቢሰራም በከተማዋ ህግን የሚተላለፉ የንግድ ተቋማት በመኖራቸው ህብረተሰቡ ፣ የምግብ ሽመታ ሲያካሂድ ከሕጋዊ እና ፈቃድ ካላቸው ተቋማት ብቻ እንዲገዛ፣ ጥርጣሬ ያለባቸውን ምርቶች በተቋሙ ነጻ ስልክ መስመር 8864 ጥቆማ በመስጠት የቁጥጥሩ አንድ አካል እንዲሆኑ አሳስበዋል። ለበለጠ መረጃ የባለስልጣኑ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችን ይከታተሉ
ፌስቡክ=https://web.facebook.com/facebook.comAAFDA
ዋትስአፕ=https://whatsapp.com/dl/
ዪቲዪብ=https://www.youtube.com/channel/UC_Oc0F_MUGBV2UcyiKtvijw
ቴሌግራም =https://t.me/AAFMHACA
ኢንስታግረም=addis ababa food and drug authority_aafda instagram
ሊንክዲን=https://www.linkedin.com/in/addis-ababa-food-and-drug-authority-aafda-10b172381?utm_source=share_via&utm_content=profile&utm_medium=member_android
ቲክቶክ=https:vm.tiktok.comZS9NqJyrTrUJ3-USEMd/
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
