uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 560 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 357-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 160-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 560 obunachiga ega bo‘ldi.

25 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 32 ga, so‘nggi 24 soatda esa -5 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 26.03% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.88% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 052 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 472 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 8 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 26 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 560
Obunachilar
-524 soatlar
+167 kunlar
+3230 kunlar
Postlar arxiv
photo content
+9

በዞኑ 507 የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች አካላት ተሰርቀዋል .......///....... በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 507 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት መሰረቃቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። የተቋሙ እና የዞኑ አመራሮች ጋር በመሰረተ ልማት ላይ ስለሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች በተወያዩበት መድረክ ላይ የሪጅኑ የቴክኒክ ባለሙያ አቶ በሱፈቃድ ባዩ እንደገለፁት በሪጅኑ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከ1 ሺህ 3 መቶ በላይ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ላይ የስርቆት ወንጀል ተፈፅሟል። ከዚህ ውስጥ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ቦርደዴ፣ መኤሶ፣ ቡሲን አርቤ እና ኪቶን ካራ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች 507 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ተሰርቀዋል። ጉዳት የደረሰባቸውን የምሰሶ አካላት ዳግም ለመጠገን ከ2 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልፀዋል። ከ2011 እስከ 2016 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በሚያልፉ 119 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎች ላይ 744 ብረቶች ለስርቆት እንደተዳረጉ የጠቀሱት ባለሙያው ስርቆት የተፈፀመባቸውን የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አስታውሰዋል። እንደ አቶ በሱፈቃድ ገለፃ በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሮቹ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው የስርቆት ወንጀል በአምስት ዓመታት ውስጥ ከተፈፀመው ዝርፊያ ጋር እጅግ ተቀራራቢ ነው። ይህም በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ስር በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች  የሚፈፀመው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢነቱ እየጨመረ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል። በአካባቢው በተደራጀ መልኩ ስርቆት የሚፈፀም መሆኑ፣ የወሰን ማስከበር ጉዳይ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ቁርጠኝነት ማነስ እና የሥራ ትብብርን ከጥቅም ጋር የማያያዝ እንዲሁም ህብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት አፋጣኝ ጥቆማ አለመስጠቱ ለስርቆቱ መባባስ አስተዋጽኦ ማድረጉን ነው ባለሙያው ያብራሩት። በመሰረተ ልማቶቹ ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ከምንጩ ለማድረቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የምዕራብ ሀረርጌ ዞን እና የጭሮ ከተማ አስተዳደር በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ባለሙያው ያስገነዘቡት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

