uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 332-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 177-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

05 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 18 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.66% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.09% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 297 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 344 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 06 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-424 soatlar
-77 kunlar
+1830 kunlar
Postlar arxiv
መሠረታዊ ሠራተኛ ማህበሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ስኬታማ ስራ አከናውኛለሁ አለ …………..….///………….. የተቋሙን ውጤታማነት እና ምርታማነት ባማከለ መልኩ የሠራተኛውን ጥቅም ለማስከበር የሚያስችሉ ስኬታማ ሥራዎች ማከናወኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አስታወቀ፡፡ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እንደተናገሩት ቀደም ሲል እስከ አንድ ዓመት እና ከዚያ በላይ ጊዜ ይወስድ የነበረውን የደረጃ ዕድገትና ዝውውር ከተቋሙ አመራሮች ጋር በቅንጅት በመስራትና አሠራሩን በማዘመን ከሁለት ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ ተችሏል፡፡ የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በቅጥር፣ በደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዲሁም በትምህርት ዕድል ይበልጥ ተጠቃሚ የሚያደርጉ መመሪያዎች ተግባራዊ መደረጋቸውንም ገልፀዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ለህክምና ከሚወጣው ወጪ 10 በመቶ ያህሉ ከሠራተኞች የሚሸፈን መሆኑን የጠቆሙት ሊቀመንበሩ የስኳር፣ የኤችአይቪ፣ የልብህመም እና የደም ግፊት ህመሞች ወጪያቸው መቶ በመቶ በተቋሙ እንዲሸፈን መደረጉን አስታውቀዋል፡፡ የዘርፍ ማህበራትን ከማጠናከር አኳያም የስራ አስፈፃሚና የኦዲት ኮሚቴ አባላትን ያካተተ የመስክ ስምሪት በማከናወን የተጓደሉ የዘርፍ አመራሮች እንዲሟሉ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ከማህበር አባላት ጋርም ሰፊ ውይይት በማድረግ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት እየተሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ከማህበር አባላት የሚቀርቡ አቤቱታዎችን ከየዘርፉ የሥራ አመራሮች ጋር በመሆን ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡ የተቋሙን አፈፃፀም ለማሳደግና የሠራተኛውን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከተቋሙ የሥራ አመራሮች ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ የሠራተኛው ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ሊረጋገጥ የሚችለው የተቋሙ ውጤታማነትም ሲያድግ በመሆኑ ሁሉም ሠራተኞች ለተቋሙ ዕድገት እና ብልፅግና በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ሊቀመንበሩ አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 29 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሠላም አደረሳችሁ!! በዓሉ የሠላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞታችን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

photo content
+2

ኢትዮ ቴሌኮም ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በ8100 ያሰባሰበውን ከ122 ሚሊዮን ብር በላይ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስረከበ ............////.......... ኢትዮ ቴሌኮም በ8100 አጭር ቁጥር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሰበሰበውን ገንዘብ ዛሬ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስረክቧል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬህወት ታምሩ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ እንደገለፁት፣ በ1ኛ ዙር 80 ነጥብ 3 ሚሊዮን እንዲሁም በ2ኛ ዙር 49 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ከደንበኞች ተሰብስቧል። በአሁኑ የ8100 የ3ኛ ዙር የገቢ ማሰባሰብ ላይ 122 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር መሰብሰቡንና እስካሁን ከተሰበሰበው ገንዘብ እንደሚልቅ አስታውቀዋል። በሶስቱ ዙሮች ከ252 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በመጥቀስ ደንበኞች ስላደረጉት አስተዋፅኦ አመስግነዋል። ኢትዮ ቴሌኮም በተቋሙና በሰራተኞቹ ስም 111 ሚሊየን ብር የቦንድ ግዢ ማከናወኑንም ወ/ት ፍሬህይወት ተናግረዋል። የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ም/ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሔ በበኩላቸው የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከ15 ቢሊየን ብር በላይ በቦንድ ግዢና በልገሳ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። የ8100 የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብርም የግድቡ ግንባታ የሁሉም ኢትዮጵያዊ አጀንዳ እንዲሆን ያደረገና ሁሉም አሻራውን እንዲያሳርፍ እድል የሰጠ ነው ብለውታል። በመሆኑም ገቢ ማሰባሰቢያው ለቀጣዮቹ 6 ወራት እንዲቀጥል ኢትዮ ቴሌኮምን ጠይቀው ይሁንታ አግኝተዋል። የተሰባሰበውን ገንዘብ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ፍሬህይወት ታምሩ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ አስረክበዋል። አቶ አሸብር ባልቻም መላው ህብረተሰብ በ8100 በኩል ሲያደርግ ለቆየው ድጋፍ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስራ አመራር ቦርድ፣ በማኔጅመንቱና በሰራተኞቹ እንዲሁም በፕሮጀክቱ ስም አመስግነዋል። የተጀመረው ድጋፍ ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 14 ቀን 2013 ዓ/ም

