uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 533 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 332-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 177-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 533 obunachiga ega bo‘ldi.

05 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 18 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.66% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.09% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 297 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 344 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 06 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 533
Obunachilar
-424 soatlar
-77 kunlar
+1830 kunlar
Postlar arxiv
photo content

ሠራተኞች በአፈፃፀማቸው ልክ ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር ተግባራዊ ይደረጋል - የሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ………///…………. በውድድር ጊዜ የትምህርት ዓይነት፣ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ አያያዝ አግባብነት ባለውና ወጥ በሆነ መልኩ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ሊተገበር እንደሚገባ የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ፡፡ ተቋሙ በቀጣይ ዓላማውን ያማከለና ሠራተኞች ባከናወኑት ተግባር ልክ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የውጤት ተኮር ስርዓት ተግባራዊ እንደሚያደርግም ገልፀዋል፡፡ የሠው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ከማስታወቂያ ጀምሮ የፈተና አወጣጥ፣ የፈተና እርማት እና የውጤት ማሳወቂያ ሂደቶች በተያዘላቸው ስታንዳርድ መሠረት በማጠናቀቅ ከቅሬታ ነፃ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ደግሞ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ወጥ የሆነ የማወዳደሪያ መስፈርቶችን ከመተግበር አኳያ ክፍተቶች በመኖራቸው ሊስተካከሉ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ በደረጃ ዕድገት፣ በዝውውርና ቅጥር ላይ የሚቀርቡ የሰራተኛ ቅሬታዎች በዘለቄታው ለመፍታት ይረዳ ዘንድ በሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ የሚወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ሳይሸራረፉ በሁሉም የሥራ ክፍሎች ሊተገበሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደገለፁት ለውድድር የሚወጡ ጥያቄዎችን ሚስጥራዊነት እንዲጠበቅ ለማድረግ ራሱን የቻለ የፈተና ቋት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ የሰው ኃይል ሁለንተናዊ አሰራርን የሚያዘምኑ በርካታ ሃሳቦች በተወያዮች የቀረቡ ሲሆን ከመሰል ተቋማት ልምድ በመውሰድ፣ የሚሻሻሉ መመሪያዎችንና ደንቦች በመለየት የተሻለ አሠራርን ተግባራዊ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች ማከናወን እንደሚገባም አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ እና የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር አመራሮች የተሳተፉበት ውይይት ላይ በተቋሙ የሚከናወኑ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውር እና የቅጥር ተግባራት ወጥ በሆነና የአሰራር ስርዓትን ባገናዘበ መልኩ እንዲከናወኑ ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአሁኑ ጊዜ ከ8 ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች አሉት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 24 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

አይ ኤፍ አር ኤስ ለመተግበር እየተሰራ ያለው ስራ በመጠናቀቅ ላይ ነው …….///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ስርዓትን (International Financial Reporting Standard) ለመተግበር እየሰራ ያለውን ስራ በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን በተቋሙ የንብረት ዋጋ ክለሳና አይ ኤፍ አር ኤስ ትግበራ ፕሮጀክት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ስራ አስኪያጅ አቶ ይርጉ ኃይሉ እንዳስታወቁት ተቋሙ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ስርዓትን ለመተግበር ፌር ፋክስ እና ፒ ደብሊው ሲ (PWC) ከተሰኙ ሁለት ኩባንያዎች ጋር ስምምነት በማድረግ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም የንብረት ቆጠራውን መረጃ የመሰብሰብና ወደ ገንዘብ የተመን የዋጋ ክለሳ ስራዉ ተጠናቋል፡፡ የ24 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ 129 ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ 36 ሺህ 210 የኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎች፣ 9 መቶ 48 ተሸከርካሪዎችንና ማሽነሪዎች፣ 48 ሺህ የቤትና የቢሮ ዕቃዎችን እንዲሁም የ3 ሺህ 232 ህንፃዎች የዋጋ ትመና ስራ መከናወኑንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በቆጠራው የተካተቱ ንብረቶች ወደ ገንዘብ ሲተመኑ የተቋሙ ሀብት 382 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ አቶ ይርጉ አስታውቀዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የቆጠራና የትመና ስራው የተከናወነው እ.ኤ.አ. በ2016 እና ከዚህ በፊት አገልግሎት በመስጠት ላይ በነበሩት ንብረቶች ላይ በተካሄደ የአይ ኤፍ አር ኤስ ስራና የንብረት ክለሳ ስራ በመስራት ሲሆን የዋጋ ትመናው የገናሌ ዳዋ 3፣ የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና በግንባታ ላይ ያሉትን ግዙፍ ፕሮጀክቶች አላጠቃለለም፡፡ ተቋሙ ፌር ፋክስ ከተሰኘ ኩባንያ ጋር ያሉትን ንብረቶች ለመቁጠርና የዋጋ ክለሳ ስራዎችን ለማከናወን የ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ስምምነት ተፈርሞ እንደነበር ያስታወሱት ስራ አስኪያጁ ኩባንያው በውሉ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ስራውን ባለመፈፀሙ ተጨማሪ የጊዜ ማራዘሚያ ተሰጥቶት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ ፌር ፋክስ በአሁኑ ወቅት ከማጠናቀቂያ ስራዎች በስተቀር የተሰጠውን ስራ በውሉ መሰረት ያከናወነ ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት የተደረገለት የውል ማራዘሚያም ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደረገም፡፡ በተያያዘ ዜና ተቋሙ ከንብረት ቆጠራውና ዋጋ ክለሳ ስራው በተጓዳኝ ፒ ደብሊው ሲ ከተሰኘ ኩባንያ ጋር ስምምነት በማድረግ የIFRS የፋይናንሺያል ሪፖርት ስራዎች እያከናወነ ይገኛል፡፡ እስከ አሁንም እ.ኤ.አ. ከ2016 እስከ 2019 ያለውን የፋይናንስ ሪፖርት ማዘጋጀት መቻሉንና ከዚህ ውስጥም እ.ኤ.አ. ከ2016 እስከ 2018 ያለው የተቋሙ የመጀመሪያ የIFRS የፋይናንስ ሪፖርት ለሂሳብና ኦዲት ቦርድ ኮርፖሬሽን በማቅረብ የምርመራ ስራው እየተከናወነ እንደሆነ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የኦዲት አገልግሎት ቦርድ የምርመራ ስራዉን ካጠናቀቀ በኋላ ተቋሙ ወደ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ስርዓት ትገበራ ይገባል፡፡ ከፒ ደብሊው ሲ ኩባንያ ጋር በ20 ወራት ውስጥ ስራዎችን አጠናቆ ለማስረከብ ስምምነት ተደርጎ የነበረ ቢሆንም ለተጨማሪ 5 ወራት ውል ተራዝሞለት ስራውን እያከናወነ መሆኑን አቶ ይርጉ አስረድተዋል፡፡ ከኩባንያው ካር የተደረገው ስምምነት የ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 23 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+1

የአሉቶ ጂኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮው በይፋ ተጀመረ ……..//………… የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታ የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮ በይፋ ተጀመረ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ጂኦተርማል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ መሳይ ፈቃዱ የቁፋሮ ሥራውን ለማከናወን የሚያስችሉ ቅድመ ሥራዎች በመጠናቀቃቸው እና የሁሉም እቃዎች አቅርቦት፣ የማሽን ተከላ እና ፍተሻ ሥራ በመጠናቀቁ ቁፋሮው ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡ ቁፋሮውን በሚያዝያ ወር አጋማሽ ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በውሃ አቅርቦት ማነስና በሌሎች ቀሪ ሥራዎች ምክንያት መዘግየቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ አሁን ግን ችግሮቹን ሙሉ በሙሉ በመቅረፍና ቀሪ ሥራዎችን በማጠናቀቅ ቁፋሮው በይፋ መጀመሩን አብስረዋል፡፡ እንደ አቶ መሳይ ገለፃ የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮው ወደ ከርሰ ምድር እስከ 2 ሺህ 700 ሜትር ጥልቀት የሚኖረው ሲሆን የመጀመሪያው 29 ሜትር ቁፋሮ ዛሬ በስኬት ተጠናቋል፡፡ ቁፋሮውን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማከናወን ከሚሰራው ሥራ ጎን ለጎን የሰራተኞች መኖሪያ ካምፕ፣ የውሃ አቅርቦት (የውሃ መስመር፣ የፓምፕ ጣቢያና የውሃ ማጠራቀሚያ)፣የክሊኒክ እና የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የመገንባትና አንዳንዶቹንም የማጠናቀቅ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አቶ መሳይ ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱን የቻይና ፔትሮሊየም ቴክኖሎጂ እና ልማት ኮርፖሬሽን (CPTDC) የውሃ አቅርቦት ሥራውን፣ የኬንያ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ኩባንያ (KenGen)፣ ኬሩ ኦይል ፊልድ እና ኬሩ መሳሪያዎች( keru oil field & keru equipment) የተባሉ የቻይና ኩባንያዎች የእንፋሎት ፍለጋ የጉድጓድ ቁፋሮውን በጥምረት ሲያከናውኑ የሲቪል ሥራውን ክሮስላንድ የተባለ የሀገር ውስጥ ተቋራጭ እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡ ፕሮጀክቱን በፋይናንስ የሚደግፈው በዓለም ባንክ ሲሆን ለግንባታውም 218 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ተመድቦለታል፡፡ የአሉቶ ላንጋኖ የከርሰ ምድር እንፋሎት የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከ7 ነጥብ 5 ወደ 70 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ታስቦ እየተሰራ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 21 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+3

