uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 544 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 333-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 158-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 544 obunachiga ega bo‘ldi.

27 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 10 ga, so‘nggi 24 soatda esa -16 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.06% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.33% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 895 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 539 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 7 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 28 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 544
Obunachilar
-1624 soatlar
-97 kunlar
+1030 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+9

photo content

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ   ..........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሥልጣን ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው ሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ላይ ችግኝ ተክለዋል። የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ይገኛል። የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ደዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ ጽዱና አረንጓዴ አካባቢን በመፍጠር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች ጀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና አለው። በመሆኑም የመንግስት ልማት ድርጅቶች ከተጠሪ ተቋማት ጋር የሚያካሂዱት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ማኅበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት ጋር  ተሳስሮ እየተፈጸመ ይገኛል ብለዋል። ከአሁን ቀደም የተተከሉ ችግኞች በጀት ተመድቦ ክትትልና ቁጥጥር በመደረጉ ከ90 በመቶ በላይ መጽደቃቸውን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞችም እንዲጸድቁ ተጠሪ ተቋማቱ በኃላፊነት እንዲሰሩ አሳስበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት ተቋሙ ከተጣለበት አገራዊ ኃላፊነት ባሻገር ባለፉት ዓመታት በተከናውኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ላይ በንቃት ሲሳተፍ ቆይቷል፡፡ ተቋሙ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሥልጣን ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሚያከናውኑት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ላይ ከመሳተፍ በተጨማሪ በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የተጠናከረ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የአካባቢ ጥበቃን ለማጎልበት ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የተቀዳ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ተቋሙ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ለአራተኛ ጊዜ እየተሳተፉ መሆናቸውን የገለጹት አቶ መርክነህ ይገዙ በተቋሙ የሕግ መምሪያ ዳይሬክተር ሁሉም ሠራተኛ ለአገራዊ መርኃ ግብሩ ስኬት የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል። በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለልና ጎርፍ በመከላከል እንዲሁም ተፈጥሯዊ የዝናብ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል። ሌላኛዋ ተሳታፊ በተቋሙ የሠራተኛ አስተዳደር ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ምዕራብ ጋሹ በበኩላቸው ለ3ኛ ጊዜ እየተሳተፉ መሆኑንና በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል። መትከል ብቻ ሳይሆን በየጊዜው የሚተከሉ ችግኞችን ተንከባክቦ ለውጤት እንዲበቁ በማድረግ በኩል ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ ላይ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል፣ የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ኃላፊ አቶ ሙሱጠፋ አባሲመል፣ የሞጆ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባን ጨምሮ አስራ ሁለት የመንግሥት የልማት ድርጅት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+9

photo content
+3

photo content
+9

2⃣ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ነው .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር አካል የሆነ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በሞጆ ሀዋሳ ፈጣን መንገድ ላይ አከናውነዋል። በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ሥራ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ወድነህ የማነ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎችን ከመገንባትና ከማስተዳደር ባለፈ በአረንጓዴ አሻራው ሀገራዊ መርሀ ግብር ላይ በመሳተፍ ጉልህ አሻራውን እያኖረ ይገኛል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል ለመከላከል እንዲሁም በቂ ውሃ እንዲያገኙ በማድረግ የግድቦችን ደህንነት በማስጠበቅ በኩል ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል። ይህም ተቋሙ ለሀገር ዕድገትና ለአህጉራዊ የኃይል ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዘው ኢንጂነር ውድነህ ጠቁመዋል። ተቋሙ ለሚተገብራቸው ሀገራዊ ስትራቴጅዎች የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ሚናው የጎላ ነው ያሉት ኢንጂነር ውድነህ ፕሮግራሙ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲተገበር ሠራተኛውና አመራሩ ድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል። በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ክብሮም ካህሳይ በበኩላቸው ተቋሙ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄዱ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ተቋሙ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር እየሰራ ላለው ሥራ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች በሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ላይሁሉም ሰው በንቃት ሊሳተፍ እንደሚገባ ተናግረዋል። በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢ የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በመንከባከብና በመከታተል ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ለአረንጓዴ አሻራ በተሰጠው ትኩረት አሁን ላይ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን መሰረት ባደረገ የደን ሽፋን ልኬት የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+6

