uz
Feedback
Amhara Media Corporation

Amhara Media Corporation

Kanalga Telegram’da o‘tish

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Amhara Media Corporation analitikasi

Amhara Media Corporation (@amharamassmedia) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 48 825 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 5 380-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 684-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 48 825 obunachiga ega bo‘ldi.

07 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -114 ga, so‘nggi 24 soatda esa -20 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlangan (Telegram tomonidan rasmiy tasdiq)
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 5.57% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 3.95% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 2 721 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 927 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 5 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

48 825
Obunachilar
-2024 soatlar
-557 kun
-11430 kun
Postlar arxiv
የአማራን ሕዝብ ወሰን እና ማንነት ጥያቄ አሳልፈው ላለመስጠት የሰላም አማራጭን መከተላቸውን የቀድሞ ታጣቂ መሪዎች ገለጹ። በአማራ ሕዝብ የማንነት እና ወሰን ጥያቄ ስም የሚደረጉ የተሳሳቱ እንቅስቃሴዎ
የአማራን ሕዝብ ወሰን እና ማንነት ጥያቄ አሳልፈው ላለመስጠት የሰላም አማራጭን መከተላቸውን የቀድሞ ታጣቂ መሪዎች ገለጹ። በአማራ ሕዝብ የማንነት እና ወሰን ጥያቄ ስም የሚደረጉ የተሳሳቱ እንቅስቃሴዎችን በመቃወም የመንግሥትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሕዝቡ መቀላቀላቸውን በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የአፋብን ከፍተኛ መሪዎች ተናግረዋል። ላለፉት ሦስት ዓመታት በጫካ በተሳሳተ መንገድ መቆየታቸውን የጠቀሱት የአፋብን የሃብት ልማት ምክትል ኀላፊ በለጠ አዱኛ ወደ ጫካ የገቡት የሕዝብን ጥያቄዎች ለማስመለስ አልመው እንደነበር ጠቅሷል።…

ከቃል ባለፈ የተግባር ውጤት። በአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት “የማንሠራራት ቀን” በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል። በዝግጅቱ ወቅት በዋና ዋና የልማት ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬ
ከቃል ባለፈ የተግባር ውጤት። በአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት “የማንሠራራት ቀን” በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሯል። በዝግጅቱ ወቅት በዋና ዋና የልማት ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን የሚያሳዩ የፎቶ አውደርዕይ እና ዶክመንተሪ ለዕይታ ቀርቧል። የርእሰ መሥተዳድር ጽሕፈት ቤት ምክትል ኀላፊ አብደላ ኑሩ እንደገለጹት ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገርም ኾነ እንደ ክልል ለወደፊት ዕድገት መሠረት የሚኾኑ…

ፍረወይኒ ኃይሉ፣ አለሽኝ ባወቅ እና አዲሱ ይሁኔ በአልቲሜት ሻምፒዮና ይሳተፋሉ። የዓለም አትሌቲክስ አልቲማት ሻምፒዮና የመጨረሻ የተሳታፊዎችን ዝርዝር ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም ተካትተዋ
ፍረወይኒ ኃይሉ፣ አለሽኝ ባወቅ እና አዲሱ ይሁኔ በአልቲሜት ሻምፒዮና ይሳተፋሉ።   የዓለም አትሌቲክስ አልቲማት ሻምፒዮና የመጨረሻ የተሳታፊዎችን ዝርዝር ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያውያን አትሌቶችም ተካትተዋል:: በዓመቱ ውስጥ በነበራቸው ስኬት መሠረት በሴት 3 ውድድሮች በወንድ ደግሞ በ1 ዘርፍ ብቻ አትሌቶች ለሚሊዮን ዶላሩ ድል ይፎካከራሉ። በዚህም መሠረት በታሪካዊው የዓለም አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒዮና ላይ አትሌቶቹ በጠንካራ ፉክክር የሚያደርጉ ሲኾን በወንዶች 5ሺህ ሜትር ቢኒያም መሐሪ እና አዲሱ ይሁኔ ሀገራቸውን ወክለው ይሮጣሉ።…

