EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 530 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 328,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 530 名订阅者。
根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 27.84%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.05% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 323 次浏览,首日通常累积 2 492 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 530
订阅者
-324 小时
-97 天
+630 天
帖子存档
15 527
በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የማመንጨት አቅምን ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ እየተሰራ ነው
…………///…………..
በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የዋና ሥራ አስፈፃሚ የቴክኒክ አማካሪ አስታወቁ፡፡
አማካሪው ኢንጂነር አንዳርጌ እሸቴ እንደገለፁት በአሁኑ ሰዓት በሀገሪቱ ያለዉ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም 4 ሺህ 528 ሜጋ ዋት ደርሷል፡፡
በቀጣዮቹ 5 ዓመታት 13 ሺህ ሜጋ ዋት እንዲሁም በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ከ17 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ለማድረስ ዕቅድ ተነድፎ እየተራ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከጀመረ ከአንድ ምዕተ ዓመት የዘለለ ዕድሜ ቢያስቆጥርም የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋኑ ግን ከ44 በመቶ እንዳልዘለለ ኢንጂነር አንዳርጌ ገልፀዋል፡፡
የዚህም ምክንያቱ በተለያዩ ምክንያቶች በሃገሪቱ ያለው የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ያለመስፋፋቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
እንደ አማካሪው ገለፃ ከዚህ በፊት የነበረው የኢነርጂ ፖሊሲ የግል ባለሃብቶች በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እንዲሳተፉ የሚጋብዝ ባለመሆኑ ለኃይል ማመንጨትና እቅም ማነስና ለተደራሽነት ሽፋኑ ማነስ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል፡፡
በመንግስት አቅም ብቻ እቅዱን ማሳካት እንደማይቻል የተናገሩት ኢንጂነር አንዳርጌ ከዚህ ጎን ለጎንም በግልና የመንግስት አጋርነትን መርሃግብር የግል አልሚዎች በኃይል ልማት ዘርፍ እንዲሰማሩ ይደረጋል ብለዋል፡፡
በዚህም በዕቅዱ የተያዘውን የማመንጨት አቅም ለማሳካት ተስፋ ተጥሎበታል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል የሚውል በርካታ የታዳሽ ኃይል ምንጭ ያላት ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የግል ባለሃብቱ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ፣ በዲቼቶና ጋድ የፀሃይ ኃይል እና በኮርቤቴ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ መሆን ጀምረዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላው ሀገሪቱ የዲዝል መጠባበቂያ ኃይል ማመንጫዎችን ጨምሮ 23 ማመንጫ ጣቢያዎችን ያስተዳድራል፡፡
ኢንጂነር አንዳርጌ እንደገለፁት መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት በሚከናወነው ሥራ ለፕሮጀክቶች ግንባታ የሚመረጡ ቦታዎችን ከወሰን ማስከበር በወቅቱ ነፃ በማድረግ፣ መመሪያ ከሚፈቅደው በላይ ተገቢ ያልሆነ የካሳ ጥያቄ ባለማቅረብና በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን በመከላከል ህብረተሰቡ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
በትግራይ ተቋርጦ የሰነበተው ኤሌክትሪክ ዳግም ተገናኝቷል
............./////........
በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በደረሰ ጉዳት ከአንድ ሳምንት በላይ ተቋርጦ የነበረው የትግራይ ኤሌክትሪክ ዳግም ተገናኝቷል።
ለቀናት ሲከናወን የነበረው መልሶ የመጠገን ስራ በስኬት በመጠናቀቁ የትግራይ ከተሞች ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝተዋል።
ከአላማጣ -መሆኒ -መቐለ የተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የካቲት 9 ቀን 2013 ዓ/ም በተሰነዘበት ጥቃት ጉዳት እንደደረሰበት መግለፃችን ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ ለቀናት ሲካሄድ የቆየው የከፍተኛ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ ከዚህ በፊት ኤሌክሪትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞች ዛሬ ከቀኑ 10:20 ጀምሮ ኤሌክትሪክ ማግኘት ችለዋል።
በወልቃይትና አካባቢው የሚገኙ ከተሞችን ኤሌኬክትሪክ ለማገናኘት የተጀመረው ጥረት አሁንም እንደቀጠለ ነው።
በዚህ አጋጣሚ የጥገና ባለሙያዎቻችን መስመሩን ለማገናኘት ላደረጉት ጥረት የተቋማችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
የካቲት 17 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
ዜና እረፍት
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወንድሜነህ ልሳነወርቅ በተወለዱ በ54 ዓመታቸው በትላንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