photo content
+9

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1ሺ 1 መቶ በላይ የሥራ መደቦች በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ እንዲሟሉ ተደርጓል …….///……. በ2016 በጀት ዓመት በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ 1 ሺህ 132 የስራ መደቦች መሟላታቸውን በሰው ሀብት ዘርፍ የሰው ሀብት አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ 677 የሥራ መዶቦችን በዕድገት፣ 362 በዝውውር እና 93 በምደባ እንዲሟሉ ተደርጓል፡፡ በበጀት ዓመቱ የሥራ መደቦችን በተፈላጊ የሰው ኃይል ለማሟላት በተሰራው ሥራ 253 ሠራተኞች በውጭ በቅጥር እንዲሟላ መደረጉን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ የፅዳት፣ የጥበቃና የአትክልተኛ ሥራዎችን በሦስተኛ ወገን ለማሰራት በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት 1 ሺህ 962 የሥራ መደቦች እንዲሸፈኑ መደረጉንም አቶ ተማም ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሥራ መሪዎች ምደባ መመሪያ እና የብቃት መመዘኛ ፈተና አፈጻፀም ማንዋል ፀድቀው ወደ ስራ መግባታቸውንም ገልፀዋል፡፡ ከተያዘው ዕቅድ አንፃር በበጀት ዓመቱ በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ የተሟላው የሰው ኃይል 135 በመቶ እና በቅጥር 97 ነጥብ 3 በመቶ መከናወኑን አስረድተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content

ጣቢያው እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል የማስተላለፍ አቅም ይዞ እየሰራ ነው ……….///………. የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቀን እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል ጭነት እየተሸከመ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ሲሳይ አይቸው እንደተናገሩት ጣቢያው በአቅራቢያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች፣ ለቢሾፍቱ፣ ለዱከም እና ሞጆ ከተሞች በቀን እስከ 50 ሜጋ ዋት በማቅረብ ላይ ይገኛል። ቀሪውን 30 ሜጋ ዋት ደግሞ በዳታ ማይኒንግ ለተሰማራ የውጭ ኩባንያዎች በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያመነጨ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ጣቢያው የኃይል ስርጭቱን የሚያሳልጡ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 600 ሜጋ ቮልት አምፒር እንዲሁም አራት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ያሉት መሆኑንም ነው አቶ ሲሳይ የገለፁት። እንደ ኃላፊው ማብራሪያ የጣቢያው ስድስት የኃይል ትራንስፎርመሮች እያንዳንዳቸው የእሳት መከላከያ መሳሪያ የተገጠመላቸው መሆኑ ጣቢያውን ከሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለየት ያደርገዋል። በማከፋፈያ ጣቢያው የተገነቡት ደረጃቸውን የጠበቁ የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶች ምቹ የሥራ አካባቢ በመፍጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል። የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በ2012 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+6

