uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 560 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 357-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 160-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 560 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 27 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.05% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.01% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 053 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 491 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 560
Obunachilar
-724 soatlar
+147 kunlar
+2730 kunlar
Postlar arxiv
photo content

ፕሮጀክቱ የማህበራዊ ኃላፊነትና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎችን እያከናወነ ነው .....//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ - ኬኒያ ፖወር ሲስተም ኢንተርኮኔክሽን ፕሮጀክት  የልማት ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋምና የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንደገለጹት የኢትዮ - ኬኒያ ኮንቨርተር ጣቢያ ከተገነባበት የሶዶ ዙሪያ ወረዳ 54 ሰዎች ካሳ ተክፍሏቸው ተነስተዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ የተከናወነበት ቦታ የልማት ተነሺዎች የከብቶቻቸው የግጦሽ ሥፍራ የነበረ በመሆኑ ከካሳ ክፍያ በተጨማሪ የልማት ተነሺዎቹን በዘላቂነት ለማቋቋም ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ የከብቶችና የዶሮ መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ መገንባቱን ተናግረዋል። የመኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካውን በሁለት ወራት ውስጥ በማጠናቀቅ በማህበር ለተደራጁት የልማት ተነሺዎች በማስተላለፍ በባለቤትነት እንዲያስተዳድሩት እንደሚደረግ ገልጸዋል። ፋብሪካው ሲጠናቀቅ በሠዓት 1 ነጥብ 8 ቶን የእንስሳትና 1 ነጥብ 2 ቶን የዶሮ መኖ እንደሚያመርት እና ይህም የልማት ተነሽዎችን በዘላቂነት ከማቋቋም ባሻገር በአካባቢው ያለውን የመኖ እጥረት በመቅረፍ በኩል ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ከ160 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ ኮንቨርተር ጣቢያው ከተገነባበት ዙሪያ እስከ አራት ኪሎ ሜትር ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመብራት ተጠቃሚ ማድረጉን አቶ ቴዎድሮስ አስታውቀዋል። ፕሮጀክቱ በሚያከናውናቸው የመልሶ ማቋቋምና የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች የአካባቢው ማህበረሰብ በፕሮጀክቱ ላይ ያለው የእኔነት ስሜት እያደገ መምጣቱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ በዚህም በአካባቢው ቀደም ሲል በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ይፈጸም የነበረው ስርቆት እየቀነሰ መምጣቱን አስረድተዋል፡፡ የልማት ተነሽ የሆኑት ቀሲስ አርካ አባተ በበኩላቸው ለፕሮጀክቱ ግንባታ ከመሬታቸው ሲነሱ በወቅቱ ካሳ እንደተከፈላቸው ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የልማት ተነሽዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም እየገነባ ያለውን የመኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ለመረከብና በባለቤትነት ለማስተዳደር የልማት ተነሽዎቹ በማህበር ተደራጅተው የግንባታውን መጠናቀቅ በጉጉት እየጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ቀሲስ አርካ ፕሮጀክቱ የልማት ተነሽዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም እና የአካባቢውን ማህበረሰብ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ላከናወናቸው ተግባራት ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ እየሠራ ነው .......//....