አቶ ወንድሜነህ ከአባታቸው ከአቶ ልሳነወርቅ በየነ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዘነበች ያደቴ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምዕራብ ሸዋ ዞን ጀልዱ ወረዳ ጉባ ሰርባ በሚባል ቀበሌ የካቲት 5 ቀን 1959 ዓ.ም ነበር የተወለዱት፡፡
ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ በትውልድ ቀያቸው ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን በ1986 ዓ.ም ከአምቦ የእርሻ ኮሌጅ በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡
ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2000 ዓ.ም በሂሳብ አያያዝና ምርመራ /accounting and auditing የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በ2009 ዓ.ም ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ አስተዳደር የትምህርት መስክ ተከታትለው ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡
አቶ ወንድሜነህ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ የስራ መስኮች ከባለሙያነት እስከ ሥራ ኃላፊነት ደረጃ ድረስ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን ማገልገላቸውን ከግል ማህደራቸው የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡
በዚህ መሠረትም፡-
• ከሐምሌ 1978 ዓ.ም እስከ ግንቦት 30 ቀን 1992 ዓ.ም በመምህርነት
• ከሰኔ 1 ቀን 1992 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 1997 ዓ.ም በአምቦ ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በሂሳብ አያያዝ ኃላፊነት
• ከታህሳስ 1 ቀን 1997 ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 1997 ዓ.ም በአምቦ ወረዳ የህብረት ስራ ማህበራት ጽ/ቤት የገጠር ፋይናንስ ግንኙነት ፕሮግራም ተጠሪ
• ከሚያዚያ 1 ቀን 1997 ዓ.ም እስከ መስከረም 25 ቀን 2002 ዓ.ም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምዕራብ ሸዋ ዞን የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ መምሪያ የኦዲትና ቁጥጥር ኃላፊ
• ከመስከረም 26 ቀን 2002 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2002 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ ዞን በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ልማት ጽ/ቤት በከፍተኛ ኦዲተርነት
• ከታህሳስ 12 ቀን 2002 ዓ.ም እስከ መስከረም 8 ቀን 2011 ዓም በገንዘብ ሚኒስቴር በፋይናንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት የስራ መደብ ከባለሙያነት እስከ ቡድን መሪነት እንዲሁም
• ከጥቅምት 1 ቀን 2011 ዓም ጀምሮ ሕይወታቸው እስከ አለፈበት የካቲት 15 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዳይሬክተር በመሆን ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይሉ አገራቸውንና ህዝባቸውን በማገልገል ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
ባለትዳርና የአንድ ወንድና የሁለት ሴት ልጆች አባት የነበሩ ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓታቸው በዛሬው እለት በአምቦ መካነኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ላለፉት 29 ዓመታት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የስራ መደቦች ያገለገሉት የአቶ ልዑል ለገሰ ስርዓተ ቀብር ትናንት የካቲት 15 ቀን 2013 ዓም በአዲስ አበባ ተፈጽሟል፡፡
አቶ ልዑል ከአባታቸው ከአቶ ለገሰ አመጠ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ወርቅነሽ በላቸው ጥር 27 ቀን 1963 ዓ.ም በቀድሞው ሸዋ ክፍለ ሀገር መርሃቤቴ አውራጃ ቢጣ በለው ወረዳ ነበር የተወለዱት፡፡
አቶ ልዑል እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ቢጣ ጀግኖች 1ኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡
ከዚህ በኋላ በተለያዩ የትምህርት ተቋማት ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ድግሪ ድረስ ተምረዋል፡፡
አቶ ልዑል ከረጅም ጊዜ ትምህርት በተጨማሪም ሙያቸውን ለማሳደግ የተለያዩ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎችን ተከታትለዋል፡፡
በ1984 ዓ.ም በቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ መብራትና ኃይል ባለስልጣን በአሁኑ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቴክኒሽያንነት ሥራ የጀመሩት አቶ ልዑል ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ተቋሙ ባሉት የተለዩዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በቴክኒሽያንነት፣ በፎርማንነት፣ በዲስትሪክት ሱፐርቫይዘርነት፣ በዲስትሪቢዩሽን ኢንጅነርነት፣ በኮምፒውተር ፐሮግራመርት እና በአይሲቲ አፕሊኬሽን ኦፊሰርነት የስራ መደቦች ላይ ላለፉት 29 ዓመታት ተቋሙን በሙያቸው አገልግለዋል፡፡
አቶ ሉሌ በተወለዱ በ50 ዓመታቸው በድንገት ህይወታቸው ከዚህ ዓለም የተለየ ሲሆን ስርዓተ ቀብራቸውም በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ገርጂ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ የአቶ ልዑል ለገሰ የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ፣ ማኔጅመንትና ሠራተኞችም በአቶ ወንድሜነህ ልሳነወርቅ እና አቶ ልዑል ለገሰ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለፅ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
