uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 538 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 326-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 538 obunachiga ega bo‘ldi.

04 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 26 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.64% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.41% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 139 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 395 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 9 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“EEP Communication”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 05 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 538
Obunachilar
-724 soatlar
-77 kunlar
+2630 kunlar
Postlar arxiv
photo content

photo content

በጢስ አባይ ኃይል ማመንጫ የባክአፕ ሲስተሙን አስመስሎ (Modification) በመስራት ማስተካከል ተችሏል ………..///………… የጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት የሚንቀሳቀስበት ሶፍትዌር በ
+2
በጢስ አባይ ኃይል ማመንጫ የባክአፕ ሲስተሙን አስመስሎ (Modification) በመስራት ማስተካከል ተችሏል ………..///………… የጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት የሚንቀሳቀስበት ሶፍትዌር በመብራት መቋረጥ ምክንያት በራሱ በመጥፋቱና መልሶ እንዲነሳ የሚያደርግ (BackUp) ፕሮግራም ስላልነበረው ለባክአፕ የሚያግዝ ባትሪ አስመስሎ (Modification) በመስራት ሲስተሙን ማስተካከል መቻሉን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ደጀኔ ጉታ ገለፁ፡፡ አቶ ደጀኔ እንደተናገሩት የሞደፊክ ስራ በመሰራቱ የዩኒቱ የኮምፒዩተር ፕሮግራም ያለምንም ችግር መስራት ችሏል፡፡ የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ሹመት በላቸው በበኩላቸው ጢስ አባይ እና ፊንጫ ኃይል ማመንጫዎች ባክ አፕ ማድረጊያ ሲስተም ስላልነበራቸው መብራት ሲቋረጥ ዩኒቶቹ ሲሰሩበት የነበረው ፕሮግራም የመጥፋት ዕድል እንደነበረው አስታውሰዋል፡፡ በዚህ የተነሳ ጢስ አባይ የነበረው ፕሮግራም በመብራት መቋረጥ ሲጠፋ ባካፕ ሲስተም ስላልነበረው ፕሮግራሙን እንደገና መጫን አስፈልጎ ነበር፡፡ ሞደፊክ የተሰራው ባካፕ ማድረጊያ ፕሮግራም በተለያየ ምክንያት ቢጠፋ እንኳ ሲስተሙ የመዘገበው ሳይጠፋ እንዲቆይ የሚያደርግ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ሶፍትዌሩ ተገኝቶ ሲስተሙ በተለያዩ የፋይል ማቆያ አማራጮች ባክአፕ ተደርጓል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ሠራተኞቹ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ደም ለገሱ ………///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደቡብ ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የ2013 ዓ.ም አፈፃፀም በመገምገም እና የ2014 ዓ.ም እቅድ ላይ በመወያየት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት አጋርነታቸውን ለመግለፅ የደም ልገሳ አደረጉ፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የሪጅን ትራንስሚሽን ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዐቢይ መኮንን እንደገለፁት በ2013 ዓ.ም በጀት ዓመት በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸሙት የኃይል ተሸካሚ ታወር ብረቶች ስርቆት ለኦፕሬሽን ሥራ እንቅፋት ሆኗል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የሪጅኑ ሠራተኞች ባገኙት አጋጣሚ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ሊሰሩና እንደተቋም ከክልል፤ ከዞን እና ከከተማ መስተዳድሮች ጋር በቅርበት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡ የሪጅኑ ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን እና ጥገና ስራ አስኪያጅ አቶ ሚሊዮን ቡልቲ በበኩላቸው በስራ ክፍሉ ሰፊ የጥገና እና የኢንስፔክሽን ስራዎች እንደተከናወኑ ገልፀዋል፡፡ የሪጅኑ አመራሮችና ሰራተኞች በ2014 ዓ.ም እቅድ ላይ የተወያዩ ሲሆን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ ለእቅዱ መሳካት የሁልም ሰራተኞች ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸው ሰራተኞች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ለሪጅኑ አገልግሎት የሚሰጥ የሞባይል መተግበሪያ ላበለፀጉት ለአቶ ማሩፍ ሚፍታየሞባይል ሽልማት አበርክቷል፡፡ ሰራተኞቹ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ካደረጉት የገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ከጅማ ደም ባንክ ጋር በመነገር 21 ዩኒት ደም ለግሰዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 32 ዩኒት ደም ለግሰዋል፡፡ የጣቢያው ሠራተኞች የሀገርን ህልውና ለማስጠበቅ እየተዋደቀ ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የአንድ ወር ደመወዛቸውን ድጋፍ ከማድረጋቸው በተጨማሪ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም አዳማ ከተማ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ደም ባንክ ቅርንጫፍ ደም በመለገስ ድጋፋቸውን አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2013 ዓ.ም

በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ድግሪ ለሚማሩ ተማሪዎች በተጋባዥ መምህርነት እና በምርምር ሥራ አማካሪነት አገልግለዋል። ዶ/ር ዮሴፍ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ ም አርፈዋል። ዶ/ር ዮሴፍ በሲቪል ምህንድስና መስክ በተለያየ ሙያና ኃላፊነት ከ25 ዓመታት በላይ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዘርፍ ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ አባል ሆነው በቆዩባቸው ዓመታት ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ ከሌሎች የቦርድ አባላት ጋር በመሆን ጥረት ያደረጉ አመራር ነበሩ፡፡ የቀብር ሥነስርዓታቸው ሐሙስ ነሐሴ 13 ቀን 2013 ዓ• ም• በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በ 9:00 ሰዓት ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ይፈፀማል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞችም በዶ/ር ዮሴፍ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን እየገለጹ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለባልደረቦቻቸውና ለወዳጆቹ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛሉ፡፡

የሀዘን መግለጫ …………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቦርድ አባል የነበሩት ዶ/ር ዮሴፍ ብሩ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተዉ ህይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ዶ/ር
የሀዘን መግለጫ …………////…………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቦርድ አባል የነበሩት ዶ/ር ዮሴፍ ብሩ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተዉ ህይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡ ዶ/ር ዮሴፍ ብሩ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጂማ ከተማ የተከታተሉ ሲሆን የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ፋኩሊቲ በሲቪል ምህንድስና በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1982 ዓ.ም. በላቀ ውጤት አጠናቀቁ። ከምረቃቸውም በኋላ በቀድሞ የአርባ ምንጭ የውሃ ቴክኖሎጂ በመምህርነት ጀምረው እስከ ከፍተኛ አመራርነት አገልግለዋል። የሁለተኛ እና የሦስተኛ ዲግሪያቸውን በህንድ ሀገር የተከታተሉ ሲሆን ረጅሙን የአገልግሎት ዘመናቸውንም የመጀመሪያ ሥራቸውን በጀመሩበት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አበርክተዋል። ዶ/ር ዮሴፍ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በነበራቸው የአገልግሎት ዘመን ከመምህርነት ባሻገር ለዩኒቨርሲቲው መስፋፋት በከፍተኛ አመራርነትና በምህንድስና ሙያቸው ጉልህ ሚና ተጫውተዋል። ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲት አገልግሎት በኋላ በሚከተሉት ዋና ዋና መሥሪያ ቤቶች ለሀገራቸው አገልግለዋል። ★ በኮንስትራክሽንና ከተማ ልማት በዳይሬክተርነት፤ ★ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት መሥራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ ★ በአያት መኖሪያ ቤቶች ድርጅት በዋና ሥራ አስኪያጅነት፤ ★ በጊፍት የመኖሪያ ቤቶች ድርጅት በዋና ሥራ አስኪያጅነት፤ ★ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ኮርፖሬሽን በቦርድ አባልነት፤ ★ በተለያዩ የሀገሪቷ ዩኒቨርሲቲዎች በሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት እና አባልነት፤ ★በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሥራ አመራር ቦርድ አባልነት፤

