uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 538 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 326-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 538 obunachiga ega bo‘ldi.

04 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 26 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.64% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.41% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 139 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 395 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 05 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 538
Obunachilar
-724 soatlar
-77 kunlar
+2630 kunlar
Postlar arxiv
ከሠራተኛው ጎን መቆም ግዴታችን ነው - አቶ አሸብር ባልቻ …………////………… ችግሮችን ለመፍታት ከሰራተኛው ጎን መቆም መልካም ፈቃድ ብቻ ሳይሆን ግዴታችንም ጭምር ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተናገሩ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው በተጠናቀቀው የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር 7ኛ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ጉባኤ ላይ እንደገለፁት ተቋሙ በ2013 በጀት ዓመት ከሠራተኛ ማህበር ጋር በመሆን የሠራተኛውን ችግሮች በመፍታት እና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ላሉ ሠራተኞች ለመድረስ በሚቻለው አቅም ተንቀሳቅሷል፡፡ ይህንንም በቀጣይ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተካሄደው የህግ ማስከበር ሥራ በሰሜን ሪጅን ለሚገኙ ሠራተኞች ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ እንዲሰጥ መደረጉ እና በአዋሽ 2 እና 3 ኃይል ማመንጫ በድንገተኛ የእሳት አደጋ ቤት ንብረት ለወደመባቸው 19 የኃይል ማማንጫው ሠራተኞች ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ንብረታቸው እንዲተካለቸው መደረጉን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቅሰዋል፡፡ ማንኛውም የተቋሙ ሠራተኛ በሞት በሚለይበት ወቅት የሁለት ወር ደመወዝ ተሰልቶ ለሟች ቤተሰብ ወይም ለህጋዊ ወራሽ ለቀብር ማስፈጸሚያ እንዲሰጥ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቶ ከሚያዚያ 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ እንዲሚገኝ አቶ አሸብር ጠቁመዋል፡፡ የተቋሙን ሠራተኞች ውጤታማ ለማድረግ ማኔጅመቱም ሆነ ቦርዱ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ ይገኛሉ ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የሠራተኞችን ችግሮችን ለመፍታት ከሰራተኛው ጎን መቆም መልካም ፈቃድ ብቻ ሳይሆን ግዴታችንም ጭምር ነው ብለዋል ፡፡ ከአዋሽ ኃይል ማመንጫ የተገኙት የዘርፍ ማህበር ተወካይ አቶ ምናለ ወልዴ ለተቋሙ አመራሮች ቦታው ድረስ በመላለስ ተጎጂዎችን እና እንዲጽናኑ እና ደግፍ እንዲያገኙ በማድረግ ለሠራተኛው አለኝታነታቸውን በተግባር በማረጋገጣቸው በሠራተኛው ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 24 ቀን 2013

የማከፋፈያ ጣቢያውን ለዕይታ ማራኪና ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል …………////………… የጅግጅጋ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ምድረግቢ የማስዋብና ቢሮዎችን ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥ
+5
የማከፋፈያ ጣቢያውን ለዕይታ ማራኪና ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል …………////………… የጅግጅጋ ባለ132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ምድረግቢ የማስዋብና ቢሮዎችን ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የጅግጅጋ ንዑስ ሪጅን ኃላፊ አብዱላሂ አብሽር እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ቀድሞ የነበረውን ዕይታ የመለወጥ ሥራ ተሰርቷል፡፡ ሥራውን የጣቢያው ሠራተኞች ሙሉ በሙሉ በጉልበታቸው ማከናወናቸውን የጠቀሱት ኃላፊው ሥራው በውጭ ቢሰራ ኖኖ እስከ 5 መቶ ሺህ ብር ያስወጣ ነበር ብለዋል፡፡ ላለፉት አራት ወራት የተከናወነው ምድረግቢውን የማፅዳት፣ ቢሮዎችን ለስራ ምቹ የማድረግና አረንጓዴ የማልበስ ሥራ ላይ የተሳተፉ የጣቢያውና የሪጅኑ ሰራተኞችን ኃላፊው አመስግነዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 24 ቀን 2013