photo content

የሰው ኃይል ቅጥርና ልማት ቢሮ (0115580623) ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፤ መልካም ዕድል!! https://jobs.amazonethiopia.com/job/ethiopian-electric-power-vacancy/

ታላቁ የኢትዮጵያ ግድብና የዩኒቨርስቲዎች ሚና ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ …….////……….. በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጪው ነሐሴ ወር መጨረሻ በሁለት ተርባይኖች ኃይል ለማመንጨት አስፈላጊ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ፡፡ ‘‘የዩኒቨርሲቲዎች ትብብርና የሳይንስ ዲፕሎማሲ ለዓባይ ዘለቄታዊ ልማትና የጋራ ተጠቃሚነት’’ በሚል ርዕሰ በጅማ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ ኢንጂነር ክፍሌ እንደገለፁት ሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት ለማከናውን አስፈላጊ ሥራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ የግድቡ አጠቃላይ አፈፃፀምም 80 በመቶ መድረሱን ይፋ አድርገዋል፡፡ በዩኒቨርስቲው አዳራሽ ግንቦት 9 ቀን 2013 ዓ.ም የተካሄደውን ውይይት የከፈቱት የጅማ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ በበኩላቸው እንደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አመለካከት ለመፍጠር፣ እውነታውን ለህብረተሰቡ ለማስዳት እና ግንዛቤ ለማሳደግ ከዩኒቨርስቲ ምሁራን ብዙ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡ የዓባይ ወንዝ ለተፋሰሱ ሀገራት የጋራ ሀብት በመሆኑ የጥርጣሬና ፉክክር መንስሄ ሊሆን አይገባም ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የጋራ ተጠቃሚነት መርህን እተከተለች ቢሆንም ግብፅ የምታራምደውን እኔ ብቻ ልጠቀም የሚል ሃሳብ ለመመከት ምሁራን እና የዘርፉ ተመራማሪዎች ለህብረተሰቡ እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ማስረዳት እንዳለባቸውም ነው የጠቆሙት፡፡ ሳይንስ ድንበር የለውም ያሉት ዶ/ር ጀማል ምሁራን በዓባይ ወንዝ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ላያ ያተኮሩ ጥናቶችን አጠናክሮ በመቀጠል በተለይና ግብፅና ሱዳን ያሉ ባለሙያዎችን በመጋበዝ መምከር፣ በጋራ መስራት እና የጋራ አቋም መያዝ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ የባለሙያዎች ቡድን አባል ፕ/ር ይልማ ስለሺ፤ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ ‘‘ግብፅ እና ሱዳን ውሃ የለንም’’ የሚል የተሳሳተ ሃሳብ ለዓለም እያቀረቡ ቢሆንም ግብፅ 154 ትሪሊየን የከርሰ ምድር ውሃ እንዳላት ኢትዮጵያውያን ምሁራን ይህንን ለአለም ዓቀፍ ማህበረሰብ ማሳወቅ አለባቸው አስታውሰዋል ። በምክክር መድረኩ ላይ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ተወካዮች፣ ምሁራን እና የዘርፉ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ‘የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያለው ጠቀሜታ እና የምሁራን ሚና’’ በሚል ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