የተቋሙ 191 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ዕዳ ተሰርዞ ወደ ካፒታል እንዲዞር ተደረገ …………////…….. መንግስት ከፍተኛ ዕዳ ያለባቸው የልማት ድርጅቶች ዕዳ እንዲሰረዝና ወደካፒታል እንዲዞር ባሳለፈው ውሳኔ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወሰደው ብድር ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆነው ዕዳ ተሰርዞ ወደ ካፒታል እንዲዞርለት ተደረገ፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የመንግስት ዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ ባደረጉት የአራትዮሽ ስምምነት ተቋሙ እ.ኤ.አ. ከ2004 እስከ 2016 ከንግድ ባንክ የወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ እንዲሁም በ2017 የወሰደው ብድር በከፊል ወደ ካፒታል እንዲዞርለት ተወስኗል፡፡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተቋሙ የወሰዳቸው ቀሪ ብድሮችን ግን በራሱ የሚከፍል ይሆናል፡፡ የዕዳ ስረዛው ተቋሙን 191 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ከነወለዱ የሚያስቀርለት ሲሆን በተያዘው በጀት ዓመት 17 ነጥብ 25 ቢሊየን ብር እንዲሁም በቀጣይ በጀት ዓመት 18 ነጥብ 81 ቢሊየን ብር ወለድ ከመክፈል ታድጎታል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ይከፈል የነበረው የ17 ነጥብ 25 ቢሊየን ብር ወለድ የተቋሙን የ2013 በጀት ዓመት ገቢ ከ85 በመቶ በላይ ይሸፍናል፡፡ የዕዳ ስረዛው የተቋሙን ዕዳ ወደ ካፒታልነት ስለሚያዞረው የሂሳብ መዝገቡን በማስተካከል ወደ ጤነኛነት የሚመልሰው ይሆናል፡፡ ጠንካራና ተወዳዳሪ ተቋም በማድረግም ወደፊት ለሚያከናውናቸው ሥራዎች አቅም ይፈጥርለታል፡፡ በስምምነቱ መሰረት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሰጠው ብድር ወደካፒታል በመዞሩ አበዳሪው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 191 ነጥብ 8 ቢሊየን ብሩን የሚጠይቀው ከተቋሙ ላይ ሳይሆን አዲስ ከተቋቋመው የመንግስት ዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን ላይ ይሆናል፡፡ ከፍተኛ ዕዳ ካለባቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የስኳር ኮርፖሬሽን፣ የቀድሞ የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ የኬሚካል ኢንደስትሪ፣ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽንና የኢትየጵያ አገልግሎት ዕዳ እንዲሰረዝ የሚያደርግ ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

በፕሮጀክቱ ሁለተኛውን የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ተጀመረ ……….////…………. የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ፍለጋ የሁለተኛ ጉድጓድ ቁፋሮ ዛሬ ተጀመረ፡፡ ለጉድጓድ ቁፋሮው የሚውል የመቆፈሪያ ሪግ ተከላ
በፕሮጀክቱ ሁለተኛውን የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ተጀመረ ……….////…………. የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ፍለጋ የሁለተኛ ጉድጓድ ቁፋሮ ዛሬ ተጀመረ፡፡ ለጉድጓድ ቁፋሮው የሚውል የመቆፈሪያ ሪግ ተከላ፣ የውሃ አቅርቦትና ሌሎች ዝግጅቶች አስቀድመው በመጠናቀቃቸው የሁለተኛው ጉድጓድ የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ዛሬ ተጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም

በፕሮጀክቱ ሁለተኛውን የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ለመጀመር ዝግጅት ተጠናቋል ……….////…………. የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ፍለጋ የሁለተኛ ጉድጓድ ቁፋሮ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሳ
+2
በፕሮጀክቱ ሁለተኛውን የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ ለመጀመር ዝግጅት ተጠናቋል ……….////…………. የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ፍለጋ የሁለተኛ ጉድጓድ ቁፋሮ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሳይት መሐንዲስ ልዑል አስፋወሰን ገለፁ፡፡ መሐንዲሱ እንደገለፁት የመጀመሪያው ጉድጓድ ቁፋሮ 475 ሜትር ደርሷል፡፡ ለሁለተኛው ጉድጓድ ቁፋሮ የሚውል የመቆፈሪያ ሪግ ተከላ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን ለቁፋሮው የሚሆን የውሃ አቅርቦትና ሌሎች ዝግጅቶችም መጠናቀቃቸውን ገልፀዋል፡፡ የቁፋሮ ሥራውን የሚያከናውነው ከተለያዩ ሀገራት የተወጣጣው ቡድንም የእርስ በእርስ ትውውቅ በማድረግ ስለሥራ ላይ ደህንነት ገለፃ ተደርጎለታል፡፡ የፕሮጀክቱ የጤና፣ ማህበራዊና አካባቢያዊ ጉዳዮች ተቆጣጣሪ ዛዛ ግሪጎሪያ በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት የሥራ ደህንነት ጉዳይ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ በመሆኑ ሁሉም ሠራተኛ በሥራ ቦታ ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለመቀነስ በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡ የሥራ ቦታ ደህንነት ራስን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን የስራ ባልደረባንም ከአደጋ የመጠበቅ ግዴታን የሚያካትት በመሆኑ ጥንቃቄ ቀዳሚው የተግባር መመሪያ ሊሆን ይገባል ብልዋል፡፡ የሁለተኛው ጉድጓድ የእንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮው በመጪዎቹ ሦስት ቀናት ለመጀመር ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 10 ቀን 2013 ዓ.ም

የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹን ከእንቦጭና ጎርፍ ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተሰርተዋል …….//……… በተያዘው በጀት ዓመት የአዋሽ II እና III የውኃ ሃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከእንቦጭ እና ጎርፍ
+3
የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹን ከእንቦጭና ጎርፍ ለመከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተሰርተዋል …….//……… በተያዘው በጀት ዓመት የአዋሽ II እና III የውኃ ሃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከእንቦጭ እና ጎርፍ ለመታደግ የቅድመ መከላከል ሥራዎች መሰራታቸው ተገለፀ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው አበበ እንደገለፁት ክረምቱን ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን የጎርፍ አደጋ መከላከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በአዋሽ II ማመንጫ ጣቢያ ወደ ተርባይኑ የሚገባው ውኃ በእንቦጭ አረም እንዳይዘጋ የሚያግዝ መከላከያ መሰራቱን የገለፁት አቶ ጌታቸው በአዋሽ III ማመንጫ ጣቢያም ጎርፍ ወደ ኃይል ማመንጫ ቤት (Power House) በመግባት ጉዳት እንዳያደርስ የሚያስችል ግንባታ መሰራቱን አብራርተዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ክረምት ተከስቶ የነበረው ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ በአዋሽ III የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ ጉዳት ማድረሱ የሚታወስ ነው፡፡ ጣቢያውን ወደ ማመንጨት ሥራው ለመመለስ በተደረገው ርብርብ ወደ ሥራ ከተመለሰ በኋላ በበጀት ዓመቱ 96 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን አቶ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡ በተያያዘ በጣቢያዎች ላይ የአረንጓዴ ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ በተያዘው እቅድ በአዋሽ II እና III የውኃ ሃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 485 ሺህ ብር በሆነ ወጭ ከ2 ሺህ 500 በላይ ሀገር በቀልና የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 07 ቀን 2013 ዓ/ም