የችግኝ ማፍላትና ተከላ በኃይል ማመንጫዎችና በፕሮጀክቶች በመካሄድ ላይ ነው …………////………… የአሉቶ ጆኦተርማል የማስፋፊያ ፕሮጀክት ችግኝ በማፍላትና በመትከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ላይ በንቃት እየተሳተፈ መሆኑን የፕሮጀክቱ የአካባቢና ማህበረሰብ ተፅዕኖ ክትትል ክፍል አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያ አየለ ባንጃው እንደገለፁት በፕሮጀክቱ የመድሃኒትነት ይዘት ያላቸው እንደ ሞሪንጋና ትሩኒም፣ ለደን ልማት የሚያገለግሉ እንደ ጀካራንዳ፣ ሸውሸዌና ግራር ያሉ፣እንዲሁም ለምግብነትና ለአፈር ጥበቃ የሚውሉ ችግኞች እየፈሉ ነው፡፡ እስካሁንም በፕሮጀክቱ በ2012 ዓ.ም 60 ሺህ፣ በ2013 ደግሞ 55 ሺህ ችግኞች መፍላታቸውን ባለሙያው ገልፀዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ከለሙት ችግኞች መካከል ለሞጆ - ዝዋይ የፍጥነት መንገድ ከ20 ሺህ በላይ፣ ለዝዋይ ፌደራል ማረሚያ ቤት ከ15 ሺህ በላይ፣ ለአካባቢው ነዋሪዎች ከ10 ሺህ በላይ የተሰራጩ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በፕሮጀክቱ እየተተከሉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንደባለሙያው ማብራሪያ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ ሙቀትና የሚሸረሸር አፈር ያለበት አካባቢ በመሆኑ ድርቅን ተቋቁመው አፈርን ለመጠበቅ የሚያስችሉ የዕጽዋት ዓይነቶች ትኩረት ተሰጥቷቸው ተተክለዋል፡፡ የተተከሉት ችግኞች እንዲፀድቁ ክትትል እየተደረገ ሲሆን በ2012 ከተተከሉት ውስጥ የፀደቁት ከ60 በመቶ በላይ መሆናቸውን ባለሙያው ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የጢስ አባይ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በጨረጨራ ግድብ አጠገብ ከ650 በላይ ሀገር በቀል ችግኞችን ተከላ አከናውኗል፡፡ ጣቢያው ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር ያገኛቸውን ችግኞች ዓባይ ከጣና ተለይቶ በሚወጣበት የጨረጨራ ግድብ አቅራቢያ ተክሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 24 ቀን 2013

photo content
+3

photo content
+9

ምክር ቤቱ ሲያካሄድ የነበረውን ጉባኤ አጠናቀቀ …………////…………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከነሐሴ 18 እስከ 20 ቀን 2013 ዓ.ም ሲያካሂድ የነበረውን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ በትናንትናው ዕለት አጠናቋል፡፡ በገባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ ለምክር ቤቱ አባላት መልዕክት ያስተላለፉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አሸብር ባልቻ በ2013 በጀት ዓመት እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ተቋምም የተለያዩ ችግሮችን ብናሳልፍም ስኬት ያገኘንበት በጀት ዓመት ነው ብለዋል፡፡ የህዳሴ ግደብ ሁለተኛ ዙር ሙሌት እንዲሁም ለኦፕሬሽን ስራዎች የሚያስፈልጉትን ግብዓቶች በማቅረብ የተሻለ የኃይል ምርት እንዲኖር መደረጉና የተቋሙ ገቢ የመሰብሰብ አቅሙ እያደገ መምጣቱ ከተገኙት ስኬቶች መካከል ተጠቃሾች ናቸው ፡፡ ተቋሙ እንደ ሌሎች አቻ ተቋማት ከዕዳ ነጻ የሆነ ተቋም እንዲሆን ለማድረግ በወሳኝነት ወጪ ቆጣቢ የሆነ አሰራር እየተተገበረና የአፈጻጸም ምዘና ስርአት መዘርጋቱንም ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ ሰራተኛ በ2014 በጀት ዓመት ለአፈጻጸም ምዘና ትግበራ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የተቋሙን ዕቅድ ለማሳካት በ2013 በጀት ዓመት የታዩ ደካማ አፈጻጸሞችን በማረም ጠንክሮ መስራት እንደሚገባ አቶ አሸብር አሳስበዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በግንባታ፣ በኦፕሬሽን፣ በንብረት እና አስተዳደርና በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ አሉ ያሏቸውን አስተያየቶችና ጥያቄዎች አንስተው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ሥራ አስፈፃሚዎቹ የተነሱ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን እንደ ግብዓት በመውሰድ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል፡፡ በ7ኛው የምክር ቤት አባላት መደበኛ ጉባኤ ላይ የተቋሙ የፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ፣ የስነ ምግባር እና የጸረ ሙስና መከታተያ ክፍል ስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የሴቶች እና ህጻናት ቢሮ ዳይሬክተር የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 21 ቀን 2013