የባህር ዳር-ወልድያ -ኮምቦልቻ ከፍተኛ የኃይል መስመር ፕሮጀክት ግንባታ እየተከናወነ ነው ………..////…………. የባህር ዳር-ወልድያ -ኮምቦልቻ ከፍተኛ የኃይል መስመር ፕሮጀክት ከሚኖሩት የባለ 400 ኪ.ቮ 831 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ውስጥ የ790 ምሰሶዎች የመሰረት ግንባታ ሲጠናቀቅ 500 ምሰሶዎችን የመትከል ስራ መከናወኑን የፕሮጀክት ሳይት ተቆጣጣሪ መሐንዲስ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ተሾመ ገለፁ፡፡ መሐንዲሱ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ 28 ኪ.ሜ የሚሸፍን ተጨማሪ የባለ 230 ኪ.ቮ ተሸካሚ 64 ታወሮች የመትከልና ሽቦ የመዘርጋት ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ ፕሮጀክቱ ከነባሩ ባህር ዳር ቁጥር 2 ማከፋፈያ ተነስቶ 381 ኪ.ሜ በመሸፈን አዲስ ወደሚገነቡት የወልዲያ እና የኮምቦልቻ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚደርስ ነው፡፡ እንደ ሳይት መሐንዲሱ ገለፃ የመስመር ዝርጋታውን ለማከናወን ከሚያስፈልጉት የኤሌክትሮ መካኒካል ዕቃዎች ውስጥ ከ85 በመቶ በላይ ሳይት የደረሱ ሲሆን ቀሪዎቹም ወደብ ደርሰዋል፡፡ የግንባታውም አማካይ አፈጻጸምም ከ60 በመቶ በላይ መድረሱን አስተባባሪ መሐንዲሱ ተናግረዋል፡፡ የመስመር ዝርጋታ ግንባታ ስራውን ታታ ፕሮጀክት ሊሚትድ የተባለ የህንድ ኩባኒያ የሚያከናውን ሲሆን አማካሪው ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነው፡፡ በ2010 ዓ.ም. የተጀመረውን ይህን ፕሮጀክት በ18 ወራት ለማጠናቀቅ ታቀዶ የነበረ ቢሆንም የኮረና ቫይረስ ወረርሽን ተጽእኖ ፣130 ታወሮች የተለያዩ ክፍሎች ላይ የስርቆት ወንጀል መፈጸሙ እና ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች እየተፈጠረ ያለው ጉዳት ፕሮጀክቱን ለተጨማሪ ጊዜና የገንዘብ ወጪ ዳርጎታል፡፡ የመስመር ዝርጋታውን ስራ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ወጪው ሙለ ለሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ተበጅቶለታል፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የክልሉን ፍትሃዊ የኃል አቅርቦት ጥያቄ በመመለስ በኩል ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይታመናል፡፡ | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 12 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content
+3

በዋቸሞ ዩኒሸርሲቲ በፓወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት መስክ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሰራተኞች ተመረቁ .............////............ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተከታታይ ትምህርት መርሀ ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒዉተር ኢንጂነሪንግ( ፓወር ስትሪም) ያሰለጠናቸውን 35 ወንድ እና 3 ሴት 3 ተማሪዎችን አስመረቀ። በኦሮምያ ክልል ሶኮሩ ወረዳ በሚገኘዉ የግልገል ጊቤ 1 ኃይል ጣቢያ በተካሄደው የምርቃት ስነ ስርዓት ላይ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እንዲሁም የዕለቱ የምረቃ ስነ -ስርዓት የክብር እንግዳ ክቡር ዶክተር ሐብታሙ አበበን ጨምሮ ፤የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ የሰዉ ሀብት ትምህርትና ጥናት ሃላፊ አቶ ወንደሰን አበበ፤ የዩኒቨርሲቲዉ የማኔጅመንትና የሴኔት አባላት ፣ የምህንድስናና ቴክኖሎጂ መምህራንና የትምህርት ክፍሉ ሃላፊዎች ተገኝተዋል። በምረቃ ስነ -ስርዓቱ የግልገል ግቤ ቁ1፣ቁ2 እና ቁ3 የሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የስራ ሃላፊዎች የታደሙ ሲሆን ፤ በስነ-ስርዓቱ በመገኘት የእንኳን በደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ የሰዉ ሀብት ትምህርትና ጥናት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ወንደሰን አበበ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ርቀት ሳይገድበዉ የተቋሙ ሰራተኞች ያላቸዉን ሀገራዊ ፋይዳ ፣ የስራ ጫናና የትምህርት እድገት ፍላጎታቸዉን በመረዳት ትምህርትን ተደራሽነቱን በማድረጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም አመስግነዋል። የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶክተር ሐብታሙ አበበ በምረቃ ስነ-ስሮዓቱ ላይ ለተመራቂዎች ባደረጉት ንግግር በዚህ አስቸጋሪ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ከ5 ዓመት በፊት የጀመሩትን ትምህርታቸዉን በማጠናቀቅ ለምረቃ በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸዉን ብለዋል። ግንቦት 10 ቀን 2013 ዓ/ም

እንኳን ለ 1442ኛው የኢድ አልፈጥር (ረመዳን) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! #ዒድ_ሙባረክ

photo content