ጳጉሜን የሕሊና እና የውስጥ ማንነት መታደሻ ማድረግ ይገባል። በኢትዮጵያ የዘመን ቀመር 13ኛዋ ወር ጳጉሜን የቀን መቁጠሪያ መሸጋገሪያ ብቻ ሳትኾን የሕሊና እና የውስጥ ማንነት መታደሻ ወቅት መኾን እ
ጳጉሜን የሕሊና እና የውስጥ ማንነት መታደሻ ማድረግ ይገባል። በኢትዮጵያ የዘመን ቀመር 13ኛዋ ወር ጳጉሜን የቀን መቁጠሪያ መሸጋገሪያ ብቻ ሳትኾን የሕሊና እና የውስጥ ማንነት መታደሻ ወቅት መኾን እንዳለባት የሃይማኖት አባቶች አስገንዝበዋል። የአቡሻኸር እና የብሉይ ኪዳን መምህሩ አክሊሉ ብርሃኑ እንደገለጹት ጳጉሜን በዘመን አቆጣጠር ውስጥ ራሷን የቻለ ቀመርና አቆጣጠር ያላት ልዩ ወር ናት። በዚች አጭር ወር ታዲያ ኢትዮጵያውያን ከእርስ በእርስ…

ዘንድሮ ከምንጊዜውም በተሻለ ባሎንዶርን የሚያሸንፍበት አቋም ላይ እንደሚገኝ ኬልያን ምባፔ ተናገረ። የ27 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ አጥቂ ባለፈው የውድድር ዓመት ለክለቡ በተሰለፈባቸው 44 ጨዋታዎች 42
ዘንድሮ ከምንጊዜውም በተሻለ ባሎንዶርን የሚያሸንፍበት አቋም ላይ እንደሚገኝ ኬልያን ምባፔ ተናገረ።   የ27 ዓመቱ የሪያል ማድሪድ አጥቂ ባለፈው የውድድር ዓመት ለክለቡ በተሰለፈባቸው 44 ጨዋታዎች 42 ግቦችን አስቆጥሯል። ሪያል ማድሪድ ግን ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ነው ያጠናቀቀው። ከክለብ ባሻገር በብሔራዊ ቡድን ደረጃም ድንቅ የብቃት ጊዜን ያሳለፈው ኬልያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ምንም እንኳን ሀገሩ ፈረንሳይ 4ኛ ደረጃን ይዛ ብታጠናቅቅም እርሱ በግሉ በ10 ግቦች የወርቅ ጫማ አሸናፊ ኾኗል። የምንጊዜም የዓለም…

የተመዘገበው የመንገድ መሠረተ ልማት ዕድገት የክልሉን የማንሰራራት ጉዞ የሚያሳይ ነው። በአማራ ክልል በመንገድ መሠረተ ልማት ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ፈጣን ዕድገት የክልሉን የማንሰራራት ጉዞ በተጨባ
የተመዘገበው የመንገድ መሠረተ ልማት ዕድገት የክልሉን የማንሰራራት ጉዞ የሚያሳይ ነው። በአማራ ክልል በመንገድ መሠረተ ልማት ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው ፈጣን ዕድገት የክልሉን የማንሰራራት ጉዞ በተጨባጭ የሚያሳይ መኾኑን የክልሉ መንገድ፣ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ቢሮ ገልጿል። የቢሮ ኀላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ.ር) እንደገለጹት ቀበሌዎችን፣ ወረዳዎችን እና ዋና ዋና የመንገድ መስመሮችን ለማስተሳሰር በተከናወኑ ሥራዎች የክልሉን የመንገድ ሽፋን ከ36 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ ማድረስ ተችሏል።…

