EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 544 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 333,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 158 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 544 名订阅者。
根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 10,过去 24 小时变化为 -16,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.06%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.33% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 895 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 7。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 544
订阅者
-1624 小时
-97 天
+1030 天
帖子存档
15 544
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራርና ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
..........///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሥልጣን ተጠሪ የሆኑ ተቋማት ከኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው ሞጆ ሐዋሳ የፍጥነት መንገድ ላይ ችግኝ ተክለዋል።
የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ይገኛል።
የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ደዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል እንደገለጹት የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ ጽዱና አረንጓዴ አካባቢን በመፍጠር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች ጀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና አለው።
በመሆኑም የመንግስት ልማት ድርጅቶች ከተጠሪ ተቋማት ጋር የሚያካሂዱት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ማኅበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት ጋር ተሳስሮ እየተፈጸመ ይገኛል ብለዋል።
ከአሁን ቀደም የተተከሉ ችግኞች በጀት ተመድቦ ክትትልና ቁጥጥር በመደረጉ ከ90 በመቶ በላይ መጽደቃቸውን የተናገሩት አቶ ሀብታሙ ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞችም እንዲጸድቁ ተጠሪ ተቋማቱ በኃላፊነት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለጹት ተቋሙ ከተጣለበት አገራዊ ኃላፊነት ባሻገር ባለፉት ዓመታት በተከናውኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ላይ በንቃት ሲሳተፍ ቆይቷል፡፡
ተቋሙ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባለሥልጣን ተጠሪ የሆኑ ተቋማት በሚያከናውኑት የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ላይ ከመሳተፍ በተጨማሪ በሁሉም የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የተጠናከረ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የአካባቢ ጥበቃን ለማጎልበት ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የተቀዳ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ተቋሙ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ለአራተኛ ጊዜ እየተሳተፉ መሆናቸውን የገለጹት አቶ መርክነህ ይገዙ በተቋሙ የሕግ መምሪያ ዳይሬክተር ሁሉም ሠራተኛ ለአገራዊ መርኃ ግብሩ ስኬት የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለልና ጎርፍ በመከላከል እንዲሁም ተፈጥሯዊ የዝናብ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
ሌላኛዋ ተሳታፊ በተቋሙ የሠራተኛ አስተዳደር ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ምዕራብ ጋሹ በበኩላቸው ለ3ኛ ጊዜ እየተሳተፉ መሆኑንና በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል።
መትከል ብቻ ሳይሆን በየጊዜው የሚተከሉ ችግኞችን ተንከባክቦ ለውጤት እንዲበቁ በማድረግ በኩል ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ ላይ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል፣ የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ኃላፊ አቶ ሙሱጠፋ አባሲመል፣ የሞጆ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባን ጨምሮ አስራ ሁለት የመንግሥት የልማት ድርጅት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
15 544
2⃣
የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብሩ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ ወሳኝ ነው
.........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር አካል የሆነ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በሞጆ ሀዋሳ ፈጣን መንገድ ላይ አከናውነዋል።
በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ሥራ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ወድነህ የማነ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫዎችን ከመገንባትና ከማስተዳደር ባለፈ በአረንጓዴ አሻራው ሀገራዊ መርሀ ግብር ላይ በመሳተፍ ጉልህ አሻራውን እያኖረ ይገኛል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል ለመከላከል እንዲሁም በቂ ውሃ እንዲያገኙ በማድረግ የግድቦችን ደህንነት በማስጠበቅ በኩል ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
ይህም ተቋሙ ለሀገር ዕድገትና ለአህጉራዊ የኃይል ትስስር መሰረት የሚሆን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዘው ኢንጂነር ውድነህ ጠቁመዋል።
ተቋሙ ለሚተገብራቸው ሀገራዊ ስትራቴጅዎች የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ሚናው የጎላ ነው ያሉት ኢንጂነር ውድነህ ፕሮግራሙ ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲተገበር ሠራተኛውና አመራሩ ድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።
በተቋሙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ክብሮም ካህሳይ በበኩላቸው ተቋሙ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በተካሄዱ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ተቋሙ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር እየሰራ ላለው ሥራ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች በሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ላይሁሉም ሰው በንቃት ሊሳተፍ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢ የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በመንከባከብና በመከታተል ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ለአረንጓዴ አሻራ በተሰጠው ትኩረት አሁን ላይ ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን መሰረት ባደረገ የደን ሽፋን ልኬት የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 13 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
15 544
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1ሺ 1 መቶ በላይ የሥራ መደቦች በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ እንዲሟሉ ተደርጓል
…….///…….