በትምህርት ላይ ያገኙትን ዕውቀት በሥራ ላይ ለማዋል እንደሚተጉ ተመራቂዎች ገለፁ …//… የጊቤ-3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ያሰለጠናቸውን 27 ወንድ እና 2 ሴት ሠራተኞች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በማመንጫ ጣቢያው ግቢ ውስጥ አስመርቋል። ከተመራቂዎች መካከል በጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ተወካይ ኃላፊ የሆነው ታሪኩ ጠንክር እንደገለፀው ላለፉት 5 ዓመታት ከሥራ ጎን ለጎን ትምህርቱን በትጋት ሲከታተል መቆየቱን ተናግሯል፡፡ በዚህም 3 ነጥብ 98 በማምጣት ከትምህርት ክፍሉና ከዩኒቨርሲቲው የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ተከትሎ የወርቅ ሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ ተሸልሟል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የመካከለኛ ክሊኒክ የህክምና ባለሙያ የሆነው ሔኖክ ተካልኝ እንደተናገረው በዋቻሞ ዩኒቨርስቲ በተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ (ፓወር ስትሪም) ለ5 ዓመታት ትምህርቱን ተከታትሏል፡፡ በጣቢያው ውስጥ የህክምና ባለሙያ ብሆንም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ያመቻቹትን ዕድል በመጠቀም ለዚህ ክብር በቅቻለሁ ብሏል፡፡ ሔኖክ 3 ነጥብ 89 በማምጣት ከትምህርት ክፍሉና ከዩኒቨርሲቲው የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ተከትሎ በከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ሜዳሊያ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ ለመሸለም በቅቷል፡፡ በዕለቱ ከተመረቁ የጣቢያው ሴት ሠራተኞች መካከል የሆነችው ብርቱካን አቢ እንደገለፀችው ባለፉት 5 ዓመታት በንድፈ ሃሳብ የቀሰመችውን ዕውቀት በስራ ላይ በማዋል የኃይል ማመንጫውን የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራ ለማቀላጠፍ እንደሚረዳት ተናግራለች፡፡ በጣቢያው በቆችባቸው 10 ዓመታት ያገኘቻቸው ልምዶች ለትምህርቷ አጋዥ እንደሆኑላትም ነው የጠቀሰችው፡፡ ብርቱካን 3 ነጥብ 21 ውጤት መስመዝገቧን ተከትሎ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ የወርቅ ሜዳሊያ ለመሸለም በቅታለች፡፡ ተመራቂዎቹ በዩኒቨርስቲው የፖወር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ እንዲከፈት መሠረት የጣሉትና በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ትምህርቱ እንዲሰጥ የዩኒቨርስቲውን ሴኔት ያሳመኑትን የቀድሞው የዩኒቨርስቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕረዚዳንት ዶ/ር አሻሞ ኤራንቆን እና መምህራኖቻቸውን እንዲሁም የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይልን አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 09 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+5

photo content
+9

photo content

የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች እና የዩኒቨርስቲው ምሁራን የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን ጎበኙ ……...///………. የወላይታ ዞን አስተዳደር፣ የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላትና የፓወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ መምህራን የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ። ጉብኝቱ የተካሔደው የጣቢያው ሠራተኞች በዩኒቨርስቲው የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ (ፓወር ስትሪም) ለ5 ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በተመረቁበት ወቅት ነው። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ገለፃ ያደረጉት የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት የኃይል ማመንጫው በማመንጨት አቅሙ አሁን በሥራ ላይ ካሉት መካከል ከፍተኛ ሲሆን የታላቁ ኤትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የሁለተኛነት ደረጃ የሚይዝ ነው። ሥራ አስኪያጁ የኃይል ማመንጫው ስለሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች፣ የግድብ ደህንነት ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የኃይል ማምረት ሂደት ለጎብኚዎቹ ገለፃ አድርገዋል። የወላይታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩት ዞኑ በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ በመሆኑ የኃይል ማመንጫው የዚህ ትሩፋት ውጤት ነው። የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሀገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ በመሆኑ የዞኑ አስተዳደር በልዩ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው ገልፀዋል። ዞኑ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር ለኢትዮጵያ መሰረተልማቶች መጠበቅ ሁሉን አቀፍ እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም ነው ኃላፊው የጠቀሱት። በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን የስርቆት ወንጀል ለመከላከል የዞኑ የፀጥታና ፍትህ አካላት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ፣ ምርምርና ማህበረሰብ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ታገሰ በበኩላቸው በጊቤ ተፋሰስ ላይ የሚገኙት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በፓወር ኢንጅነሪንግ የምርምር ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። ዩኒቨርስቲው "ብርሃናችሁ በማህበረሰቡ ውስጥ ይብራ!" የሚለውን መሪ ቃል ተግባራዊ ለማድረግ ለማህበረሰቡና ለተቋማት ችግር ፈቺ የሆኑ ምርምሮችን በማከናወን ጉልህ ድርሻ የሚሰጣቸው ውጤቶች ማስመዝገቡን ተናግረዋል። ዩኒቨርስቲው የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዶ/ር ታምራት በጊቤ 1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እየተማሩና እየተመረቁ የሚገኙ ሠራተኞች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል። በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ የተመረቁት የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች የሀገር ጀግኖች ናቸው ሲሉም ነው ያወደሱት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ሐምሌ 08 ቀን 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ

photo content
+9