በድንቅ ብቃቱ ደጋፊውን እያሳመነ የመጣው ዝምተኛው ገዳይ። ክህሎቱን ጠንቅቀው በሚረዱት እና ለፍልስፍናቸው ተስማሚ መኾኑን በሚያውቁት አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቀዳሚ ተመራጭ ተጫዋች ነው ጀርመናዊው ካይ
በድንቅ ብቃቱ ደጋፊውን እያሳመነ የመጣው ዝምተኛው ገዳይ።   ክህሎቱን ጠንቅቀው በሚረዱት እና ለፍልስፍናቸው ተስማሚ መኾኑን በሚያውቁት አሠልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቀዳሚ ተመራጭ ተጫዋች ነው ጀርመናዊው ካይ ሃቨርትዝ። በሜዳ ውስጥ በሚያሳየው ረቂቅ ጥበብ እና ልዩ አጫወት የዘመናዊ እግር ኳስን ውበት በግልጽ የሚያንጸባርቅ ልዩ ተጫዋች መኾኑን እያሳየ ይገኛል። ሃቨርትዝ በሜዳ ላይ ከሚያሳያቸው አስደናቂ እንቅስቃሴዎች መካከል የተጋጣሚ ተከላካዮች ባልተገነዘቡት ቅጽበት ባዶ ቦታዎችን የመፈለግ እና የመጠቀም ችሎታው…

ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያን በመንገድ መሠረተ ልማት ስኬታማ ያደረጋት ምንድን ነው ? ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ለመንገድ መሠረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት መጠነ ሰፊ ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች።
ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያን በመንገድ መሠረተ ልማት ስኬታማ ያደረጋት ምንድን ነው ? ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ለመንገድ መሠረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት መጠነ ሰፊ ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች። በዚህም በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ከከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በ2010 ዓ.ም ከነበረው የ126 ሺህ 773 ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን በ2018 ዓ.ም ወደ 180 ሺህ 232 ኪሎ ሜትር አድጓል። ለስኬታማነቱ ምክንያቶችም ተቋማዊ አደረጃጀትን…

ከውድመት ወደ ማንሰራራት – አዲሱ የምዕራብ ጎጃም ገጽታ የምዕራብ ጎጃም ዞን አሥተዳደር ‘የማንሰራራት ቀንን በፍኖተ ሰላም እና ጅጋ ከተሞች የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን በመጎብኘት አክብሯል
ከውድመት ወደ ማንሰራራት – አዲሱ የምዕራብ ጎጃም ገጽታ የምዕራብ ጎጃም ዞን አሥተዳደር ‘የማንሰራራት ቀንን በፍኖተ ሰላም እና ጅጋ ከተሞች የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን በመጎብኘት አክብሯል። ጉብኝቱ የንጹህ መጠጥ ውኃን በሶላር የመተካት፤ የጌጠኛ ድጋይ ንጣፍ፤ በጸጥታ ችግር የወደመ የቢሮ ዕድሳት፤ በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ የተከናወኑ የዲጂታላይዜሽን ተግባራት እና ሌሎችም ሥራዎች ይገኙበታል። የጅጋ ከተማ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባ ምስጋናው ድንቁ ከተማ…

ጳጉሜ 2-13-2018.pdf20.16 MB

የሰኞ በኩር ጋዜጣ ጳጉሜን 2 -13 -2018 ዓ.ም ዕትም
የሰኞ በኩር ጋዜጣ ጳጉሜን 2 -13 -2018 ዓ.ም ዕትም

ማንሠራራት በእንጅባራ ከተማ ምን መልክ አለው? የእንስሳት ሀብት ልማቱን በማዘመን በኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን አወንታዊ ሚና ለማሳደግ እየተሠራ መኾኑን የእንጅባራ ከተማ አሥተዳደር አስታውቋል። በከተማ
ማንሠራራት በእንጅባራ ከተማ ምን መልክ አለው? የእንስሳት ሀብት ልማቱን በማዘመን በኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን አወንታዊ ሚና ለማሳደግ እየተሠራ መኾኑን የእንጅባራ ከተማ አሥተዳደር አስታውቋል። በከተማ አሥተዳደሩ የማንሠራራት ቀንን ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት ተክብሮ ውሏል። ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ በኾነ ወጪ በግንባታ ላይ የሚገኘው ፉችታ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት፤ በኩታ ገጠም እየተሠራ ያለው የወተት ሀብት ልማት እና…