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለጹት ከከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችና ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት እያደገ መጥቷል። ተቋሙ በሀገሪቱ ያለውን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን አዳዲስ የኃይል ማመንጫዎችን፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እየገነባ ይገኛል። የማመንጨት አቅሙን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና ኮይሻን ጨምሮ አምስት የኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል ብለዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ የተጀመሩት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በአሁኑ ወቅት ያለውን የሀገሪቱን የማመንጨት አቅም ከእጥፍ በላይ በማሳደግ የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር ለበርካታ የአፍሪካ አገራት ኃይል ለማቅረብ ምቹ መደላድልን ይፈጥራል፡፡ ነባር የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ከማሳደግና ያረጁ የማስተላለፊያ መስመሮችን ከመቀየር ባሻገር እንደ አውሮፓያን አቆጣጠር በ2030 የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን 78 በመቶ ለማድረስ አቅዶ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለጻ ተቋሙ አሁን ላይ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቀለበት(ሪንግ) በማድረግ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ጥረት እያደረገ ከመሆኑም ባሻገር ተቋሙ የኃይል ብክነትን የሚቀንሱና አሰራሩን የሚያዘምኑ ስማርት ሜትር፣ ሳፕ እና ሳውዝ ክላውድ የሚባሉ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ አውሏል፡፡ ሆኖም ተቋሙ የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላትና ተደራሽነቱን ለማሳደግ በሚያደርገው ጥረት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ፈተና እንደሆነበትም አብራርተዋል፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆቱ መጠኑ ቢለያይም በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እያጋጠመ ያለ ችግር መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ ለዚህም የሕግ ክፍተት፣ የፖለቲካ አመራሩ ቁርጠኝነት ማነስ እና የግንዛቤ እጥረት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ለአብነትም በ2016 በጀት ዓመት ተቋሙ በስርቆት ምክንያት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም እሱን ለመጠገን ደግሞ 200 ሚሊዮን ብር በማውጣት በድምሩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት ጠቁመዋል፡፡ የጎረቤት ሀገራትንና የዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ልምድ በመቅሰም፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፣ የፖለቲካ አመራሩንና ማህበረሰቡን በማሳተፍ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ተቋሙ እየሰራ ይገኛልም ብለዋል፡፡ የተቋሙ ሀብት የሀገር ሀብት መሆኑን በመገንዘብ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

#EEP #EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል። ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 - 3:30 ሰዓት በአማርኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም በዜናዎች ቻናል ዘወትር እሁድ ምሽት ከ12:10 - 12:40 ሰዓት በኦሮምኛ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ቋንቋዎች ቻናል። ዘወትር ዓርብ ምሽት ከ2:30 - 3:00 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ በብሄራዊ ሬዲዮ  ይቀርባል። በቅርብ ቀን ይጠብቁን! https://www.youtube.com/watch?v=FzCdm5sI5KU የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም

የምስራቅ አንድ ሪጅን ለፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ተጠቃሚዎች ሥልጠና እየሰጠ ነው ………///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በሥራ ላይ በሚውለው የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ዙሪያ ለተጠቃሚዎች ሥልጠና እየሰጠ መሆኑን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡ የሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንዳስታወቁት በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበረው የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል በሪጅኑ እየተከናወነ የሚገኘውን የጥገና ሥራ ለማዘመን ያስችላል፡፡ ሠራተኛው የሞጁሉን አሰራር ተረድቶ በአግባቡ ተግባራዊ እንዲያደርገውና የተቋሙን ዕቅድ እንዲያሳካ ሪጅኑ በተለያዩ ዙሮች ለተጠቃሚዎች ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በሪጅኑ አዘጋጅነት በሦስት