uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 530 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 328-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 176-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 530 obunachiga ega bo‘ldi.

06 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 6 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 27.84% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.05% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 323 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 492 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 07 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 530
Obunachilar
-324 soatlar
-97 kunlar
+630 kunlar
Postlar arxiv
photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የማመንጨት አቅምን ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ እየተሰራ ነው …………///………….. በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈፃሚ የቴክኒክ አማካሪ አስታወቁ፡፡ አማካሪው ኢንጂነር አንዳርጌ እሸቴ እንደገለፁት በአሁኑ ሰዓት በሀገሪቱ ያለዉ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም 4 ሺህ 528 ሜጋ ዋት ደርሷል፡፡ በቀጣዮቹ 5 ዓመታት 13 ሺህ ሜጋ ዋት እንዲሁም በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ ዕቅድ ተነድፎ እየተራ ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከጀመረ ከአንድ ምዕተ ዓመት የዘለለ ዕድሜ ቢያስቆጥርም የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋኑ ግን ከ44 በመቶ እንዳልዘለለ ኢንጂነር አንዳርጌ ገልፀዋል፡፡ የዚህም ምክንያቱ በተለያዩ ምክንያቶች በሃገሪቱ ያለው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ያለመስፋፋቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አማካሪው ገለፃ ከዚህ በፊት የነበረው የኢነርጂ ፖሊሲ የግል ባለሃብቶች በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እንዲሳተፉ የሚጋብዝ ባለመሆኑ ለኃይል ማመንጨትና እቅም ማነስና ለተደራሽነት ሽፋኑ ማነስ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል፡፡ በመንግስት አቅም ብቻ እቅዱን ማሳካት እንደማይቻል የተናገሩት ኢንጂነር አንዳርጌ ከዚህ ጎን ለጎንም በግልና የመንግስት አጋርነትን መርሃግብር የግል አልሚዎች በኃይል ልማት ዘርፍ እንዲሰማሩ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በዚህም በዕቅዱ የተያዘውን የማመንጨት አቅም ለማሳካት ተስፋ ተጥሎበታል ሲሉ ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል የሚውል በርካታ የታዳሽ ኃይል ምንጭ ያላት ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የግል ባለሃብቱ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ፣ በዲቼቶና ጋድ የፀሃይ ኃይል እና በኮርቤቴ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ መሆን ጀምረዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላው ሀገሪቱ የዲዝል መጠባበቂያ ኃይል ማመንጫዎችን ጨምሮ 23 ማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡ ኢንጂነር አንዳርጌ እንደገለፁት መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት በሚከናወነው ሥራ ለፕሮጀክቶች ግንባታ የሚመረጡ ቦታዎችን ከወሰን ማስከበር በወቅቱ ነፃ በማድረግ፣ መመሪያ ከሚፈቅደው በላይ ተገቢ ያልሆነ የካሳ ጥያቄ ባለማቅረብና በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን በመከላከል ህብረተሰቡ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

በትግራይ ተቋርጦ የሰነበተው ኤሌክትሪክ ዳግም ተገናኝቷል ............./////........ በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በደረሰ ጉዳት ከአንድ ሳምንት በላይ ተቋርጦ የነበረው የትግራይ ኤሌክትሪክ ዳግም ተገናኝቷል። ለቀናት ሲከናወን የነበረው መልሶ የመጠገን ስራ በስኬት በመጠናቀቁ የትግራይ ከተሞች ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝተዋል። ከአላማጣ -መሆኒ -መቐለ የተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የካቲት 9 ቀን 2013 ዓ/ም በተሰነዘበት ጥቃት ጉዳት እንደደረሰበት መግለፃችን ይታወሳል። ይህን ተከትሎ ለቀናት ሲካሄድ የቆየው የከፍተኛ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ ከዚህ በፊት ኤሌክሪትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞች ዛሬ ከቀኑ 10:20 ጀምሮ ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል። በወልቃይትና አካባቢው የሚገኙ ከተሞችን ኤሌኬክትሪክ ለማገናኘት የተጀመረው ጥረት አሁንም እንደቀጠለ ነው። በዚህ አጋጣሚ የጥገና ባለሙያዎቻችን መስመሩን ለማገናኘት ላደረጉት ጥረት የተቋማችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ምስጋና አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 17 ቀን 2013 ዓ.ም