በደብረ ታቦር እና በበቆጂ አዳዲስ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ሊገነቡ ነው …………///………. በአማራ ክልል በደብረ ታቦር ከተማ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል በበቆጂ ከተማ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ሊከናወን ነው፡፡ የደብረ ታቦር ባለ 230/33/15 ኪ.ቮ ማከፋፈያ ጣቢያ ከባህር ዳር - አላማጣ ከሚሄደው ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠልፎ የሚገነባ ሲሆን የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ከመልካ ዋከና - ቆቃ ከተዘረጋዉ ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠልፎ የሚገነባ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ በከተሞቹና በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ከተማዎች እና ወረዳዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያግዛሉ፡፡ የደብረ ታቦር ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክትን ለመገንባት 11 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም የበቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክትን ለማከናወን 9 ነጥብ 9 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይፈልጋል፡፡ የፕሮጀክቶች የግንባታ ስራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል (own force) ቢሮ ይከናወናል፡፡ የፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማከናወን የዕቃ አቅራቢ ግዢ ለማከናወን ከአበዳሪው ዓለም ባንክ ፍቃድ ተገኝቶ የጨረታ ሰነድ በመሸጥ ላይ ነው፡፡ በተመሳሳይ ዜና የጉራራ፣ ጎፋ እና መካኒሳ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ እንዲሁም ሁለት የባለ 132 ኪ.ቮ ማስተላለፊያ መስመሮችን አቅም የማሳደግ ስራ ለማከናወን እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ የፕሮጀክቶችን ስራ ለማከናወንም የአዋጭነት ጥናቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ከአበዳሪው የአፍሪካ ልማት ባንክ ይሁንታ ከተገኘና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ከተጠናቀቁ በኋላ የፕሮጀክቶቹ ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 07 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከኤሌክትሪክ ኤክስፖርት ከ90 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ተገኝቷል ……..////……… በተጠናቀቀው የ2013 በጀት ዓመት ለጎረቤት ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ኃይል ከ90 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ድቨሎፕመንት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሱዳን እና ጅቡቲ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 80 ነጥብ 7 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ ኤሌክትሪክ በማቅረብ 90 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መሰብሰቡን መምሪያው አስታውቋል፡፡ ይህም ከእቅዱ የ9 ነጥብ 7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወይም የ12 በመቶ ብልጫ እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ወደ ሀገራቱ በተናጠል ለሱዳን 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በመሸጥ 55 ነጥብ 48 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጅቡቲ ከ5 መቶ 27 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በመሸጥ 35 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከውጭ ሃገራት የኃይል ሽያጭ የሰበሰበው ገቢ በ2012 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከሰበሰበው ጋር ሲነፃፀር የ24 ነጥብ 1 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወይም የ36 ነጥብ 2 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ በ2013 በጀት ዓመት ለኬንያ 695 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 48 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በኬንያ በኩል እየተገነባ ያለው የኢትዮ ኬንያ የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ባለመጠናቀቁ ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ አልተቻለም፡፡ ተቋሙ ከውጭ ሃገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የሚሰበስበው ዓመታዊ ገቢ በየዓመቱ እያደገ የሚገኝ ሲሆን ይህም 2011 በጀት ዓመት ከነበረበት 54 ነጥብ 9 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በ2012 በጀት ዓመት 66 ነጥብ 4 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያደገ ሲሆን በ2013 በጀት ዓመትም 90 ነጥብ 5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መድረስ መቻሉን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በቂ ውሃ መያዛቸው እና የኃይል መቆራረጥ መቀነሱ ለበጀት ዓመቱ እቅድ መሳካት እና በዓመቱ ለተስተዋለው የገቢ አሰባሰብ እድገት በምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 06 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+1

ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መኖር ለአንድ ተቋም ውጤታማነት አስፈላጊ ነው ተባለ ................////................ በአንድ ተቋም ውስጥ ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መኖሩ ለተቋሙ ውጤታማነት አስፈላጊ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋም ትራንስፎርሜሽናል ቢሮ አስታወቀ፡፡ ቢሮው በተቋማዊ ባህል ዙሪያ ባካሄደው ረቂቅ የዳሰሳ ጥናት ላይ ከተቋሙ የስራ ክፍሎች ከተውጣጡ የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ተወያይቷል። የቢሮው ስራ አስኪያጅ አቶ አንዱአለም ኪዳኔ እንደተናገሩት በአንድ ተቋም ውስጥ ጠንካራና ግልጽ የሆነ ተቋማዊ ባህል መኖር ተቋሙ የተጣለበትን ዓላማና ግብ ለማማሳካት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ ዳሰሳ ጥናቱ ተቋሙ አሁን ያለውን ተቋማዊ ባህል ለማወቅ፣ ያለውን ክፍተት ለማሻሻልና ጥንካሬውን ለማጎልበት የሚያስችሉ እርምጃዎችን ለማመላከት እንደሚያግዝም አቶ አንዱአለም ገልፀዋል፡፡ እንደ ስራ አስኪያጁ ገለፃ የዳሰሳ ጥናቱ ተቋማዊ ባህል ለተቋም ውጤታማነት ያለውን አስተዋጽኦ ለማስቀመጥ እና የኮርፖሬት ቢዝነስ ባህል ያለው ተቋም ለመገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ አውደ ጥናቱ የተካሄደው በዳሰሳ ጥናቱ የተገኙ ግኝቶችን ከሁሉም የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ለማስተዋወቅ እና ከተሳታፊዎች ተጨማሪ መረጃዎችን ለማሰባሰብ ታስቦ እንደሆነ አቶ አንዱአለም አስታውቀዋል፡፡ በአውደ ጥናቱ ላይ እንደተገለጸው ሠራተኛው ተቋሙን የራሱ አድርጎ በኃላፊነት ያለመንቀሳቀስ፣ ግብ ተኮር ባህል አለመኖር፣ ግለሰቦችና ቡድኖች ግብን ለማሳካት ግልጽ የሆነ እቅድ አለመኖር፣ ግለሰቦችና ቡድኖች በሰሩት ሥራ የእውቅናና ሽልማት ሥርዓት አለመኖር፣ የተጠያቂነት ሥርዓት ያለመዘርጋት እና የቡድን ስራ የተዳከመ መሆን የሚሉት በረቂቅ ዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ ግኝቶች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ግኝቶች በተጨማሪም የሥራ መሪዎች የተቋሙን እቅድ ለማሳካት በቡድን ተባብረው ያለመስራት፣ ሰራተኞች የተቋሙን እሴቶች፣ ግቦችና የትኩረት መስኮችን ያለመረዳት፣ ሠራተኛው በተቋሙ ስለሚከናወኑ ነገሮች ወቅታዊ መረጃ ያለማግኘት እና የመሳሰሉት በዳሰሳ ጥናቱ ከተገኙ ግኝቶች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ግልጽ የሆነ ተቋማዊ ባህል እንደሌለው የጠቆሙት ስራ አስኪያጁ ጠንካራ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት የአመራር ስርዓቶችን መከለስ፣ የተቋማዊ ባህል ማሻሻያ እርምጃዎችን መተግበር፣ ተቋማዊ መናበብን ማጎልበት፣ የለውጥ ሥራ አመራር ሞዴልን መቅረጽ፣ የሠራተኛ ተግባቦት ሥርዓት መዘርጋት እና የአመራር አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን መቅረጽ እንደሚገባ ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ ለተቋማዊ ባህል ግንባታ የሥራ መሪዎች ድርሻቸው የጎላ መሆኑን በመጠቆም ሠራተኛዉ ተቋማዊ ባህልን ከስራው ጋር አስተሳስሮ መሄድ እንዳለበት አቶ አንዱአለም አሳስበዋል፡፡ በዕለቱ ከዳሰሳ ጥናቱ በተጨማሪ ተቋማዊ ባህልና ውጤቱ በሚል ርዕስ ሰነድ ቀርቧል፡፡ ሰነዱን ያቀረቡት በትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የፕሮጀክቶች እቅድ ክትትል ዳይሬክተር አቶ ልብሰወርቅ አስፋው እንደተናገሩት የተቋምን ራዕይና ተልዕኮ በአግባቡ ለማሳካት ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት ያስፈልጋል፡፡ እንደ አቶ ልብሰ ወርቅ ገለፃ ጠንካራ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት የሠው ሃብት አቅምን ማሳደግ እና በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ ረቂቅ ዳሰሳ ጥናቱ አስፈላጊ መረጃዎች ተካተው በተቋሙ ከፍተኛ የስራ አመራር ከጸደቀ በኋላ ሁሉም ሠራተኛ እንዲያገኘው እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content
+1

በበጎፈቃደኝነትት ደም የለገሱ አመራሮችና ሰራተኞች ተመሰገኑ ..........///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች ዛሬ በዋና መስሪያ ቤት ባደረጉት የደም ልገሳ 44 ዩኒት ደም ተሰብስቧል። የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አስፈፃሚ ቡድን በደም ልገሳው ላይ የተሳተፉ የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞችን ስላደረጉት አስተዋፅኦ አመስገኗል። ደም ለመለገስ አስበውና ወስነው በተለያዩ ምክንያቶች መለገስ ያልቻሉትም በጎነት ከሀሳብ የሚጀመር በመሆኑ ውሳኔያቸው ከልገሳው ያልተለየ በመሆኑ ምስጋና ተችሯቸዋል። ሠራተኛው በጎነትን ከመደበኛ ስራው በተጓዳኝ በማከናወን ለሀገሩ ያለውን ፍቅር እንዲገልፅ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አስፈፃሚ ቡድን አሳስቧል። ነሐሴ 5 ቀን 2013 ዓ/ም