photo content
+9

photo content

photo content
+5

ማህበሩ ሀገርን ለማዳን ለሚደረገው የህልውና ዘመቻ ድጋፍ አደረገ ………..///……… ሁለተኛ ቀኑን የያዘው 7ኛው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበር የምክር ቤት አባላት ጉባኤ ሀገርን ለማዳን ለሚደረገው የህልውና ዘመቻ የ2 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ እንዲደረግ ወሰነ፡፡ የምክር ቤቱ አባላት የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ እየተካሄደ ላለው የህልውና ዘመቻ አጋርነታቸውን ለማሳየት ከማህበሩ ሂሳብ ወጪ የሚሆን የ2 መቶ ሺህ ብር ድጋፍ እንዲደረግ ወስነዋል፡፡ ማህበሩ የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት ሲከፈል እንደአዲስ የተቋቋመና የአቅም ውስንነት ያለው ቢሆንም ከሀገር የሚበልጥ የለም በሚል ድጋፉን ለመስጠት መወሰኑ በጉባዔው ላይ ተገልጿል፡፡ በቀጣይም በሚቻለው ሁሉ አባላቱን በማስተባበር በተለያዩ መልኮች ድጋፉን አጠናክሮ ለመቀጠል የጋራ መግባባት ተደርሷል፡፡ ማህበሩ በትላንት ውሎው የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበሩ ሊቀ መንበር አቶ መኮንን ክፍሌ ያቀረቡትን የ2013 በጀት ዓመት ክንውን ሪፖርት፣ የማህበሩን የኦዲት ሪፖርት፣ የሂሳብ ሪፖርት እና የማህበሩ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት ላይ ውይይት አድርጎ አጽድቆታል፡፡ በዛሬው ዕለትም ከፌደራል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ስለተሻሻለው የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ እና ስለሰራተኛ መብቶች እና ግዴታዎች ለምክር ቤቱ አባላት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በነገው ዕለት ከተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ ጉባኤው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 19 ቀን 2013