የመድኃኒት አቅርቦት ችግርን እየፈታ ያለው የማኅበረሰብ መድኃኒት ቤት። የደቡብ ጎንደር ዞን እና የፋርጣ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ጳጉሜን ሁለት “የማንሥራራት ቀን” ምክንያት በማድረግ የልማት ሥራዎ
የመድኃኒት አቅርቦት ችግርን እየፈታ ያለው የማኅበረሰብ መድኃኒት ቤት። የደቡብ ጎንደር ዞን እና የፋርጣ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ጳጉሜን ሁለት “የማንሥራራት ቀን” ምክንያት በማድረግ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል። በዕለቱ በተካሄደው የጉብኝት መርሐግብር የሕዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ፕሮጀክቶች ተጎብኝተዋል። አርሶ አደሮች የነበረባቸውን የመድኃኒት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የተቋቋመው የማኅበረሰብ መድኃኒት ቤት የጉብኝቱ አካል ነው። የጉብኝቱ ተሳታፊ ሲሳይ አያሌው እንደገለጹት መድኃኒት ቤቱ አርሶ አደሮች…

“ለቃችሁ ውጡልን” የቫሌንሲያ ደጋፊዎች ትላንት ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም በስፔን ላሊጋ 4ኛ ሳምንት በሜዳቸው ዲ ሜስታላ ስታዲየም ባርሴሎናን የጋበዙት ቫሌንሲያዎች 5 ለ 0 በኾነ ውጤት ተሸንፈዋል፡፡
“ለቃችሁ ውጡልን” የቫሌንሲያ ደጋፊዎች ትላንት ጳጉሜን 1/2018 ዓ.ም በስፔን ላሊጋ 4ኛ ሳምንት በሜዳቸው ዲ ሜስታላ ስታዲየም ባርሴሎናን የጋበዙት ቫሌንሲያዎች 5 ለ 0 በኾነ ውጤት ተሸንፈዋል፡፡ የቫሌንሲያ ደጋፊዎችም ከዚህ ከባድ ሽንፈት በኋላ በባለቤቶቹ እና ስሜት አልባ ናቸው ባሏቸው ተጫዋቾች ላይ የበረታ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡ በሜዳቸው በባርሴሎና 5ለ0 ከተሸነፉበት አሳፋሪ ውጤት በኋላ በቫሌንሲያ ደጋፊዎች ከፍተኛ ቁጣ የተነሳ ሲኾን በክለቡ ላይ እየደረሰ ያለውን…

“ኢትዮጵያም በተግባር እያንሠራራች ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የከተሞቻችን ማንሠራራት፥
“ኢትዮጵያም በተግባር እያንሠራራች ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የከተሞቻችን ማንሠራራት፥ የሀገራችን ማንሠራራት መልክ ነው ብለዋል። ደረጃቸውን የጠበቁ ከተሞች የሥልጣኔ መስታወቶች ናቸው። የሀገርን የዕድገት ደረጃ፣ የሕዝቦችን የአስተሳሰብ ከፍታ፣ የአካባቢ ጥበቃ ቁርጠኝነትና የልማት አቅጣጫ በግልጽ የሚያሳዩ ሕያው ገጾች ናቸው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ሀሳብ አመንጪነት ከአዲስ አበባ ተነስቶ…

ባሕርዳር የኢትዮጵያን የስኬት ጉዞ እያሳየች ነው። የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር “የኢትዮጵያ ማንሠራራት” በሚል መሪ መልዕክት ጳጉሜን ሁለት “የማንሠራራት ቀንን “በከተማው የተሠሩ የመሠረተ ልማት ሥ
ባሕርዳር የኢትዮጵያን የስኬት ጉዞ እያሳየች ነው። የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር “የኢትዮጵያ ማንሠራራት” በሚል መሪ መልዕክት ጳጉሜን ሁለት “የማንሠራራት ቀንን “በከተማው የተሠሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን በመጎብኘት አክብሯል። ጉብኝቱም በዘመናዊ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የታጀበ ነው። የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ኢትዮጵያ ትላልቅ የልማት ሥራዎችን በማከናወን የትንሣኤ ጉዞ ላይ ትገኛለች ብለዋል። ባሕር ዳር ከተማ ከኮሪደር…