ህብረተሰቡን በማንቀሳቀስ በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ማስቆም ይገባል .......///......... በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረርጌ ዞን ህብረተሰቡን በማንቀሳቀስ በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎችን ማስቆም እንደሚገባ የዞኑ ጽ/ቤት ኃላፊ ገለፁ። የጽ/ቤት ኃላፊው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ ከምዕራብ ሀረርጌ ዞን እና ከተለያዩ ወረዳዎች ከተውጣጡ አመራሮች፣ የፀጥታ እና ደህንነት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከጭሮ ከተማ አስተዳደር ጋር በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ ስለሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ላይ በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ስለ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃላይ ገፅታና እንደ ተቋም በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ እየደረሱ ስላሉ ጉዳቶች አብራርተዋል። በተቋሙ የምስራቅ አንድ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ በበኩላቸው ከ2011 እስከ 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ዓመታት በዞኑና በከተማ አስተዳደሩ ስለተፈፀሙ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ሞሰሶዎች ስርቆት መጠንና ስርቆቱ በየትኞቹ አካባቢዎች እንደሚፈፀም ለተወያዮቹ ገለፃ አድርገዋል። የጭሮ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድ ዑመር የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎቹ በተደራጀ መልኩ ከተሰረቁ በኋላ ፖሊሶች ቁጥጥር የሚያደርጉባቸውን የፍተሻ ጣቢያዎች አቋርጠው ስለሚያልፉ ችግሩም ሆነ መፍትሔ ያለው በእኛው እጅ ነው ብለዋል። በአካባቢው የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን የሚቆርጡ፣ የሚደልሉ፣ የሚሸጡና የሚገዙ ግለሰቦችንና ለእነርሱ ሽፋን የሚሰጡ የፀጥታ አካላት የሚፈፅሙትን ወንጀል ለመከላከል ተደጋጋሚ የምክክር መድረኮች በማዘጋጀት ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባ ገልፀዋል። በምዕራብ ሀረርጌ ዞን የጉምቢ ወረዳ ቦርደዴ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ይርጋ ብሩ እንዳሉት በወረዳው በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ የሚገኘው የስርቆት ወንጀል እጅግ በጣም አስደንጋጭ ነው። የወረዳው ፀጥታ ዘርፍ የተሰረቁ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች መዳረሻቸውን የመለየትና የመፈተሽ ሥራዎችን መስራቱንም ጠቁመዋል። እንደ ኢንስፔክተር ይርጋ ገለፃ በአካባቢው ከማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ዝርፊያ በተጨማሪ በባቡር ሀዲድ ብረቶች ላይም መሰል ችግሮች እያጋጠሙ ይገኛሉ። የጭሮ ከተማ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዚያድ አማን በበኩላቸው  ከተማ አስተዳደሩ የመብራት መቋረጥን እንደ ፀጥታ ቾግር አድርጎ ይገነዘባል። የስርቆት ድርጊቱ የአካባቢው መገለጫ እንዳይሆን አበክረን እንሰራለን ብለዋል። እንደ አቶ ዚያድ ገለፃ ዝርፊያ ከሚፈፀምበት አካባቢ እስከ አዲስ አበባ ድረስ የተዘረጋ የስርቆት ሰንሰለት በመኖሩ ችግሩን ለማስቆም በጋራ መስራት ይገባል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ እንደገለፁት የኃይል መሰረተ ልማት ስርቆትን ለማስቀረት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም እየተሰራ ነው። የምዕራብ ሀረርጌ ዞንና የጭሮ ከተማ አስተዳደርም የስርቆት ወንጀሉን ለመከላከል የቁጥጥር ሥርዓታቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል። የምዕራብ ሀረርጌ ዞን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ አህመድ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ኤሌክትሪክ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ አመራሩ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ ዝርፊያዎች ላይ ትኩረት አድርጎ ሊሰራ እንደሚገባው ተናግረዋል። የስርቆት ወንጀሉን በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ ህጋዊና አስተማሪ  ርምጃ በመውሰድ ድርጊቱን ማስቆም እንደሚገባም ነው አቶ ቶፊቅ ያሳሰቡት። በውይይቱ ላይ የተሳተፉ አመራሮች ህብረተሰቡን በማንቃትና የስርቆት ወንጀሉን በመከላከል ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+9

ክሊኒኩ ለጣቢያው ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው .....//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ክሊኒክ የጣቢያው ሠራተኞች ጤንነታቸው ተጠብቆ ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ በቅርበት የህክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ። የክሊኒኩ ነርስ ሲስተር የትናየት አደረግሽ እንደገለጹት ክሊኒኩ የላቦራቶሪ አገልግሎትን ጨምሮ ተኝተው ለሚታከሙና ተመላላሽ ታካሚ ሠራተኞች የተሟላ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው። የጣቢያው ሠራተኛ በሥራ ላይ ለሚገጥማቸው አደጋም ሆነ ህመም ክሊኒኩ ሙሉ የሕክምና አገልግሎት እና የመድሃኒት አቅርቦት በነጻ እየሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። ማመንጫ ጣቢያው የሚገኝበት ቦታ በርሃማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥውን የወባ በሽታን ጨምሮ ልዩ ልዩ ወረርሽኞችን ለመከላከል በአካባቢው ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር በመተባበር የአጎበር እደላ እና የመድኃኒት ርጭት እንደሚከናወንም ተናግረዋል። ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችንና ወረርሽኞችን ቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ለጣቢያው ሠራተኞች እንደሚሰጡም ጠቁመዋል። ከክሊኒኩ አቅም በላይ በሚሆንበት ጊዜ ሠራተኞች ለተጨማሪ ህክምና ተቋሙ አብሮ ለመስራት ስምምነት ወደፈጸመባቸው ሆስፒታሎች ሪፈር እንደሚላኩም ጠቁመዋል። በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ክሊኒኩ ለ256 የጣቢያው ሠራተኞች የተመላላሽና ተኝተው የማከም ህክምና አገልግሎት መስጠቱን የጠቆሙት ሲስተር የትናየት ይህ የታካሚዎች አሃዝ በድግግሞሽ የህክምና አገልግሎት ያገኙ ሠራተኞችን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዋናው መስሪያ ቤት ካለው መካከለኛ ክሊኒክ በተጨማሪ በማመንጫ ጣቢያዎች 12 ክሊኒኮች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ ........///....... በ7ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን ገጥሞ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል። ሁለቱ ቡድኖች በድሬዳዋ ስቴዲየም ዛሬ ባከናወኑት ጨዋታ አቤል ሀብታሙ፣ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ እና ያሬድ የማነ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሶስቱን የማሸነፊያ ጎሎች አስቆጥረዋል። ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደጉትን ሁለት ጎሎች አንጋፋው አጥቂ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል። ብርቱ ፉክክር በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመስመር ላይ የተመሰረተ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲከተል ፋሲል ከነማ በአንፃሩ ኳስን በመቆጣጠር የጨዋታ ብልጫ ለመውሰድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቷል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ በሊጉ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