ዙሮች በሚሰጠው ሥልጠና ላይ በሪጅኑ ሥር የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች፣ የማስተላለፊያ መስመርና የማከፋፈያ ጣቢያ የጥገና ክፍል ባለሙያዎች እና ኦፕሬተሮች እንደሚሳተፉ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሥልጠናው ለማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊዎች በመሰጠት ላይ እንደሆነ ገልፀው በቀጣይ ለጥገና ክፍል እና ለኦፕሬተሮች ተመሳሳይ ሥልጠና በሁለት ዙሮች እንደሚሰጥ አመልክተዋል፡፡ በመረጃ አሰባሰብ፣ በጥገና አሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦትና አስተዳደር፣ በመሳሪያዎች አጠቃቀም እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገው ስልጠና በንድፈ ሀሳብና በተግባር በመታገዝ እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ወርዲ ገለፃ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ሲተገበር የተቋሙን ብሎም የሪጅኑን የጊዜ፥ የገንዘብ እና የዕቃዎችን አጠቃቀምና አያያዝ በማሻሻል ሥራዎችን ያቀላጥፋል። ከሳፕ ሥልጠና በተጨማሪ የሠራተኛውን አቅም ሊያሳድጉ የሚችሉ የተለያዩ ሥልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያነሱት ዳይሬክተሩ ለዚህም ከሠራተኛው ግብዓት በመሰብሰብ እና ሪጅኑ ያስፈልጋሉ ብሎ በለያቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠናዎችን በዕቅድ ላይ ተመስረቶ ለመስጠት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል ተጠቃሚዎች ሥልጠና በእያንዳንዱ ዙር ለአስር ቀናት የሚሰጥ ይሆናል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል። ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 ሰዓት በኋላ ይቀርባል። በቅርብ ቀን ይጠብቁን! https://www.youtube.com/watch?v=FzCdm5sI5KU የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም

በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳይጀመሩ የቆዩ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ ነው ……..///…….. ከሦስት ዓመት በፊት ለግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች ኃይል ለማቅረብ በዕቅድ ተይዘው የነበሩ ፕሮጀክቶችን በተያዘው በጀት ዓመት ለማስጀመር እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ ገለፀ። በዘርፉ የአፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ታረቀኝ እንንደገለፁት ለደብረ ማርቆስ-ቡሬ፣ ገንዳ አርባ፣ ወይናታ እና ጎንደር-ዳንሻ- ሁመራ- ባዕከር የግብርና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ኃይል የሚያቀርቡ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት የሚያስፈልገው የውጭ ምንዛሪ ሊገኝ ባለመቻሉ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ መጀመር አልተቻለም። የውጭ ምንዛሪ እጥረቱ ተቋሙ በዕቅድ የያዛቸውን ሥራዎች በመርሃ ግብሩ መሠረት እንዳያከናውን እንቅፋት ሆኖበት እንደቆየ ያስታወሱት አቶ አክሊሉ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቶችን ግንባታ ማስጀመር የሚያስችል የውጭ ምንዛሪ መገኘቱን አስታውቀዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የደብረ ማርቆስ - ቡሬ፣ ገንዳ አርባ እና ወይናታ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክቶችን ለመጀመር ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የውጭ ምንዛሪ ችግሩን ለመፍታት ተቋሙ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ነው ያስረዱት። ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ የሚጠይቁ በመሆናቸው የግንባታ ስራውን ለማስጀመር ያልተቻለ ሲሆን አሁን በተገኘው የውጭ ምንዛሪ ሦስቱ ፕሮጀክቶች በተያዘው የበጀት ዓመት እንደሚጀመሩ አቶ አክሊሉ አረጋግጠዋል፡፡ ለፕሮጀክቶች የሚያስፈልገው የውጭ ምንዛሪ ችግር ሙሉ በሙሉ እስኪፈታ ተቋሙ ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹን የግንባታ ሥራ ለመጀመር ሲታቀድ ለአራቱም ፕሮጀክቶች 4 ነጥብ 83 ቢሊዮን ብር የግንባታ ወጪ ተመድቦላቸው እንደነበር አቶ አክሊሉ አስታውሰዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ጉዳይ ከብሔራዊ ደህንነት ተለይቶ የማይታይ ነው - አቶ ሀብታሙ ውቤ …….