photo content

ተቋሙ የ25 ዓመት መሪ ዕቅድ እያዘጋጀ ነው …………///………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ25 ዓመት መሪ ዕቅድ እያዘጋጀ መሆኑን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንዳስታወቁት ሀገሪቱ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለመገንባት እያደረገችው ላለው ጥረት የኤሌክትሪክ ኃይል ቀድሞ መገኘት ስላለበት የኤሌክትሪክ ዘርፍ የ25 ዓመት መሪ ዕቅድ ማዘጋጀት አስፈልጓል፡፡ በዚህም ዕቅዱ የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ዕድገት ያለውን ድርሻ በሚያሳይ መልኩ መሪ ዕቅዱ እየተዘጋጀ ይገኛል ብለዋል፡፡ መሪ እቅዱ ከአሜሪካ መንግስት በተገኘ የ5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እርዳታ ደብሊው ኤስ ፒ (WSP) ከተሰኘ የእንግሊዝ አማካሪ ኩባንያ ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ አንዱአለም ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ በማጥናት ወደ ፊት ምን አይነት ፍጆታ ይኖራል? የኤሌክትሪክ ኃይል በምን አይነት መልኩ ተደራሽ መሆን አለበት? የሚገነቡ ፕሮጀክቶች ምን ዓይነት አካባቢዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ይኖራቸዋል? እንዲሁም ምን ያህል ወጪ ያስፈልጋቸዋል የሚለውን ስራ እንደሚያከናውን ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ እስካሁን ባለው ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ዘርፍ ዕቅድ መጠናቀቁን የጠቆሙት ሥራ አስፈጻሚው በ2014 ዓ.ም መጀመሪያ የ25 ዓመቱን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሚዘጋጀው መሪ ዕቅድ ከ10 ዓመቱ የዘርፉ ዕቅድ ጋር በተናበበ መልኩ እንዲሄድ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑንም አቶ አንዱአለም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በፊት የነበረው የኃይል ማመንጨት ሥራ በውሃ ላይ ጥገኛ የነበረ መሆኑን ያነሱት አቶ አንዱአለም በተለያየ ጊዜ ድርቅ ሲከሰት የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ይስተዋል ነበር ብለዋል፡፡ የ25 ዓመቱ መሪ ዕቅድ የኤሌክትሪክ ማመንጨት ሥራው ከውሃ ጥገኝነት ተላቆ በሌሎች የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጮች ላይ ትኩረት በማድረግ ከዚህ በፊት ሰያጋጥሙ ለነበሩ ችግሮች መፍትሔ ይዞ ይመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 19 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content
+4

ማህበሩ የምክር ቤት አባላት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ …………./////……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር የምክር ቤት አባላት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ራስ ሆቴል ማካሄድ ጀምሯል፡፡ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ከ70 በላይ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ያቀፈው የሀገር አቀፍ ኃይል ማመንጫ፣ ኬሚካልና ማዕድን ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ መንገሻ ደሴን ጨምሮ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ መኮንን ክፍሌ እና የማህበሩ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል፡፡ በጉባኤው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ መንገሻ ደሴ እንደተናገሩት ፌደሬሸኑ ከአባል ማህበራት በሚቀርብለት የመብት ማስከበር ጥያቄ መሰረት ደረጃውን ጠብቆ፣ የህግ ሥርዓቱን በመከተል የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የማስከበር ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ሥራ አስፈጻሚ የተቋሙ የስራ አመራር ቦርድ አባል በመሆን በተቋሙ ሠላማዊ የሆነ የኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈን አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ማህበሩ የሠራተኛውን ጥቅም እና መብት ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ ለሚያጋጥመው ተግዳሮት ፌደሬሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል፡፡ ለ3 ቀናት የሚቆየው የማህበሩ ስብሰባ በኮቪድ -19 በሽታ ህይወታቸውን ላጡ የተቋሙ ሠራተኞች የህሊና ጸሎት በማድረግ እና በተለያዩ ምክንያቶች በተጓደሉ የማህበሩ አባላት ምትክ የተመረጡትን ለአባላቱ የማስተዋወቅ ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡ ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበሩ በ2013 በጀት ዓመት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት ሪፖርት፣ የማህበሩ የኦዲት ሪፖርት እና የማህበሩ የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድና በጀት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2013