በ2016 በጀት ዓመት በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ 1 ሺህ 132 የስራ መደቦች መሟላታቸውን በሰው ሀብት ዘርፍ የሰው ሀብት አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ተማም አፍደል እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ 677 የሥራ መዶቦችን በዕድገት፣ 362 በዝውውር እና 93 በምደባ እንዲሟሉ ተደርጓል፡፡
በበጀት ዓመቱ የሥራ መደቦችን በተፈላጊ የሰው ኃይል ለማሟላት በተሰራው ሥራ 253 ሠራተኞች በውጭ በቅጥር እንዲሟላ መደረጉን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
የፅዳት፣ የጥበቃና የአትክልተኛ ሥራዎችን በሦስተኛ ወገን ለማሰራት በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት 1 ሺህ 962 የሥራ መደቦች እንዲሸፈኑ መደረጉንም አቶ ተማም ተናግረዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሥራ መሪዎች ምደባ መመሪያ እና የብቃት መመዘኛ ፈተና አፈጻፀም ማንዋል ፀድቀው ወደ ስራ መግባታቸውንም ገልፀዋል፡፡
ከተያዘው ዕቅድ አንፃር በበጀት ዓመቱ በዕድገት፣ በዝውውርና በምደባ የተሟላው የሰው ኃይል 135 በመቶ እና በቅጥር 97 ነጥብ 3 በመቶ መከናወኑን አስረድተዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
15 544
ጣቢያው እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል የማስተላለፍ አቅም ይዞ እየሰራ ነው
……….///……….
የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቀን እስከ 80 ሜጋ ዋት ኃይል ጭነት እየተሸከመ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ።
ኃላፊው አቶ ሲሳይ አይቸው እንደተናገሩት ጣቢያው በአቅራቢያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች፣ ለቢሾፍቱ፣ ለዱከም እና ሞጆ ከተሞች በቀን እስከ 50 ሜጋ ዋት በማቅረብ ላይ ይገኛል።
ቀሪውን 30 ሜጋ ዋት ደግሞ በዳታ ማይኒንግ ለተሰማራ የውጭ ኩባንያዎች በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያመነጨ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
ጣቢያው የኃይል ስርጭቱን የሚያሳልጡ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ሁለት ባለ 600 ሜጋ ቮልት አምፒር እንዲሁም አራት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ያሉት መሆኑንም ነው አቶ ሲሳይ የገለፁት።
እንደ ኃላፊው ማብራሪያ የጣቢያው ስድስት የኃይል ትራንስፎርመሮች እያንዳንዳቸው የእሳት መከላከያ መሳሪያ የተገጠመላቸው መሆኑ ጣቢያውን ከሌሎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለየት ያደርገዋል።
በማከፋፈያ ጣቢያው የተገነቡት ደረጃቸውን የጠበቁ የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶች ምቹ የሥራ አካባቢ በመፍጠር ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ተናግረዋል።
የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በ2012 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
15 544
በትምህርት ላይ ያገኙትን ዕውቀት በሥራ ላይ ለማዋል እንደሚተጉ ተመራቂዎች ገለፁ
…//…
የጊቤ-3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ያሰለጠናቸውን 27 ወንድ እና 2 ሴት ሠራተኞች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በማመንጫ ጣቢያው ግቢ ውስጥ አስመርቋል።
ከተመራቂዎች መካከል በጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ተወካይ ኃላፊ የሆነው ታሪኩ ጠንክር እንደገለፀው ላለፉት 5 ዓመታት ከሥራ ጎን ለጎን ትምህርቱን በትጋት ሲከታተል መቆየቱን ተናግሯል፡፡
በዚህም 3 ነጥብ 98 በማምጣት ከትምህርት ክፍሉና ከዩኒቨርሲቲው የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ተከትሎ የወርቅ ሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ ተሸልሟል።
በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የመካከለኛ ክሊኒክ የህክምና ባለሙያ የሆነው ሔኖክ ተካልኝ እንደተናገረው በዋቻሞ ዩኒቨርስቲ በተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ (ፓወር ስትሪም) ለ5 ዓመታት ትምህርቱን ተከታትሏል፡፡
በጣቢያው ውስጥ የህክምና ባለሙያ ብሆንም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ያመቻቹትን ዕድል በመጠቀም ለዚህ ክብር በቅቻለሁ ብሏል፡፡
ሔኖክ 3 ነጥብ 89 በማምጣት ከትምህርት ክፍሉና ከዩኒቨርሲቲው የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ተከትሎ በከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ሜዳሊያ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ ለመሸለም በቅቷል፡፡
በዕለቱ ከተመረቁ የጣቢያው ሴት ሠራተኞች መካከል የሆነችው ብርቱካን አቢ እንደገለፀችው ባለፉት 5 ዓመታት በንድፈ ሃሳብ የቀሰመችውን ዕውቀት በስራ ላይ በማዋል የኃይል ማመንጫውን የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራ ለማቀላጠፍ እንደሚረዳት ተናግራለች፡፡