ዜና እረፍት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወንድሜነህ ልሳነወርቅ በተወለዱ በ54 ዓመታቸው በትላንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ አቶ ወንድሜነህ ከአባታቸው ከአቶ ልሳነወርቅ በየነ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዘነበች ያደቴ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምዕራብ ሸዋ ዞን ጀልዱ ወረዳ ጉባ ሰርባ በሚባል ቀበሌ የካቲት 5 ቀን 1959 ዓ.ም ነበር የተወለዱት፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ በትውልድ ቀያቸው ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን በ1986 ዓ.ም ከአምቦ የእርሻ ኮሌጅ በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2000 ዓ.ም በሂሳብ አያያዝና ምርመራ /accounting and auditing የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በ2009 ዓ.ም ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ አስተዳደር የትምህርት መስክ ተከታትለው ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡ አቶ ወንድሜነህ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ የስራ መስኮች ከባለሙያነት እስከ ሥራ ኃላፊነት ደረጃ ድረስ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን ማገልገላቸውን ከግል ማህደራቸው የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ በዚህ መሠረትም፡- • ከሐምሌ 1978 ዓ.ም እስከ ግንቦት 30 ቀን 1992 ዓ.ም በመምህርነት • ከሰኔ 1 ቀን 1992 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 1997 ዓ.ም በአምቦ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በሂሳብ አያያዝ ኃላፊነት • ከታህሳስ 1 ቀን 1997 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 1997 ዓ.ም በአምቦ ወረዳ የህብረት ስራ ማህበራት ጽ/ቤት የገጠር ፋይናንስ ግንኙነት ፕሮግራም ተጠሪ • ከሚያዚያ 1 ቀን 1997 ዓ.ም እስከ መስከረም 25 ቀን 2002 ዓ.ም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምዕራብ ሸዋ ዞን የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ መምሪያ የኦዲትና ቁጥጥር ኃላፊ • ከመስከረም 26 ቀን 2002 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2002 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ ዞን በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ልማት ጽ/ቤት በከፍተኛ ኦዲተርነት • ከታህሳስ 12 ቀን 2002 ዓ.ም እስከ መስከረም 8 ቀን 2011 ዓም በገንዘብ ሚኒስቴር በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት የስራ መደብ ከባለሙያነት እስከ ቡድን መሪነት እንዲሁም • ከጥቅምት 1 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ ሕይወታቸው እስከ አለፈበት የካቲት 15 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዳይሬክተር በመሆን ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይሉ አገራቸውንና ህዝባቸውን በማገልገል ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ ባለትዳርና የአንድ ወንድና የሁለት ሴት ልጆች አባት የነበሩ ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓታቸው በዛሬው እለት በአምቦ መካነኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ላለፉት 29 ዓመታት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ያገለገሉት የአቶ ልዑል ለገሰ ስርዓተ ቀብር ትናንት የካቲት 15 ቀን 2013 ዓም በአዲስ አበባ ተፈጽሟል፡፡ አቶ ልዑል ከአባታቸው ከአቶ ለገሰ አመጠ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወርቅነሽ በላቸው ጥር 27 ቀን 1963 ዓ.ም በቀድሞው ሸዋ ክፍለ ሀገር መርሃቤቴ አውራጃ ቢጣ በለው ወረዳ ነበር የተወለዱት፡፡ አቶ ልዑል እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ቢጣ ጀግኖች 1ኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡ ከዚህ በኋላ በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ድግሪ ድረስ ተምረዋል፡፡ አቶ ልዑል ከረጅም ጊዜ ትምህርት በተጨማሪም ሙያቸውን ለማሳደግ የተለያዩ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎችን ተከታትለዋል፡፡ በ1984 ዓ.ም በቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ባለስልጣን በአሁኑ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቴክኒሽያንነት ሥራ የጀመሩት አቶ ልዑል ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ተቋሙ ባሉት የተለዩዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በቴክኒሽያንነት፣ በፎርማንነት፣ በዲስትሪክት ሱፐርቫይዘርነት፣ በዲስትሪቢዩሽን ኢንጅነርነት፣ በኮምፒውተር ፐሮግራመርት እና በአይሲቲ አፕሊኬሽን ኦፊሰርነት የስራ መደቦች ላይ ላለፉት 29 ዓመታት ተቋሙን በሙያቸው አገልግለዋል፡፡ አቶ ሉሌ በተወለዱ በ50 ዓመታቸው በድንገት ህይወታቸው ከዚህ ዓለም የተለየ ሲሆን ስርዓተ ቀብራቸውም በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ገርጂ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ የአቶ ልዑል ለገሰ የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ፣ ማኔጅመንትና ሠራተኞችም በአቶ ወንድሜነህ ልሳነወርቅ እና አቶ ልዑል ለገሰ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለፅ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