photo content

የሁለቱ ተቋማት አመራሮች የደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ ........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች የደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያን ዛሬ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት የፌዴራል  ፖሊስ የምዕራብ ኦሮሚያ አዛዥ ኮማንደር ማሙዬ አባተ እንዳሉት የተቋሙ አመራሮች በግዳጅ ላይ ያሉትን የሠራዊት አባላት መጎብኘታቸው ለሠራዊቱ አባላት የሞራል ጥንካሬ ይሰጣል። ማከፋፈያ ጣቢያው በረሃማ ቦታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ የውሃ አቅርቦት እንዲስተካከል እና የወባ መከላከያ አጎበር እንዲሰጣቸው እንዲሁም የጥበቃ ማማ እንዲገነባላቸው ጠይቀዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ደህንነትና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት ተቋሙ ከፌደራል ፖሊስና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የመሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ ይገኛል። በሠራዊቱ አመራሮች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር እንደሚነጋገሩም ገልፀዋል። በተቋሙ የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ በበኩላቸው  ለጥበቃ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የንብረት ማስቀመጫ መጋዘን ለመገንባት መታቀዱንና ያልተሟሉ ፋሲሊቲዎችን ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመነጋገር ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው የማስፋፊያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ……...///…….... የቦሌ ለሚ ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማከፋፈያ  ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ተስፋዬ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ግንባታ የተከናወነው ጣቢያው ኃይል የመጫን አቅሙ በመቀነሱ ሳይሆን በ15 ኪሎ ቮልት ተጨማሪ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ በመታሰቡ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአካባቢው የ15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር መጨመር ለማስፋፊያ ግንባታው ዋና ምክንያት እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ አቶ ዮሐንስ ገለፃ የማስፋፊያ ሥራው የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታዎችን ጨምሮ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንፎርመር የማስቀመጥ፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ቤት ግንባታ፣ የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ገጠማና በ230 ኪሎ ቮልት በኩል የቤይ ዕቃዎችን የመትከል እንዲሁም የፍተሻና የሙከራ ሥራዎችን ያጠቃልላል። የቦሌ ለሚ የማከፋፈያ ጣቢያ በተደረገለት የማስፋፊያ ግንባታ በአሁኑ ወቅት ስድስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንደተገነቡለት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህም ለቦሌ አራብሳ፣ በሻሌና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ዝግጁ የተደረጉት አዳዲሶቹ ወጪ መስመሮች ኃይል መስጠት የሚጀምሩት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የማሰራጫ መስመሮች ከተዘረጉ በኋላ በመሆኑ ለአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ለዲስትሪክቱ የማሳወቅ ሥራ መሰራቱን አስታውቀዋል፡፡ የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች የልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አብራርተዋል። የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም በመከናወኑ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን እንዳስቻለም ነው አቶ ዮሐንስ የገለፁት። የማስፋፊያ ሥራው በሪጅኑ አቅም እንዲከናወን የተቋሙ የሥራ አመራር እና የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለሰጡት ዕድልና ኃላፊነት እንዲሁም በሥራው ላይ ለተሳተፉ ባለሙያዎች ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። የቦሌ ለሚ የማከፋፈያ ጣቢያ ካሉት 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች መካከል ለኢንዱስትሪዎችና ለከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ኤሌክትሪክ እያቀረቡ የሚገኙት ዘጠኙ ብቻ ናቸው። ማከፋፈያ ጣቢያው ከ240 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው አንድ ባለ 50 እና  ሁለት ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት። በ15 ሚሊየን ብር በጀት የተከናወነውን የቦሌ ለሚ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ለማጠናቀቅ ሁለት ዓመት ጊዜ ወስዷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት ስሜት እንዲጠበቅ ማድረግ ይገባል ……….