Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 739
Obunachilar
-124 soatlar
+17 kunlar
-730 kunlar
Postlar arxiv
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በአጫጭር ስልጠና እያሰለጠናቸው ለሚገኙ ሰልጣኞች በተግባር የተደግፈ የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ሰጠ::
አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በSolar PV Instalation ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙትን 47 ሰልጣኞች
በ > Apply Principles of renewable energy Operation.
> Read and Interpret Plans and Specifications.
> Install DC/AC Wiring Systems
in conduit and Conneet Equipment.
> Determine and sizing of PV system.
> Perform Site Assessment.
Unit of Competency ላይ ሰልጣኞቹን በኦሲስ ኦርፋን ቻሪቲ ለ 2 ቀን የቆይ በተግባር የተደግፈ የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ተሰጥቷል::
ሰልጣኞቹ በንድፈ ሀሳብ ሲከተታተሉ የቆዩትን ስልጠና ስራ ቦታው ላይ በአካል ተገኝተው በተግባር የሰለጠኑ ሲሆን ይህም ሰልጣኞቹ በቀጣይ ወደስራ አለም ሲገቡ በእጅጉ እንደሚያግዛቸው ተገልጿል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 30/2016 ዓ.ም
Witness of Christ Church ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ::
የስልጠና ድጋፉ የተሰጠው ለኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፖርትመንት አሰልጣኝ መምህራን ሲሆን የስልጠናው ይዘትም በResidential and Commercial Electrical Systems in USA Standard ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልፅጿል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 30/2016 ዓ.ም
የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረፊያና ማረሚያ ቤት ጋር ለታራሚዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዙሪያ ከስልጠና እስከ ስልጠና ማዕከል አቅም ግንባታ መፍጠር የሚያስችል የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ።
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ከማረሚያ ቤቱ ጋር የተደረገው ስምምነት ኮሌጁ ያለበትን ያለበትን ማህበራዊ ኃላፊነት ከመወጣት ያለፈ በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ ታራሚዎች የበቁ ሞያተኞችን ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት ሁሉአቀፍ በሆነ ድጋፍና በጥምረት የመስራት የሁለትዮሽ መግባባት የፈጠረው ነው ብለዋል።
በስምምነት ፊርማው ላይ የማረሚያ ቤቱ ሀላፊ ረ/ኮሚሽነር ወንድሙ ደበላ እንደተናገሩት ስምምነቱ ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የሚሠጠዉን ስልጠና ከማጠናከር ባለፈ ታራሚዎች ታንፀዉ እንዲወጡ የአንድ አካል ሚና ብቻውን ውጤት ስለማያመጣ ኮከሌጁ ጋር የተደረገው ስምምነትና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም በማረሚያ ቤቱ እየተሰጠ የሚገኘውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ያግዝ ዘንድ አጠቃላይ የገንዘብ ግምታቸው ስድስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ ሶስት መቶ ብር የሚያወጡ ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለአውቶሞቲቭ እና ለፈርኒቸር ስልጠናዎች የሚያገለግሉ የተለያዩ የስልጠና ማቴሪያሎችና ማሽኖችን ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥር 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የአሰልጣኝ ልማት እና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የአሰልጣኝ ልማት ቡድን ለኢትዮ-ጣልያን እና ድሬዳዋ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የ ELECTRICAL ELECTRONICS አሰልጣኝ መምህራን ለ15ቀናት በ POER SYSTEMS SYMULATION AND ANALISIS, PSIM, MATLAB, ETAB, MULTYSYSTEM and MOTOR XP የሶፍትዌር እና የተግባር ስልጠናዎችን ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በተጋበዙ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠና አስጀምረዋል፤፤
ስልጠናው አሰልጣኞች ካላቸው እውቀት በተጨማሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካሉ አሰልጣኞች በሙያው እውቀትን እና ልምዶች ለመካፈል እንዲሁም የቴሙትስ አሰልጣኞች ያላቸውን የካበተ የተግባር እውቀት እና ልምዶችን ለዩኒቨርስቲ አሰልጣኞች የሚያካፍሉበት የሁለትዮሽ እውቀት ሽግግር የሚደረግበት አጋጣሚ መሆኑን ተጋባዥ አሰልጣኙ ብርሃኑ ደገፋ (ዶ/ር) ገልፀዋል፤፤
ቴክኒክና ሙያ በየወቅቱ የዘመነውን የቴክኖሎጂ እና የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት አድርጎ በየጊዜው ስልጠናውን የሚያዘምን እንደመሆኑ አሰልጣኞችም ብቁ እና ተወዳዳሪ ስልጠና አጠናቃቂዎችን ለማፍራት እንዲችሉ ወቅታዊ ስልጠናዎችን የሚያገኙበት ዕድሎችን እንደሚመቻችም የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፤፤
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 18/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ ብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ ይላል::
👉ኢትዮ-ጣሊያን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ለዳዊት አረጋውያን መርጃ የሙያ ድጋፍ አደረገ
የኮሌጁ ውድ-ወርክ ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት ዳዊት አረጋውያን መርጃ ከለጋሾች ያገኛቸውንና አገልግሎት መስጠት የማይችሉ አልጋዎችና ወንበሮችን የሚያስፈልጉ ግብአቶችን አሟልቶ በመጠገን አስረክቧል።
የጥገና ስራውን በመስራት በቅን መንፈስ ሙያዊ ድጋፍ ላደረጉት ለኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ምክትል ዲን አቶ ኤልያስ አህመድ እና የዲፓርትመንቱ ተጠሪ ለሆኑት አቶ ዮሴፍ እንዳልካቸው የአረጋውያን መርጃ ድርጅቱ ሀላፊ አቶ ዳዊት በቀለ በአረጋውያኑ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
Dawit Aregawiyan Merja
ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