ዜና እረፍት
ዜና እረፍት

photo content

photo content

photo content

የሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል …………..//////………… ከአዲስ አበባ በ561 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በደቡብ ክልል በቤንቺ ማጂ ዞን በሚዛን ከተማ የሚገኘው የሚዛን 132/66/33/15 ኪ.ቮ. ከፍተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ተገቢውን አገልግሎት እየሠጠ ይገኛል፡፡ የጣቢያው ተወካይ ኃላፊ ወ/ት ታደለች ተረፈ እንደተናገሩት በ1998 ዓ.ም. ከቦንጋ ማከፋፈያ ጣቢያ 132 ኪ.ቮ. በመቀበል ለሚዛን ከተማና ለአካባቢው በ15 እና 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች ኃይል በመስጠት በይፋ ሥራ የጀመረው ጣቢያው አገልግሎቱን ሳያቋርጥ እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ እንደተወካይ ኃላፊዋ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ለሚዛን ከተማ ፣ ለሸኮ ወረዳ እና ለአካባቢው ሃይል ሲሰጥ በ 33 ኪ.ቮ ወጪ መስመሮች ደግሞ ለጨና፣ ለዲማ ወረዳዎች እና ለአካባቢው ኃይል በማቅረብ የሚጠበቅበትን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው በደቡብ ምዕራብ ሪጅን ስር ካሉት 14 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል ከኃላፊነት ጀምሮ የሴቶች ሚና ጎልቶ የሚታየበትና የጣቢያው ኃላፊን ጨምሮ ሁለት ኦፕሬተሮች ሴቶች የሚገኙበት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2013 ዓ.ም

በመላው ትግራይ ኤሌክትሪክ ዳግም ተቋረጠ ………../////…………. የጁንታው ርዝራዦች በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በፈፀሙት ጥቃት በመላው ትግራይ ኤሌክትሪክ ተቋርጧል፡፡ የጁንታው ርዝራዦች አዲጉዶም በተባለ አካባቢ ከአላማጣ - መሆኒ - መቐለ በተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባደረሱት ጥቃት ነው በክልሉ ኤሌክትሪክ የተቋረጠው፡፡ ከዚህ ቀደም መስመሩ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት እንደነበረና ለመጠገንም ረዘም ያለ ጊዜ እንደወሰደ ይታወሳል፡፡ ክልሉ ኃይል ከሚያገኝባቸው መስመሮች አንዱ የአላማጣ - መሆኒ - መቐለ መስመር ሲሆን የተከዜ አክሱም መስመር ደግሞ የጥገና ሥራው እየተከናወነ እንደነበር መገለፁ አይዘነጋም፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወደመውን መሰረተ ልማት ዳግም በመጠገን መልሶ ኃይል ለመስጠት እየሰራ ይገኛል:: የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 10 ቀን 2013 ዓ.ም

በአባ ወረዳ አዲስ ባለ132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊገነባ ነው …………/////…….. በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን በአባ ወረዳ በ48 ሚሊዮን ብር ወጪ አዲስ ባለ 132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊገነባ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሰብስቴሽንና ትራንስሚሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኽኝ እንደገለፁት 1998 ዓ.ም. ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአባ ባለ 132/33 ኪ.ቮ. ማከፋፈያ ጣቢያ በ2012 ዓ.ም. በደረሰበት የመሬት መሸራተት የተነሳ አገልግሎት አቋርጧል፡፡ በመሆኑም ችግር የገጠመውን ማከፋፈያ ጣቢያ በአዲስ ባለ132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለመተካት መወሰኑን ተናግረዋል፡፡ አካባቢው ኃይል እንዳያጣ አደጋው በደረሰበት ወቅት ተቀሳቃሽ (የሞባይል) የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በጊዜያዊነት መተከሉን ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል፡፡ ተንቀሳቀሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ባሉት 3 ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች ለዳወሮ እና ለኮንታ ዞኖች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሚገኝበት ቦታ የኦሞ ሸለቆ ውስጥ የሚገኝበት በመሆኑ ተደጋጋሚ የመሬት መሸራተት የሚከሰትበት አስቸጋሪ ቦታ ነው ፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም በተደረገው የአፈር ጥናት ከነባሩ ማከፋፈያ ጣቢያ በ18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ስሙ ቦሪቃ በሚባል አለታማ ቦታ ላይ አዲስ ማከፋፈያ ለመገንባት የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ዳሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ የግንባታ ሥራው በተቋሙ የራስ ኃይል በሁለት ዓመት ያልቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አባ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከአዲስ አበባ በ451 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 08 ቀን 2013 ዓ.ም