በ Itsmydam.et የሞባይል መተግበሪያ ከ115 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ተሰበሰበ ………..//////…………. ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የሚያስችል Itsmydam
+1
Itsmydam.et የሞባይል መተግበሪያ ከ115 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ተሰበሰበ ………..//////…………. ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የሚያስችል Itsmydam.et የተሰኘው የሞባይል መተግበሪያ ይፋ በተደረገ በአጭር ጊዜ ውስጥ 1058 ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተሳትፈውበት 115,599 የአሜሪካን ዶላር ተሰብስቧል፡፡ የitismydam የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማጠናቀቅ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የበለጸገ መተግበሪያ ሲሆን ገንዘቡ ሙሉ በሙሉ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ብቻ የሚውል ነው። መተግበሪው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ቪዛ፣ ማስተር ካርድ እና አሜክስን በመጠቀም ከየትኛውም የዓለም ክፍል በአንድ ጊዜ እስከ 10,000 ዶላር ድጋፍ እንዲያደርጉ ያስችላል፡፡ itismydam የሞባይል እና ድህረ ገጽ መተግበሪያ ሙሉ በሙሉ የበለጸገው በኤግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ኃ.የተ.የግ.ማ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተ አካውንት ተሰባስቦ በቀጥታ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሥራ እንዲውል ይደረጋል፡፡ በተመሳሳይም ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ይፋ በተደረገው www.mygerd.com የተሰኘው ድረ ገጽን መሰረት ያደረገ የድጋፍ ማሰባሰቢያ 182,992 የአሜሪካን ዶላር ተሰብስቧል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2013

ተቋሙ ከኃይል ኤክስፖርት ከ138 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዷል ………..///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው የበጀት ዓመት ከውጭ የኃይል ሽያጭ ከ1 መቶ 38 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ማቀዱን በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነሰ ደቨሎፕመንት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚኒሊክ ጌታሁን እንዳስታወቁት በተያዘው የበጀት ዓመት ለሱዳን፣ ለጅቡቲ እና ኬንያ ከ1 ነጥብ 63 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 138 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቀዷል፡፡ ገቢውን ለመሰብሰብ ለሱዳን 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ 55 ነጥብ 48 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጅቡቲ 527 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ 34 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት መታሰቡን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ እስካሁን የኢነርጂ ኤክስፖርት ወዳልተጀመረበት ኬኒያ ወደ 695 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብና 48 ነጥብ 65 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ዕቅድ መያዙንም ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል የኢትዮ- ኬንያ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠናቀቁና የኬንያም ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ታሳቢ ተደርጎ ከጥር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ለማድረግ እቅድ ተይዟል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለኬንያ 695 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 48 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በኬንያ በኩል እየተገነባ ያለው የኢትዮ- ኬንያ የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ባለመጠናቀቁ ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ እንዳልተቻለ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ ከሦስቱ ሀገራት በተጨማሪ በቀጣይ ከሶማሌ ላንድ፣ ከታንዛኒያ እና ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ለመፍጠር የሁለትዮሽ ግንኙነት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