15 527
የሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል
…………..//////…………
ከአዲስ አበባ በ561 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በደቡብ ክልል በቤንቺ ማጂ ዞን በሚዛን ከተማ የሚገኘው የሚዛን 132/66/33/15 ኪ.ቮ. ከፍተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ተገቢውን አገልግሎት እየሠጠ ይገኛል፡፡
የጣቢያው ተወካይ ኃላፊ ወ/ት ታደለች ተረፈ እንደተናገሩት በ1998 ዓ.ም. ከቦንጋ ማከፋፈያ ጣቢያ 132 ኪ.ቮ. በመቀበል ለሚዛን ከተማና ለአካባቢው በ15 እና 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች ኃይል በመስጠት በይፋ ሥራ የጀመረው ጣቢያው አገልግሎቱን ሳያቋርጥ እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
እንደተወካይ ኃላፊዋ ገለፃ ማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ለሚዛን ከተማ ፣ ለሸኮ ወረዳ እና ለአካባቢው ሃይል ሲሰጥ በ 33 ኪ.ቮ ወጪ መስመሮች ደግሞ ለጨና፣ ለዲማ ወረዳዎች እና ለአካባቢው ኃይል በማቅረብ የሚጠበቅበትን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ማከፋፈያ ጣቢያው በደቡብ ምዕራብ ሪጅን ስር ካሉት 14 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል ከኃላፊነት ጀምሮ የሴቶች ሚና ጎልቶ የሚታየበትና የጣቢያው ኃላፊን ጨምሮ ሁለት ኦፕሬተሮች ሴቶች የሚገኙበት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
የካቲት 12 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
በመላው ትግራይ ኤሌክትሪክ ዳግም ተቋረጠ
………../////………….
የጁንታው ርዝራዦች በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በፈፀሙት ጥቃት በመላው ትግራይ ኤሌክትሪክ ተቋርጧል፡፡
የጁንታው ርዝራዦች አዲጉዶም በተባለ አካባቢ ከአላማጣ - መሆኒ - መቐለ በተዘረጋው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ባደረሱት ጥቃት ነው በክልሉ ኤሌክትሪክ የተቋረጠው፡፡
ከዚህ ቀደም መስመሩ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት እንደነበረና ለመጠገንም ረዘም ያለ ጊዜ እንደወሰደ ይታወሳል፡፡
ክልሉ ኃይል ከሚያገኝባቸው መስመሮች አንዱ የአላማጣ - መሆኒ - መቐለ መስመር ሲሆን የተከዜ አክሱም መስመር ደግሞ የጥገና ሥራው እየተከናወነ እንደነበር መገለፁ አይዘነጋም፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወደመውን መሰረተ ልማት ዳግም በመጠገን መልሶ ኃይል ለመስጠት እየሰራ ይገኛል::
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
የካቲት 10 ቀን 2013 ዓ.ም
15 527
በአባ ወረዳ አዲስ ባለ132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊገነባ ነው
…………/////……..
በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን በአባ ወረዳ በ48 ሚሊዮን ብር ወጪ አዲስ ባለ 132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሊገነባ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሰብስቴሽንና ትራንስሚሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኽኝ እንደገለፁት 1998 ዓ.ም. ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአባ ባለ 132/33 ኪ.ቮ. ማከፋፈያ ጣቢያ በ2012 ዓ.ም. በደረሰበት የመሬት መሸራተት የተነሳ አገልግሎት አቋርጧል፡፡
በመሆኑም ችግር የገጠመውን ማከፋፈያ ጣቢያ በአዲስ ባለ132/33 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለመተካት መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
አካባቢው ኃይል እንዳያጣ አደጋው በደረሰበት ወቅት ተቀሳቃሽ (የሞባይል) የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በጊዜያዊነት መተከሉን ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል፡፡
ተንቀሳቀሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ባሉት 3 ባለ 33 ኪ.ቮ. ወጪ መስመሮች ለዳወሮ እና ለኮንታ ዞኖች ኃይል እየሰጠ ይገኛል ፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሚገኝበት ቦታ የኦሞ ሸለቆ ውስጥ የሚገኝበት በመሆኑ ተደጋጋሚ የመሬት መሸራተት የሚከሰትበት አስቸጋሪ ቦታ ነው ፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም በተደረገው የአፈር ጥናት ከነባሩ ማከፋፈያ ጣቢያ በ18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ስሙ ቦሪቃ በሚባል አለታማ ቦታ ላይ አዲስ ማከፋፈያ ለመገንባት የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ዳሬክተሩ አብራርተዋል፡፡
የግንባታ ሥራው በተቋሙ የራስ ኃይል በሁለት ዓመት ያልቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አባ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከአዲስ አበባ በ451 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
የካቲት 08 ቀን 2013 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