ኢትዮ ቴሌኮም በ8100 የሰበሰበውን ገንዘብ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ ያስረክባል ……………////…………. ኢትዮ ቴሌኮም በ8100 አጭር ቁጥር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሰበሰበው
ኢትዮ ቴሌኮም በ8100 የሰበሰበውን ገንዘብ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ ያስረክባል ……………////…………. ኢትዮ ቴሌኮም በ8100 አጭር ቁጥር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሰበሰበውን ገንዘብ ዛሬ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሊያስረክብ ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ከታላቁ የኦትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በ8100 አማካይነት ለግድቡ ግንባታ የሚውል ገንዘብ ከደንበኞ ቹ ሲያሰባስብ መቆየቱ ይታወሳል። በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የመገናኛ ብዙሃን በተገኙበት የርክክብ ስነስርዓቱ የሚከናወን ይሆናል። በስነስርዓቱ ላይ ስለሚነሱ ጉዳዮችና ስለተሰባሰበው ገንዘቡን መጠን ዘግየት ብለን ዝርዝር መረጃዎች ይዘን እንመለሳለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 14 ቀን 2013 ዓ/ም

የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ከግሪድ ጋር ማገናኘት ተችሏል .............////.......... የተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ከብሔራዊ የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር የማገናኘት ስራ በስኬት ተከናውኗል። ጣቢያው ከብሔራዊ የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር የሚገናኝበት መስመር በመቋረጡ ምክንያት ለወራት ኃይል ማመንጨት አቁሞ እንደነበር ይታወሳል። ከመጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ግን በጊዜያዊነት ከሲስተም ጋር ሳይገናኝ ራሱን በራሱ እየተቆጣጠረ (Isolated mode) ኃይል ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከግሪድ ጋር እንዲገናኝ ተደርጓለ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከመሆኒ መቀሌ ያለው መስመር ከተከዜ- መቀሌ ከተዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ኃይል እንዲያገኝ ማድረግ ተችሏል። ቀደም ሲል ከአላማጣ መኾኒ አሸጎዳ መቀሌ የሚሄደው መስመር ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት የትግራይ ክልል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ እንደነበር መግለፃችን አይዘነጋም። ሚያዝያ 13 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

የህዳሴ ግድብ የታችኛው የውሃ ማስተንፈሻዎች ተጠናቀው ስራ ጀመሩ ………………./////……………. የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የታችኛው የውሃ ማስተንፈሻ ሁለት ቱቦዎች(Bottom outlet) ተጠናቅቀው ሥራ የሙከራ ሥራ ጀምረዋል፡፡ የውሃ ማስተንፈሻዎቹ የዓባይን ወንዝ አጠቃላይ ዓመታዊ የውሃ ፍሰት መጥነው የማሳለፍ አቅም እንዳላቸው የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ገልፀዋል፡፡ የውሃ ማስተንፈሻዎቹ የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት በዓመት በአማካይ የሚያገኙትን የውሃ ፍሰት እንደማያስተጓጎል ማረጋገጫ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ ጠ/ሚር ዶክተር አብይ አህመድ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት ከመከናወኑ በፊት በተጠናቀቁት የውሃ ማስተንፈሻዎች አማካኝነት ተጨማሪ ውሃ እንደምትለቅ እና መረጃም እንደምታጋራ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም.

ለግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፓርኮች የኃይል አቅርቦት ስምምነት ተፈረመ ……………/////…………….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያየ የሀገሪቱ ክፍል ለተገነቡት የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት መሰረተ ልማት ለመዘርጋት የሚያስችል ስምምነት ከሁለት የቻይና ኩባንያዎች ጋር ተፈራረመ፡፡ ሲኖ ሀይድሮ እና ሲዩአን ኤሌክትሪክ (sieyuan electric CO. LTD) ከተሰኙ ሁለት የቻይና ኩባንያዎች ጋር ሚያዚያ 6 ቀን 2013 ዓ.ም የተፈረመው ስምምነት ለቡሬ፣ ለበአከር፣ የወይናንታ እና የገንዳ አርባ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ለዳንሻ፣ ሁመራ፣ ጎንደር II ማከፋፈያ ጣቢያዎች የዲዛይን፣ የዕቃዎችን ፍብረካና አቅርቦት፣ የግንባታ እንዲሁም የሙከራና ፍተሻ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የየኩባንያዎቹ ተወካዮች ተፈራርመዋል፡፡ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት መንግስት የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ የሚገኝ በመሆኑ ስምምነቱ ለኢንዱስትሪ ፓርኮቹን የኃይል ጥያቄ ለመፍታት ከፍተኛ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቶችን ግንባታ በተቀመጠላቸው መርሃ ግብር መሰረት ለማጠናቀቅ ኩባንያዎች ሌት ተቀን መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል፡፡ ተቋሙ ፕሮጀክቶቹ በሚገነቡባቸው አካባቢዎች ከወሰን ማስከበር ነፃ ከማድረግ ጀምሮ ለኩባንያዎች አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል፡፡ የኩባንያዎቹ ተወካዮች በበኩላቸው ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ በተለያዩ የኤሌክትሪክ ኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ ፕሮጀክቶችን በመገንባትና ዕቃ በማቅረብ ተሳትፎ እንደነበራቸው አስታውሰው በስምምነቱ መሰረት የፕሮጀክቶችን ሥራ በጥራትና በተቀመጠላቸው መርሃ ግብር መሰረት አጠናቆ ለማስረከብ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡ ኩባንያዎቹ በቀጣይ ከተቋሙ ጋር አብሮ የመስራት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡ በግዥ መምሪያ የፕሮጀክት ግዥ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሁሴን አደም በበኩላቸው እንደገለጹት ከሲዩአን ኤሌክትሪክ ኩባንያ ጋር የተካሄደው ስምምነት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የማከፋፈያ ጣቢያ የዲዛይን፣ የዕቃ ማምረትና አቅርቦት፣ የግንባታ፣ የሙከራና ፍተሸ ስራዎችን ለማከናወን እንዲሁም ለጎንደር II ባለ 230 ኪሎ ቮልትና ለሁመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማሻሻያ ስራ እና አዲስ ለሚገነቡት ለበአከርና ዳንሻ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የሚያገለገሉ ዕቃዎችን ለማቅረብ ነው፡፡ የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክትን በ14 ወራት ውስጥ በማጠናቀቅ ለማስረከብ እና ከ15 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይና ከ118 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን አቶ ሁሴን ተናግረዋል፡፡ አቶ ሁሴን አክለውም ለጎንደር II፣ ለዳንሻ፣ ለበአከርና ለሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የሚዉለውን ዕቃ ለማቅረብ የተካሄደው ስምምነት ከ10 ነጥብ 8 ሚሊዬን ዶላር በላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይ ከሲኖ ሀይድሮ ኩባንያ ጋር የተካሄደው ስምምነት በምስራቅ ሸዋ ዞን ባቱ አካባቢ ለሚገነባው የገንዳ አርባ እና በይርጋለም አካባቢ ለተገነባው የወይናንታ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርክ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የዲዛይን፣ የፍብረካና አቅርቦት፣ የግንባታ እንዲሁም የሙከራና የፍተሻ ስራዎችን ለማከናወን ነው፡፡ የገንዳ አርባንና የወይናንታን የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ፕሮጀክት በ12 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እና ለዚህም ከ13 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላርና ከ14 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ስምምነት መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ለሁሉም ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገው ገንዘብ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 07 ቀን 2013 ዓ.ም.

photo content

photo content

photo content

photo content

የአዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከዕቅድ በላይ ኢነርጂ አመነጨ …………../////........... የአዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 75 ነጥብ 45 ጌጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማምረት አቅዶ 89 ነጥብ 01 ጌጋ ዋት ሰዓት ማመንጨቱን የአዋሽ II እና III የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ኃላፊ አቶ ጌታቸው አበበ አስታወቁ፡፡ ኃላፊው እንደገለፁት የአዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግን 92 ነጥብ 29 ጌጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማምረት አቅዶ 65 ነጥብ 8 ጌጋ ዋት ሰዓት ማምረት ችሏል፡፡ የአዋሽ III የኃይል ማመንጫ ጣቢያ አፈፃፀም ዝቅ ሊል የቻለው በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ ባጋጠመው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሳቢያ ጣቢያው ለአስር ሳምንታት ኃይል ማመንጨት በማቆሙ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የአዋሽ II የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግን በእንቦጭ ወረርሽኝ ምክንያት ለ1 ወር ኃይል ማመንጨት አቁሞ የነበረ ቢሆንም የዘጠኝ ወር አፈፃፀሙ ግን ከዕቅዱ ከፍ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያዎቹ በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ በእንቦጭ አረም እና በጎርፍ ምክንያት ለተወሰኑ ሳምንታት አገልግሎት መስጠት አቁመው የነበረ ቢሆንም በተደጋጋሚ በተሰሩ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎች ጣቢያዎቹ የተሻለ የኤሌክትሪክ ኢነርጂ በማምረት ላይ ይገኛሉ፡፡ የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሮቤል አበበ በበኩላቸው የጎርፍ መከላካያ እና ሌሎች ያልጠናቀቁ ቀሪ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን የጣቢያውን ደህንነት ለማስጠበቅ እየተሰራ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ የኃይል ማመንጫውን ለማደስ የሚያስችል ጥናት ተጠናቆ ለሥራ አመራሩ ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች መጀመራቸውን አቶ ጌታቸው ጠቁመዋል፡፡ ጣቢያው የአዋሽ ተፋፈስ አካል ከመሆኑም ባሻገር በጣቢያው ክልል ውስጥ የተለያዩ የዱር አራዊቶች የሚገኙበት ሥፍራ በመሆኑ ለቱሪስት መስህብነት ተመራጭ ሊያደርገው እንደሚችል ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የአዋሽ II እና III የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፡፡ ሚያዝያ 04 ቀን 2013 ዓ.ም.

photo content

photo content

photo content

photo content