//…… በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈጸመው ስርቆት በየዓመቱ ከሃያ በመቶ በላይ እየጨመረ መምጣቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለጹት የሚፈጸመው ስርቆት በዚሁ ከቀጠለ ብሔራዊ የኃይል ቋቱን በማዳከም ከጥቅም ውጭ ሊያደርገው ይችላል፡፡ ከአሁን ቀደም ከፍተኛ ሥርቆት ይፈጸም የነበረው በ132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ የነበረ ሲሆን በአሁን ወቅት ግን ስርቆቱ ወደ 230 እና 400 ኪሎ ቮልት መስመሮችማደጉን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት በስርቆት ምክንያት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት በድምሩ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት አቶ ሀብታሙ አስታውሰዋል፡፡ በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የስርቆት ድርጊቶች በዚሁ የሚቀጥሉ ከሆነ ተቋሙ ከሚደርስበት የንብረት ኪሳራ እና የኃይል ብክነቱ በላይ ብሔራዊ የኃይል ቋቱ የሚፈለገውን አገልግሎት እንዳይሰጥ ሊያደርገው እንደሚችል ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ሀብታሙ ገለጻ የብሔራዊ የኃይል ቋቱ መሰረተ ልማት ጉዳይ ከብሔራዊ ደህንነት ተለይቶ የማይታይ በመሆኑ ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል ሁሉም ሊረባረብ ይገባል፡፡ የሀገሪቱ የኃይል ፍጆታ በየዓመቱ ከአስራ አምስት በመቶ በላይ እያደገ መምጣቱን ያነሱት ሥራ አስፈጻሚው ይሄን ፍላጎት ለማሟላትና በአፍሪካ ተመራጭ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን በሚያደርገው ጥረት ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀኑን አስታውቀዋል፡፡ በ2016 በጀት ዓመት ብቻ 75 የሚደርሱ ታወሮች መውደቃቸውን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ የማስተላለፊያ መስመሮቹ የሚያልፉበት መልከዓምድር አስቸጋሪ በመሆኑ በተቋሙ አቅም ብቻ ደህንነታቸውን ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልፀዋል፡፡ የሕግ አፈጻጸሙ ወጥ አለመሆን፣ የመስተዳድር አካላትና ሕብረተሰቡ በእኔነት ስሜት ችግሩን ለመቅረፍ ዝግጁ ያለመሆን እና የግንዛቤ እጥረት የሚፈጸመውን የስርቆት ድርጊት እንዳባባሰው ተናግረዋል፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ተቋሙ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትን ጨምሮ ከሌሎች የጸጥታና የመስተዳድር አካላት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆትን በመከላከል በኩል ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ ከ40 ሺ በላይ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች፣ ከ20 ሺ ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመሮች እንዲሁም ማከፋፍያ ጣቢያን ከማከፋፍያ ጣቢያና ማከፋፍያ ጣቢያን ከኃይል ማመንጫ ለማገናኜት የሚያስችሉ 307 የማስተላለፊያ መስመሮች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

#EEP #EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል። ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 ሰዓት በኋላ ይቀርባል። በቅርብ ቀን ይጠብቁን! https://www.youtube.com/watch?v=FzCdm5sI5KU የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም

#EEP #EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል። ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 ሰዓት በኋላ ይቀርባል። በቅርብ ቀን ይጠብቁን! https://www.youtube.com/watch?v=FzCdm5sI5KU የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም

#EEP #EBC ፍኖተ ብርሃን የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተቋማችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በማተኮር በአዲሱ ዓመት፣ በልዩ አቀራረብ ለዕይታ በሚመች ሰዓት ወደ እናንተ ይደርሳል። ዘወትር ሐሙስ ምሽት ከ3:00 ሰዓት በኋላ ይቀርባል። በቅርብ ቀን ይጠብቁን! https://youtu.be/GptaGE-ob5k የዩቲዩብ ቻናላችንንም ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም

በተያዘው በጀት ዓመት ከ25 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ለማመንጨት ታቅዷል ……….///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት ከተለያዩ የኃይል ምንጮች 25 ሺህ 423 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት መታቀዱን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ፡፡ በዘርፉ የዕቅድ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ኃይል ለማመንጨት ከታቀደው ውስጥ 24 ሺህ 245 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከውሃ፣ 1 ሺህ 100 ነጥብ 78 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከነፋስ እንዲሁም 77 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ከደረቅ ቆሻሻ የሚመረት ነው፡፡ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት በስድስት ማመንጫ ጣቢያዎች ጥገና የሚፈልጉ ዩኒቶችን በመጠገን ወደ ኦፕሬሽን ለመመለስ እና የጣቢያዎችን ዝግጁነት 92 በመቶ ለማድረስ ታቅዷል ብለዋል፡፡ በዚህም በአዋሽ 2ኛ፣ ጢስ አባይ 2፣ አመርቲ ነሼ፣ ፊንጫ፣ አዳማ 1ኛ እና አሸጎዳ የኃይል ማመንጫ የቆሙ ዩኒቶች ላይ አስፈላጊውን ጥገና በማከናወን ጣቢያዎች በሙሉ አቅማቸው ኃይል እንዲያመነጩ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገለፃ የኢነርጅ አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ በሁሉም ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ደረጃዉን የጠበቀ የቅድመ መከላከል፤ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡ ለዚህም በበጀት ዓመቱ ለሚከናወኑ ተግባራት ዝርዝር መርሃ ግብር መቀመጡንና ሥራዎቹ በተያዘላቸው መርሃ ግብር መሰረት እንዲፈጸሙም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ሥራ አስኪያጇ እንዳሉት ወደ ግድቦች የሚገባው የውሃ መጠን አስተማማኝ በመሆኑ፣ አዳዲስ የኃይል ማመንጫዎች ሥራ መጀመራቸው፣ የኃይል ፍላጎት እና ፈጣን የቴክኖሎጂ ዕድገት መኖራቸው በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኃይል ለማሳካት እንደ መልካም አጋጣሚ የሚወሰዱ ናቸው፡፡ በአንጻሩ በማመንጫ ጣቢያዎች ላይ የቴክኖሎጂ ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸው የቆዩ መሣሪያዎች መኖራቸው፤ በማመንጫ ጣቢያዎች አካባቢ የሚነሱ የካሳ ጥያቄዎች እንዲሁም በከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት አካላት ላይ ተደጋጋሚ ስርቆቶች መፈፀማቸው ለዕቅዱ አፈፃፀም እንደስጋት መቀመጣቸውን አስረድተዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ለማመንጨት የተያዘው ዕቅድ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ4 ሺህ 449 ጊጋ ዋት ሰዓት ብልጫ ያለው ይኖረዋል። በበጀት ዓመቱ 19 ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል ያመነጫሉ ተብለው ዕቅድ እንደተያዘላቸው ሥራ አስኪያጇ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ከ6 ሺህ በላይ የተቋሙ ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጤና አገልግሎት ቢሮ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ6 ሺህ ለሚልቁ የተቋሙ ሠራተኞች በተመላላሸ ህክምና አገልግሎት መስጠቱን አስታወቀ፡፡ የቢሮው ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተኸልቁ እንደገለፁት የታካሚዎች አኀዝ በበጀት ዓመቱ በድግግሞች የህክምና አገልግሎት ያገኙ የተቋሙ ሠራተኞችን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ የተቋሙ ክሊኒክ ከመደበኛ ህክምና አገልግሎት በተጨማሪ ለ143 ሠራተኞች የሥራ ላይ ድንገተኛ ህክምና አገልግሎት መሰጠቱንም ጠቁመዋል። ክሊኒኩ ከአቅሙ በላይ የሆኑ ህክምናዎች ሲያጋጥሙት የተቋሙ ሠራተኞች የተሻለ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ከ19 የጤና ተቋማት ጋር የውል ስምምነት በመፈፀም እየሰራ መሆኑንም ነው አቶ አድማሱ ያስታወቁት፡፡ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እና የመድኃኒት አቅርቦት በሀገር ደረጃ እጥረቶች ቢኖሩም ተቋሙ መንግስታዊ ከሆነው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጋር የረጅም ጊዜ ውል በመፈራረም እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በስምምነቱ መሠረት ከኤጀንሲው የሚያገኛቸውን የህክምና መሳሪያዎች እና መድኃኒቶች ለዋናው መ/ቤት እና በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለሚገኙ ክሊኒኮች ማቅረቡንም ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለፃ በዋና መስሪያ ቤት ክሊኒክ የሚገኘው አምቡላንስ በተቋቋመው የድንገተኛ ህክምና ሰጪ ቡድን በአዲስ አበባ እና በአቅራቢያው ለሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች ድንገተኛ የህክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ከህክምና አገልግሎት ባሻገር በሸታን ቀድሞ ከመከላከል አንፃር የቢሮው የኤች አይ ቪ ኤድስ እና በሸታ መከላከል እና መቆጣጠር ቡድን በዋና መስሪያ ቤት፤ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እና ሪጅኖች የግንዛቤ ማሰጨበጫ እና ትምህርታዊ ስልጠና መስጠቱንም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9