በተቋሙ አምስት ዘርፎች ላይ የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት - ERP ለመተግበር የሚያግዝ ስልጠና ተጀመረ ……../////………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወቅቱ በተመረጡ አምስት ዘርፎች ላይ የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት (Enterprise resource planning) ለመተግበር የሚያስችለውን ስልጠና ዛሬ ጀመረ፡፡ የተቋሙ የሞደርናዜሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደተናገሩት ተቋሙ ከኢትዮጰያ አየር መንገድ እና ሳፕ(SAP) ከተባለ ዓለምአቀፍ ኩባንያ ጋር በመተባበር በሶስት ደረጃዎች የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት ትግበራ ላይ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የተቋሙን ግዙፍ ሃብት የሚያቀሳቅሱት የሰው ኃይል አስተዳደር ፣የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ልማት፣ የፋይናስ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታ እና ኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላፊያ ግንባታ ፕሮጀክቶች፣የንብረት አስተዳደር እና የግዢ የስራ ክፍሎችና ዘርፎች መለየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለዩት ዘርፎችም ያሉባቸውን የአሰራር ክፍተቶችና ችግሮች በመለየት ክፍተቱንና ችግሮቹን የሚሞላ የሶፍትዌር ቴክኖሎጂ በጥናት የማዘጋጅት እንዲሁም የማህደር እና የመረጃ ማሰባሰብ ስራዎች ላለፉት ስምንት ወራቶች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡ የተዘጋጀው ስልጠና ለተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት በተዘጋጁት ሞጁሎች እና ሶፍትዌሮች ላይ የተግባር ልምምድ በመስጠት ዘርፎቹን ወደ ሙሉ ትግበራ በማስገባት ወቅቱ የሚጠይቀውን ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት (Enterprise resource planning) መተግበር ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ፈጣን ፣ትክክለኛና ቀልጣፋ የመረጃ፣የማህደር፣የፕሮጀክት አስተዳደር፣የፋይናስ፣ የግዢ እና የንብረት አያያዝ እና አስተዳደር እንዲኖር በማድረግ በተቋሙ ያለውን የመረጃና የዶክመንት አያያዝ ችግር ይቀርፋል፡፡ ሪጅኖችና ዘርፎችን ከማዕከል ጋር በመረጃ መረብ በማስተሳሰር እና ብክነትን በማስቀረት ገቢን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ እንደሚያስችል አቶ ገነቱ አስገንዝበዋል፡፡ ከየስራ ዘርፎቹ የተወጣጡት ሰልጣኞች የተግባር ስልጠና ልምምዱን በአግባቡ በመረዳት እና በመያዝ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡ የተግባር ልምምዱ ሲጠናቀቅ በ2014 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ ወደ ትግበራ ለመግባት ዕቅድ ተይዟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2013 ዓ.ም

በቀጣይ 10 ዓመታት ለኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች 40 ቢሊየን ዶላር ያስፈልጋል …….///………. በቀጣይ 10 ዓመታት ከተለያዩ የኃይል አማራጮች 71 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱአለም ሲዓ ገለፁ፡፡ ፕሮጀክቶች ለመገንባት 40 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግም ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱአለም ገለፃ ለፕሮጀክቶቹ ያስፈልጋል ተብሎ የታሰበው ገንዘብ በግልና በመንግስት አጋርነት፣ በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በአለም ባንክ፣ በሌሎች የልማት አጋሮችና አበዳሪ ተቋማት፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲሁም በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል ተብሎ ዕቅድ ተይዟል፡፡ በ10 ዓመቱ ውስጥ ይገነባሉ ተብለው በዕቅድ ከተያዙ ፕሮጀክቶች መካከልም 16 የውሃ፣ 24 የነፋስ፣ 17 የእንፋሎት እንዲሁም 14 የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ አቶ አንዱአለም እንዳሉት በዕቅድ የተያዙትን የኃይል ፕሮጀክቶች ግንባታ በመንግስት ብቻ ማሳካት ስለማይቻል በአሁኑ ሰዓት የግልና የመንግስት አጋርነት ስትራቴጂ ተቀርፆ በመሰራት ላይ ይገኛል፡፡ ይገነባሉ ተብለው ከተለዩት ፕሮጀክቶች መካከል የትኞቹ ፕሮጀክቶች ቀድመው መገንባት እንዳለባቸው እና የትኞቹ በአነስተኛ ዋጋ መገንባት እንሚችሉ የመለየት ስራ እንደሚከናወንም አቶ አንዱአለም አብራርተዋል፡፡ ማመንጫ ፕሮጀክቶች በግል አልሚዎች እና በግልና በመንግስት ሽርክና እንዲገነቡ በተያዘው አቅጣጫ መሰረት ሁለት የፀሐይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች አኳ ፓወር በተሰኘ የሳዑዲ አረቢያ ኩባንያ የሚገነቡ ሲሆን ኩባንያው ወደ ግንባታ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የአይሻ 1 የነፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ግንባታ ለማከናወንም አሚያ ከተሰኘ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ኩባንያ ጋር ድርድር መጀመሩን የጠቆሙት አቶ አንዱአለም የሌሎች የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች አልሚን ለመለየት በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱአለም ገለፃ የቱሉሞየና ኮርቤቲ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በግል አልሚዎች አማካኝነት ግንባታቸው ተጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content