በጣቢያው በቆችባቸው 10 ዓመታት ያገኘቻቸው ልምዶች ለትምህርቷ አጋዥ እንደሆኑላትም ነው የጠቀሰችው፡፡
ብርቱካን 3 ነጥብ 21 ውጤት መስመዝገቧን ተከትሎ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት እጅ የወርቅ ሜዳሊያ ለመሸለም በቅታለች፡፡
ተመራቂዎቹ በዩኒቨርስቲው የፖወር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ እንዲከፈት መሠረት የጣሉትና በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ትምህርቱ እንዲሰጥ የዩኒቨርስቲውን ሴኔት ያሳመኑትን የቀድሞው የዩኒቨርስቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕረዚዳንት ዶ/ር አሻሞ ኤራንቆን እና መምህራኖቻቸውን እንዲሁም የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይልን አመስግነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 09 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
15 544
የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች እና የዩኒቨርስቲው ምሁራን የኃይል ማመንጫ ጣቢያውን ጎበኙ
……...///……….
የወላይታ ዞን አስተዳደር፣ የዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የሴኔት አባላትና የፓወር ኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፍ መምህራን የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ጎበኙ።
ጉብኝቱ የተካሔደው የጣቢያው ሠራተኞች በዩኒቨርስቲው የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር ፕሮግራም በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ (ፓወር ስትሪም) ለ5 ዓመታት ትምህርታቸውን ተከታትለው በተመረቁበት ወቅት ነው።
በመስክ ጉብኝቱ ወቅት ገለፃ ያደረጉት የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት የኃይል ማመንጫው በማመንጨት አቅሙ አሁን በሥራ ላይ ካሉት መካከል ከፍተኛ ሲሆን የታላቁ ኤትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የሁለተኛነት ደረጃ የሚይዝ ነው።
ሥራ አስኪያጁ የኃይል ማመንጫው ስለሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎች፣ የግድብ ደህንነት ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የኃይል ማምረት ሂደት ለጎብኚዎቹ ገለፃ አድርገዋል።
የወላይታ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ታደሰ ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩት ዞኑ በተፈጥሮ የታደለ አካባቢ በመሆኑ የኃይል ማመንጫው የዚህ ትሩፋት ውጤት ነው።
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለሀገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ በመሆኑ የዞኑ አስተዳደር በልዩ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው ገልፀዋል።
ዞኑ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር ለኢትዮጵያ መሰረተልማቶች መጠበቅ ሁሉን አቀፍ እገዛ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም ነው ኃላፊው የጠቀሱት።
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀመውን የስርቆት ወንጀል ለመከላከል የዞኑ የፀጥታና ፍትህ አካላት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ፣ ምርምርና ማህበረሰብ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ታገሰ በበኩላቸው በጊቤ ተፋሰስ ላይ የሚገኙት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በፓወር ኢንጅነሪንግ የምርምር ዘርፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
ዩኒቨርስቲው "ብርሃናችሁ በማህበረሰቡ ውስጥ ይብራ!" የሚለውን መሪ ቃል ተግባራዊ ለማድረግ ለማህበረሰቡና ለተቋማት ችግር ፈቺ የሆኑ ምርምሮችን በማከናወን ጉልህ ድርሻ የሚሰጣቸው ውጤቶች ማስመዝገቡን ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲው የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዶ/ር ታምራት በጊቤ 1፣ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እየተማሩና እየተመረቁ የሚገኙ ሠራተኞች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል።
በኤሌክትሪካልና ኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ የትምህርት መስክ የተመረቁት የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች የሀገር ጀግኖች ናቸው ሲሉም ነው ያወደሱት።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
ሐምሌ 08 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ | ቴሌግራም | ትዊተር | ዩትዩብ ቻናል | ቲክቶክ | ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