ለጥንቃቄ! በበዓል ወቅት ግብይት በሀሰተኛ የብር ኖቶች እንዳይታለሉ ይጠንቀቁ። ትክክለኛ የብር ኖቶችን ከሐሰተኛ ኖቶች ለመለየት ከስር የተቀመጡ የመለያ መንገዶችን ልብ ይበሉ።
+2
ለጥንቃቄ! በበዓል ወቅት ግብይት በሀሰተኛ የብር ኖቶች እንዳይታለሉ ይጠንቀቁ። ትክክለኛ የብር ኖቶችን ከሐሰተኛ ኖቶች ለመለየት ከስር የተቀመጡ የመለያ መንገዶችን ልብ ይበሉ።

“የታሪክ ተወቃሽ ላለመኾን ከጓደኞቼ ጋር የሰላም አማራጭን ተቀብያለሁ” ብሬኑን ይዞ ሰላምን የመረጠው ወጣት በሰሜን ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች የሰላምን አማራጭ በመቀበል በአዲስ ዓመት ዋ
“የታሪክ ተወቃሽ ላለመኾን ከጓደኞቼ ጋር የሰላም አማራጭን ተቀብያለሁ” ብሬኑን ይዞ ሰላምን የመረጠው ወጣት በሰሜን ጎንደር ዞን የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች የሰላምን አማራጭ በመቀበል በአዲስ ዓመት ዋዜማ ለሕዝቡ የሰላም ስጦታ እያበረከቱ ነው። በክልሉ የጸጥታ መዋቅር ውስጥ ለ11 ዓመት አገልግሏል። በ2015 ዓ.ም ደግሞ ጥያቄዎችን በአፈሙዝ እናስፈታለን በሚል ወደ ጫካ መግባቱን ያስታውሳል። በሰሜን ጎንደር ዞን ሲንቀሳቀሱ በቆዩ ታጣቂዎች የሻለቃ መሪ ነበር አምሳያው ገብሬ። በሕዝብ ላይ እገታ፤…

በቴክኖሎጂ የተቃኘው የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ! ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ የቅንጦት ጉዳይ አይደለም። የሀገራት ብሔራዊ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ መለኪያ ወደ መኾን ተሸጋ
በቴክኖሎጂ የተቃኘው የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ! ዛሬ ላይ ቴክኖሎጂ የቅንጦት ጉዳይ አይደለም። የሀገራት ብሔራዊ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ መለኪያ ወደ መኾን ተሸጋግሯል። ኢትዮጵያም ይህንን በመረዳት ጉዞዋን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ አድርጋለች። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ.ር) ኢትዮጵያ የሰው ሠራሽ አስተውሎትን አቅም በተግባር እያረጋገጠች እና ለአፍሪካ ኢኖቬሽን መንገድ እየጠረገች ትገኛለች ብለዋል።…

“ከተዘጉ ፋብሪካዎች ወደ ምርት ትንሣኤ” ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ከባሕላዊ ምርት ወደ ዘመናዊ ተወዳዳሪ ማኑፋክቸሪንግ በመሸጋገር ለውጥ እያስመዘገበች እና እያንሠራራች ትገኛለች። የኢንዱ
“ከተዘጉ ፋብሪካዎች ወደ ምርት ትንሣኤ” ኢትዮጵያ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ከባሕላዊ ምርት ወደ ዘመናዊ ተወዳዳሪ ማኑፋክቸሪንግ በመሸጋገር ለውጥ እያስመዘገበች እና እያንሠራራች ትገኛለች። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ከማስፋፋት ባለፈ የጨርቃ ጨርቅ፣ የሲሚንቶ፣ የቆዳ፣ የሌጦ እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የማምረት አቅም እያደገም መጥቷል። ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድልም ፈጥሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) “የኢትዮጵያ ታምርት” እንቅስቃሴዎች ሀገራዊ ኢኮኖሚውን ስር…