Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Kanalga Telegram’da o‘tish
Ko'proq ko'rsatish
1 739
Obunachilar
-124 soatlar
+17 kunlar
-730 kunlar
Postlar arxiv
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ አካሄደ።
መድረኩን የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የመሩት ሲሆን በተቋሙ የሚገኙ የስራ ሂደቶች የዘጠኝ ወር ተቋማዊ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለኮሌጁ ማኔጅመንት አቅርበዋል::
በመድረኩም በዋና ዋና ቁልፍ ተግባራት ፣ የማስፈፀም አቅም ፣በሀብት አጠቃቅም እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረገ የሪፖርት ግምገማ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን የቀጣይ ሦስት ወር የስራ አቅጣጫን በማስቀመጥም መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር ትግበራ ለሁለት ተከታታይ ዙሮች የህይወት ክህሎት ስልጠና ሰልጥነው ያጠናቀቁ ሁለት ሺ የሚጠጉ ሰልጣኞች የምርቃት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በድምቀት ተካሂዷል
በዚህ የሰልጣኞች የምርቃት ፕሮግራም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ በመገኘት ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አቶ ሀርቢ ተመራቂዎችን በቀጣይ በተለያዩ ፋብሪካዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ በምትቀላቀሉበት ወቅት በስነ-ምግባር የታነፃችሁና በታታሪነት የምታገለግሉ መሆን ይገባቹሀል በማለት የመከሩ ሲሆን፤ ለዚህ መርሀ ግብር መሳካትም አስታዎፆ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ለተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት በስልጠናው ወቅት ያሳዩትን የስራ ተነሳሽነትና ስነ-ምግባር በቀጣይም እንዲያጠናክሩት ተናግረዋል።
በተለይም አሁን ላይ በድሬዳዋ ኢንደስትሪ እየተስፋፋ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወጣቱም አስፈላጊውን ስነ-ግባርና ክህሎት አግኝቶ ዘርፉን እንዲቀላቀል እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች ከፍተኛ ሚና አንዳላቸው የገለፁት ደግሞ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ዳንኤል ተሬሳ ናቸው።
አቶ ዳንኤል አያይዘውም ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የወጣት ስራ አጦችን ቁጥር በመቀነሱ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
ተመራቂዎች በበኩላቸው በስልጠና ቆይታቸው በርካታ ክህሎት እንዳገኙ ገልፀው ለስልጠናው አዘጋጆችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
©️ የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የዐቢይ ፆምን ምክንያት በማድረግ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሄዱ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኝት በዐቢይ ጾም ስርዓተ ቅዳሴ አከናውነው ለሚመለሱ የክርስትና እምነት ተከታዮች የተለያዩ ምግቦች እና የታሸጉ ውሃዎችን በማቅረብ ማእድ የማጋራት መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 11/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ ልዑክ ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እና የስራ ጉብኝት አካሄደ::
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ የተጀመሩ የሪፎርምና የመደበኛ ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ የሚያስችለውን ጉብኝ ለማድረግ እንደተገኘም ነው የተገለፀው::
በነበረው መርሃ-ግብርም የኮሌጁ ማኔጅመንት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በኩል ለልዑካን ቡድኑ ባለፉት ስድስት ወራት በኮሌጁ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትን በተመለከት ኮሌጁ ያለውን አፈፃፀም ትኩረት በማድረግ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን የቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግም ከልዑካን ቡድኑ ጋር ውይይት ተደርጏል።
በተጨማሪም ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ ስልጠና የሚሰጥባቸውን ዲፖርትመንቶችና ወርክሾፖች ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በዚህም የተለያዩ የለውጥ ስራዎችንና ፕሮጀክቶችን መመክከት ችለዋል::
የዚህ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ዓላማም በትግበራ ወቅት የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ልማት እና የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት መሆኑም ተመላቷል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 08/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የዒድ-አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል::
ዒድ-ሙባረክ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጎ አድራጎት ክበብ የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ::
የበጎ አድራጎት ክበቡ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ይህን ድጋፍ ያደረገ ሲሆን በድጋፉም በማህበረሰቡ ጥቆማ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ለተለዩ 20 እቅመ ደካሞችን የአስቤዛና የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል::
ክብቡ እንደገለፀውም ይህ ተግባር ቀጥሎም በጣይ ቀናት የዐቢይ ፆምን ምክንያት በማድረግ በተመሳሳይ ድጋፍ የሚደረግም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 30/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የረመዳን ፆምን በማስመልከት የኢፍጣር መርሀ-ግብር አካሄዱ::
ይህ መርሃ-ግብር ድሬዳዋን በተለየ መልኩ የሀይማኖት አብሮነትና መደጋገፍ ያለባት ከተማ እንደሆነች የሚያጠናክር እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም በዚህ በረመዳንና በዐቢይ ፆም ወቅት ያሳየነውን መደጋገፍና አብሮነት በስራችን ላይም በማጠናከር ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስታውሰው የዛሬውን የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁና ለተሳተፉ የኮሌጁ ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በኢፍጣር መርሃ-ግብሩ ላይም የኮሌጁ አመራሮች፣ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ከተቋሙ ጋር በጋራ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል ።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው እለት በለገሐር አደባባይ ''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም '' በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ፡፡
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