///……… ሁሉም የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች በየአካባቢያቸው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት ስሜት እንዲጠብቁ የምስራቅ ወለጋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አሳሰቡ፡፡ የነቀምቴ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ምስጋኑ ቱሉ በበኩላቸው ያለ ኤሌክትሪክ የትኛውንም ዕቅድ ማሳካት ስለማይቻል በአጥፊዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች ትናንት የምስራቅ ወለጋ ዞን እና ከዞኑ 18 ወረዳዎች የተውጣጡ አመራሮች እንዲሁም የነቀምቴ ከተማ አመራሮች በተሳተፉባቸው ሁለት መድረኮች ላይ በመገኘት ተቋሙን እየፈተኑት ስላሉት የመሰረተ ልማት ስርቆት ወንጀሎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ደህንነት ቁጥጥር እና ክትትል ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት በዞኑ ሥርቆት በሚበዛባችው ጉቶ ወረዳ - ሶረቃ ቀበሌ፣ ሁኪ ከተማ ዙሪያ፣ ሌቃ ዱለቻ ወረዳ፣ ደዴሳ አካባቢ፣ ጅማ አርጆ ወረዳ፣ ጊዳ አያና ወረዳ -ጉትን ከተማ አመራሩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 464/97 አንቀጽ 3 እንደተደነገገው ሁሉም የመንግስት መዋቅር የኤሌክትሪክና የቴሌኮም መሠረት ልማቶችን የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡ በአዋጁ የተጣለባቸውን ግዴታ በማይወጡ አመራሮች ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚያችል አሰራር መዘርጋት እንደሚገባም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በየደረጃው ከሚገኙ አመራሮች ጋር የመሰረተ ልማቶቹ በሚጠበቁበት ሁኔታ የተጀመረው ወይይት በመላው ሀገሪቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ በተቋሙ የንብረት እና ጠቅላላ አግልግሎት ዘርፍ የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ በበኩላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ረጅም ኪሎ ሜትሮችን ስለሚያቆራርጡ የመሰረተ ልማቱን መጠበቅ የሁሉንም ተሳትፎ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም ከማህበረሰቡና በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አንስተው አመራሩ በኃላፊነት ስሜት እንዲሰራ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል፡፡ ምክትል አስተዳዳሪው አቶ ገመዳ ተረፈ በዞኑ በተዘጋጁ መድረኮች ላይ ለተሳተፉ ከ18 ወረዳ ለተውጣጡ አመራሮች እንደገለፁት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መጠበቅ ለሁሉም የተሰጠ በመሆኑ የቀበሌና የወረዳ አመራሮች በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቅ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በዞኑ ሁኬ ከተማ በተካሄደ የተቀናጀ ፍተሻ ብዛት ያላችው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት አካላት በጋሪ ላይ የበየዱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማካሄድ ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ መሰረተ ልማቱን በማስጠበቅ ረገድ የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት አመራሮቹ የተሻለ ወጤት ለማምጣት እንዲሰሩም አሳስበዋል፡፡ የነቀምቴ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ምስጋኑ ቱሉ በበኩላቸው ያለ ኤሌክትሪክ የትኛውንም ዕቅድ ማሳካት ስለማይቻል በአጥፊዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል፡፡ የህዝብ እና የመንግሥትን ንብረት የማይጠበቅ አመራር ካለ ተጠያቂነት እንደሚኖርበት ሊያውቅ ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

10 ሰዓታት የፈጀው የጥገና ሥራ በስኬት ተጠናቋል ……..///……… ከትናንት በስቲያ በእሳት አደጋ ምክንያት በጊዜያዊነት አገልግሎት መስጠት ያቋረጠውን የድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ መስመር የማዛወር ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት ትናንት ምሽት ከ1:00 ሰዓት እስከ ሌሊት 11፡00 ከሁርሶ ወደ ድሬዳዋ አንድ፣ ወደ ሀረር እና ጅግጅጋ የሚሄዱ መስመሮችን የማዛወር ሥራ ተሰርቷል፡፡ ዛሬ ረፋድ መስመሩን የመፈተሽ ሥራ ተከናውኖ ወደሁሉም አካባቢዎች ኃይል እንደደረሰ መረጋገጡን ገልፀዋል። የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ጉዳት እንዳጋጠመው ተደርጎ የተሰራጨው ዘገባ የሀሰት መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ከሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ወጪ መስመር በማዘጋጀት ችግሩ መፈታቱን አስታውቀዋል፡፡ ፈታኝ የሆነው የመስመር ማዛወር ሥራ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟቸው በነበሩ አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች በትዕግስት ስለጠበቁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም